#AddisAbaba #ንግድ
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ማህበረሰብ ያለወከባ በተረጋጋ መንፈስ የንግድ ተግባሩን ለማከናወን እንዲያስችል ዕድል ይፈጥርለታል የተባለ አዲስ መመሪያ ስራ ላይ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።
አዲሱ መመሪያ " በመንደር ንግድ ቁጥጥር አሰራር ስርዓት መመሪያ 159/2016 " እንደሚባል ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
መመሪያው በየትኛው አስተዳደር እርከን የትኛው አይነት እርምጃ እንደሚወሰድ በግልጽ ያስቀመጠ ሲሆን ይህም ሲታይ የነበረውን ግልጽ እና ፍትሃዊ ያልሆነ አሰራር ያስቀራል ተብሏል።
በአዲሱ የመንደር ንግድ መመሪያ መሰረት የወረዳ የንግድ ቁጥጥር ባለሙያ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ ህጉ የሚፈቅድለት በተመደበበት መንደር ላይ ፦
➡ ያለ ንግድ ፍቃድ
➡ ባልታደሰ ፍቃድ
➡ በታገደ አልያም በተሰረዘ ንግድ ፈቃድ የሚነግድ የንግድ ድርጅት ላይ #ብቻ_ነው። ይህን ሲያደርግም ለቅርብ ኃላፊ ማሳወቅ አለበት።
ከዚህ ወጪ ያሉት ጥፋቶች #በሙሉ እርምጃ ሳይወስድ ለቅርብ ኃላፊው በፅሁፍ በማሳወቅ ለውሳኔ ወደ ንግድ ቢሮ መላክ ይጠበቅበታል ፤ የተወሰነውን ውሳኔ የማስፈፀም ኃላፊነትም አለበት።
መመሪያው ፦ https://t.me/tikvahethiopia/87886
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
አማራጭ የሕግ እውቀት
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/
👉 LinkedIn 👈
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/
👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ማህበረሰብ ያለወከባ በተረጋጋ መንፈስ የንግድ ተግባሩን ለማከናወን እንዲያስችል ዕድል ይፈጥርለታል የተባለ አዲስ መመሪያ ስራ ላይ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።
አዲሱ መመሪያ " በመንደር ንግድ ቁጥጥር አሰራር ስርዓት መመሪያ 159/2016 " እንደሚባል ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
መመሪያው በየትኛው አስተዳደር እርከን የትኛው አይነት እርምጃ እንደሚወሰድ በግልጽ ያስቀመጠ ሲሆን ይህም ሲታይ የነበረውን ግልጽ እና ፍትሃዊ ያልሆነ አሰራር ያስቀራል ተብሏል።
በአዲሱ የመንደር ንግድ መመሪያ መሰረት የወረዳ የንግድ ቁጥጥር ባለሙያ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ ህጉ የሚፈቅድለት በተመደበበት መንደር ላይ ፦
➡ ያለ ንግድ ፍቃድ
➡ ባልታደሰ ፍቃድ
➡ በታገደ አልያም በተሰረዘ ንግድ ፈቃድ የሚነግድ የንግድ ድርጅት ላይ #ብቻ_ነው። ይህን ሲያደርግም ለቅርብ ኃላፊ ማሳወቅ አለበት።
ከዚህ ወጪ ያሉት ጥፋቶች #በሙሉ እርምጃ ሳይወስድ ለቅርብ ኃላፊው በፅሁፍ በማሳወቅ ለውሳኔ ወደ ንግድ ቢሮ መላክ ይጠበቅበታል ፤ የተወሰነውን ውሳኔ የማስፈፀም ኃላፊነትም አለበት።
መመሪያው ፦ https://t.me/tikvahethiopia/87886
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
አማራጭ የሕግ እውቀት
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/
👉 LinkedIn 👈
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/
👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
#ጉምሩክ
🔴 “ በኢንቮይስም ከፍለን እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ አሉን ” - አስመጪዎች
⚫️ “ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም” - ኮሚሽኑ
ጉምሩክ ኮሚሽን ከማክሮ ኢኮኖሚ ፓሊሲ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ባወጣው አዲስ መመሪያ "ከእጥፍ በላይቀረጥ ክፈሉ'' እየተባሉ መሆኑን አስመጪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ኮሚሽኑም ከቅሬታው በኋላ ማሻሻያ ማድረጉን መረጃ ነግረናችሁ ነበር።
ሆኖም ከ150 በላይ የሚሆኑ “ በኢነቮይስ ከፍለናል ” የሚሉ አስመጪዎች፣ ኮሚሽኑ ከማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ትግበራወሰ በኋላ ያወረደውና በአስመጪዎች በኩል “ አዋጅን በደብዳቤ ሽሯል ” በሚል ቅሬታ ቀርቦበት ኮሚሽኑ በድጋሚ ማሻሻያ አደረኩበት ያለው ደብዳቤም ቅሬታቸውን እንዳልፈታላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
በዚህም እንዲያወያያቸው ጭምር ኮሚሽኑን በደብዳቤ እንደጠቁ ሆኖም ምላሽ እንዳልጠሰጣቸው ገልጸው፤ ጉዳዩን በድጋሚ እንዲያጤነው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።
አስመጪዎች በዝርዝር ያቀረቡት ቅሬታ ምንድን ነው ?
“ ደብዳቤው (ማስተካከያ የተደረገበት) መልስ ስላልሰጠን መልሰን ደብዳቤ ፃፍንላቸው፡፡ ምክንያቱም ከማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ በፊት የገቡ እቃዎች እንዲስተካከሉ ተብሎ ብዙዎቹም አውጥተዋል፡፡
የእኛ ጥያቄ፤ ቅድሚያ እቃው ዶኩሜንት እንደደረሰን ጂቡቲ ላይ እንዳለ በኢንቮይስ ዲክላራሲዮን ይቆረጣል። ጂቡቲ ጭነት ሊዘገይ ስለሚችል ፤ በየሳምንቱ ደግሞ ሬት ስለሚቀይር ያንን ነገር እንዳይነካው ሁሉም ነጋዴ ከዚህ በፊት ለዓመታት የሰራው በዚህ አይነት አካሄድ ነው፡፡
እቃው ጂቡቲ እያለ ዶኩሜንቱ ከመጣ በኢንቮይስ ይከፈላል። ቀሪ ሂሳብ ደግሞ ከፍተሻ በኋላ 'ይለቀቅ' ሲባል ያኔ ተከፍሎ ይመጣል፡፡ አሁን ግን በኢንቮይስም ከፍለን 'እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ' አሉን፡፡
እኛ ደግሞ አልተስማማንም፡፡ ጉምሩክ በገባበት ሳይሆን ዶኩሜንት ባስገባንበት፤ ዲክራላሲዮን ባስቆረጥንበት ነው መስተናገድ ያለብን፡፡ 5 ሚሊዮን ስንከፍል የነበርነው 10 ሚሊዮን፣ 10 ሚሊዮን ይከፍል የነበረ 20 ሚሊዮን ብር ከፈሉ እየተባልን ነው፡፡
አሁን ጠዋት አንድ ሬት ከሰዓት ሌላ ሬት አለው ጉምሩክ፤ ድሮ ግን በየሳምንቱ አንድ ሬት ነበረው፡፡ ሐሙስ ቀን የሚቀየር ሬት ብቻ ነበር የሚሰጡት፡፡
ይህ ደግሞ ኪሳራና ተጠቃሚውም ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚጣመጣበት ጉምሩክም ይገነዘባል፡፡ ይህን ነገር ቢያስተካካል ባለው ዋጋ መሸጥ ይቻላል ” ነው ያሉት፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቀረበው ቅሬታ የኮሚሽኑ ምላሽ ምንድን ነው ? ኮሚሽኑ ባለፈው አደረኩት ባለው ማሻሻያ የአሁኖቹ ቅሬታ አቅራቢዎችን ጉዳይ አካቶ ምላሽ ሰጥቷል? ከሆነ እንዴት ? ሲል ጉምሩክ ኮሚሽኑንን ጠይቋል።
የኮሚሽን ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።
“ ኮሚሽኑ የተለዬ ምላሽ የለውም ከዚያ ጉዳይ ጋር በተያያዘ። የተሰጠው ምላሽ ሁሉንም ጉዳዮች ከቨር ያደረገ ስለሆነ ቀደም ሲል በወጣ ደብዳቤ ምላሽ የተሰጠበት ጉዳይ ነው፡፡
የተለዬ ኮሚሽኑ የሚያየው ጉዳይ የሌለ መሆኑን ነው የማውቀው። ሁሉም ጉዳዮች እዛ ላይ ቴኪኒካሊ ከጉምሩክ አዋጅ አንጻር ታይተው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
አጠቃላይ ነው ባለፈውም አቤቱታ የቀረበው፡፡ ስለዚህ ምላሽ የተሰጠበት አግባብ አለ፡፡ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም፤ ይታወቃል።
'መስተናገድ የለብን በዚህ የሚል ጉዳይ' ካለ ኮሚሽኑ የሰጠውን ምላሽ መቃወም መብት ነው። ተራ ቁጥር 1፣ 2፣ 3፣ 4 በሚሉ ተራ ቁጥሮች ላይ ተገልጿል፡፡
የተቀመጡት ኮንዲሽኖች ጂቡቲ ላሉት እቃዎች፣ አገር ውስጥ ላልገባ እቃ በነባሩ የውጭ ምንዛሪ እንስተናገድ ነው ጥያቄያቸው። ያነም ኮሚሽኑ ደብዳቤው ላይ በገለጸው ልክ (ተራቁጥር አራት ይመስለኛል) በግለጽ የተቀመጠ ጉዳይ ነው።
እነርሱ አቤቱታቸውን መቀጠል ይችላሉ፤ ኮሚሽኑ እኮ ከዚህ አንጻር የከለከለው ነገር የለም፡፡ ስለዚህ የተሰተው ምላሽ ይሄው ነው ከዚያ ውጪ የተለየ የሚሰጥ ምላሽ የለንም በዚያ ደብዳቤ ተመልሶ ያለፈ ጉዳይ ስለሆነ” ብለዋል።
#TikvahethiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ በኢንቮይስም ከፍለን እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ አሉን ” - አስመጪዎች
⚫️ “ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም” - ኮሚሽኑ
ጉምሩክ ኮሚሽን ከማክሮ ኢኮኖሚ ፓሊሲ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ባወጣው አዲስ መመሪያ "ከእጥፍ በላይቀረጥ ክፈሉ'' እየተባሉ መሆኑን አስመጪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ኮሚሽኑም ከቅሬታው በኋላ ማሻሻያ ማድረጉን መረጃ ነግረናችሁ ነበር።
ሆኖም ከ150 በላይ የሚሆኑ “ በኢነቮይስ ከፍለናል ” የሚሉ አስመጪዎች፣ ኮሚሽኑ ከማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ትግበራወሰ በኋላ ያወረደውና በአስመጪዎች በኩል “ አዋጅን በደብዳቤ ሽሯል ” በሚል ቅሬታ ቀርቦበት ኮሚሽኑ በድጋሚ ማሻሻያ አደረኩበት ያለው ደብዳቤም ቅሬታቸውን እንዳልፈታላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
በዚህም እንዲያወያያቸው ጭምር ኮሚሽኑን በደብዳቤ እንደጠቁ ሆኖም ምላሽ እንዳልጠሰጣቸው ገልጸው፤ ጉዳዩን በድጋሚ እንዲያጤነው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።
አስመጪዎች በዝርዝር ያቀረቡት ቅሬታ ምንድን ነው ?
“ ደብዳቤው (ማስተካከያ የተደረገበት) መልስ ስላልሰጠን መልሰን ደብዳቤ ፃፍንላቸው፡፡ ምክንያቱም ከማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ በፊት የገቡ እቃዎች እንዲስተካከሉ ተብሎ ብዙዎቹም አውጥተዋል፡፡
የእኛ ጥያቄ፤ ቅድሚያ እቃው ዶኩሜንት እንደደረሰን ጂቡቲ ላይ እንዳለ በኢንቮይስ ዲክላራሲዮን ይቆረጣል። ጂቡቲ ጭነት ሊዘገይ ስለሚችል ፤ በየሳምንቱ ደግሞ ሬት ስለሚቀይር ያንን ነገር እንዳይነካው ሁሉም ነጋዴ ከዚህ በፊት ለዓመታት የሰራው በዚህ አይነት አካሄድ ነው፡፡
እቃው ጂቡቲ እያለ ዶኩሜንቱ ከመጣ በኢንቮይስ ይከፈላል። ቀሪ ሂሳብ ደግሞ ከፍተሻ በኋላ 'ይለቀቅ' ሲባል ያኔ ተከፍሎ ይመጣል፡፡ አሁን ግን በኢንቮይስም ከፍለን 'እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ' አሉን፡፡
እኛ ደግሞ አልተስማማንም፡፡ ጉምሩክ በገባበት ሳይሆን ዶኩሜንት ባስገባንበት፤ ዲክራላሲዮን ባስቆረጥንበት ነው መስተናገድ ያለብን፡፡ 5 ሚሊዮን ስንከፍል የነበርነው 10 ሚሊዮን፣ 10 ሚሊዮን ይከፍል የነበረ 20 ሚሊዮን ብር ከፈሉ እየተባልን ነው፡፡
አሁን ጠዋት አንድ ሬት ከሰዓት ሌላ ሬት አለው ጉምሩክ፤ ድሮ ግን በየሳምንቱ አንድ ሬት ነበረው፡፡ ሐሙስ ቀን የሚቀየር ሬት ብቻ ነበር የሚሰጡት፡፡
ይህ ደግሞ ኪሳራና ተጠቃሚውም ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚጣመጣበት ጉምሩክም ይገነዘባል፡፡ ይህን ነገር ቢያስተካካል ባለው ዋጋ መሸጥ ይቻላል ” ነው ያሉት፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቀረበው ቅሬታ የኮሚሽኑ ምላሽ ምንድን ነው ? ኮሚሽኑ ባለፈው አደረኩት ባለው ማሻሻያ የአሁኖቹ ቅሬታ አቅራቢዎችን ጉዳይ አካቶ ምላሽ ሰጥቷል? ከሆነ እንዴት ? ሲል ጉምሩክ ኮሚሽኑንን ጠይቋል።
የኮሚሽን ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።
“ ኮሚሽኑ የተለዬ ምላሽ የለውም ከዚያ ጉዳይ ጋር በተያያዘ። የተሰጠው ምላሽ ሁሉንም ጉዳዮች ከቨር ያደረገ ስለሆነ ቀደም ሲል በወጣ ደብዳቤ ምላሽ የተሰጠበት ጉዳይ ነው፡፡
የተለዬ ኮሚሽኑ የሚያየው ጉዳይ የሌለ መሆኑን ነው የማውቀው። ሁሉም ጉዳዮች እዛ ላይ ቴኪኒካሊ ከጉምሩክ አዋጅ አንጻር ታይተው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
አጠቃላይ ነው ባለፈውም አቤቱታ የቀረበው፡፡ ስለዚህ ምላሽ የተሰጠበት አግባብ አለ፡፡ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም፤ ይታወቃል።
'መስተናገድ የለብን በዚህ የሚል ጉዳይ' ካለ ኮሚሽኑ የሰጠውን ምላሽ መቃወም መብት ነው። ተራ ቁጥር 1፣ 2፣ 3፣ 4 በሚሉ ተራ ቁጥሮች ላይ ተገልጿል፡፡
የተቀመጡት ኮንዲሽኖች ጂቡቲ ላሉት እቃዎች፣ አገር ውስጥ ላልገባ እቃ በነባሩ የውጭ ምንዛሪ እንስተናገድ ነው ጥያቄያቸው። ያነም ኮሚሽኑ ደብዳቤው ላይ በገለጸው ልክ (ተራቁጥር አራት ይመስለኛል) በግለጽ የተቀመጠ ጉዳይ ነው።
እነርሱ አቤቱታቸውን መቀጠል ይችላሉ፤ ኮሚሽኑ እኮ ከዚህ አንጻር የከለከለው ነገር የለም፡፡ ስለዚህ የተሰተው ምላሽ ይሄው ነው ከዚያ ውጪ የተለየ የሚሰጥ ምላሽ የለንም በዚያ ደብዳቤ ተመልሶ ያለፈ ጉዳይ ስለሆነ” ብለዋል።
#TikvahethiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔈 #የዜጎችድምጽ
" ወረዳው ከነእቃዬ ሜዳ ላይ ጥሎኝ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " - እንባ የሚተናነቃት ወጣት
በአዲስ አበባ አስተዳደር የካ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ቀበሌ 9/10 የምትገኝ ወጣት ከአሳዳጊ አክስቷ ጋር ትኖርበት ከነበረው የቀበሌ ቤት አሳዳጊዋ ስትሞት ከቤቱ እንድትወጣ ተደርጋ ጎዳና እንደወጣች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል እሮሮ አሰምታለች።
" ወረዳው ከነእቃዬን ሜዳ ጥሎ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " ብላለች።
ወርቅነሽ አለሙ የምትባለው ይህች ወጣት የአባቷ ታላቅ እህት ከ3 ዓመቷ ጀምሮ ከባህር ዳር ወደ አ/አ አምጥታት ነው ያሳደገቻት።
እዚሁ ቤት እስከ 2016 ዓ/ም ማለቂያ ድረስ ነበሩ።
በ2016 ዓ/ም አሳዳጊ አክስቷ ከሞትች ከ40 ቀናት በኃላ ወረዳው " ወራሽ ልጅ ስላልሆሽ ልቀቂ " ይላታል።
ጉዳዩን ይዛ ፍርድ ቤት ሄደች። ፍርድ ቤትም ሄዳ መፍትሄ አልተሰጣትም።
" ወረዳ እኔን ጠዋት በግብረ ኃይል ከነእቃዬ አውጥቶ ጥሎኝ ከሰዓት በኋላ ራሱ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ቤቴ ውስጥ አስገባው " ስትል ቅሬታ አሰምታለች።
ከዚህ አለፍ ሲል ቤቱ ሁለት ክፍል ሆኖ ሳለ ወደ አራት ክፍል አስፋፍቶ ሰርቶት ዞር ብሎ የጠየቀው አካል የለም ብላለች።
ወረዳው ምን ምላሽ ሰጠ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታውን ይዞ የወረዳ 6 ጽ/ቤት አስተዳደር ኃላፊ አቶ ምስጋናው ሂጂቱን አነጋግሯል።
ቅሬታዋ አቅራቢዋ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብት እንዳላት አምነውበታል።
ኃላፊው ፤ " ባለመብት ናት የቀበሌ ቤት መውረስ የሚችለው ልጅ ነውና ልጅ ከሆነች መውረስ መብቷ ነው " ብለዋል።
" በሕጉ መሠረት የቀበሌ ቤት ፣ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብቷ የተጠበቀ ነው ፤ በዚያ ደረጃ ሆኖ ከነበረ እኔ ጋ ይምጡ እናስተካክላለን ይሄ የተነሳው ጉዳይ ትክክል ከሆነ " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ ጉዳይ ተጨማሪ ማብራሪያ እና ግልጽነት ስለሚፈልግ የሕግ ባለሙያ አነጋግሯል።
የሕግ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ምን አሉ ?
- ኑዛዜውን ማጽደቅ ትችላለች። ግን የቀበሌ ቤት ላይ ተወላጆች ካልሆኑ በስተቀር ከሕግ አንጻር በባዮሎጂካል ተወላጅ ያልሆነ ልጅ የጉጂፈቻ ማስረጃ ቀደም ሲል ሊኖር ይገባል።
- ለቀበሌ ቤት የጉዲፈቻ ማስረጃ ስሌላት ውርስ ተቀባዩዋን ከሞራልና ከአስተዳደራዊ አንጻር ካልሆነ በስተቀር ከሕግ አንጻር የወረዳው አስተደዳደር ሊያስተናግዳት አይችልም።
- ከሞራል አንጻር አሳዳጊዋ ስላረፉ፣ ልጅቷ ደግሞ ተተኪ ልጅ ናት፤ በሥነ ልቦና እናትና ልጅ ሆነው አብረው ኖረዋል። የቀበሌ ቤት የሚባለው ደግሞ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች የሚኖበት ነው። ስለዚህ ከሕግ አንጻር የኑዛዜ ተቀባይ መሆን ባትችልም አንዱ ወጥቶ ሌላው የሚገባበት፣ ለዜጎች የተሰራ ቤት በመሆኑ ልትኖርበት ይገባ ነበር ከሞራል አንጻር።
- ከሕግ አንጻር በቀበሌ ቤት ላይ ኑዛዜ ማድረግ አይቻልም።
- ለምሳሌ የፌደራል ኪራይ ቤቶችን አንድ ሰው ተከራይቶ ቢኖር ሲሞት ሊናዘዝበት አይችልም። ምክንያቱም የንብረቱ ባለቤት መንግስት ነው። በመሳሳይ ሁኔታ የቀበሌ ቤቶች ውስጥ የሚኖር ሰው ሲሞት ኑዛዜ ሊያደርግ አይችልም። ኑዛዜ ማድረጉ በሕግ ውጤት አያመጣም።
- በዜጎች ንብረትና ሕይወት ላይ ውሳኔ የሚሰጡ ሰዎች (ዳኞች) ከወረዳ ጋር በመመሳጠር ክርክር በተነሳበት የመንግስት ቤት ውስጥ መግባት የሕግ ጥሰት ነው። ሕግን ያልተከተለ አካሄድ ነው። በተወሰነ ደረጃ ሙስና ተብሎ ጉዳዩን ወደ ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ብታመለክትበት ዳኛው ከኃላፊነቱ የሚነሳበት ቀጥተኛ ማስረጃ ነው የሚሆነው።
- ክርክር በተነሳበት ጉዳይ ላይ የጥቅም ግንኙነት በመፍጠር እንዲህ ማድረግ ትልቅ የዲሲፒሊን ጥፋት ነው።
- ልጅቷ ቅጹ ላይ አለች፣ ደባል ናት፣ የቤተሰብ አባል ናት ቀጥተኛ ልጅ ባትሆንም፣ የቀበሌ ቤቶች ደግሞ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎቸ ነው የተዘጋጁት፣ ሜዳ ላይ መጣል የለባትም ብሎ የወረዳው አስተዳደር ወስኖ ወይ በዚያው ቤት ሊያስቀጥላት ይገባል የቀበሌ ቤቱ የሚፈርስ ከሆነም ምትክ የመንግስት ቤት እንድታገኝ ሁኔታዎችን ማመቻቸት አለበት።
- በህሊና ፍርድ ወይ አስተዳደራዊ በሆነ መንገድ የወረዳው አስተዳደር መፍትሄ ሊሰጣት ይገባል።
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-08
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ወረዳው ከነእቃዬ ሜዳ ላይ ጥሎኝ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " - እንባ የሚተናነቃት ወጣት
በአዲስ አበባ አስተዳደር የካ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ቀበሌ 9/10 የምትገኝ ወጣት ከአሳዳጊ አክስቷ ጋር ትኖርበት ከነበረው የቀበሌ ቤት አሳዳጊዋ ስትሞት ከቤቱ እንድትወጣ ተደርጋ ጎዳና እንደወጣች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል እሮሮ አሰምታለች።
" ወረዳው ከነእቃዬን ሜዳ ጥሎ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " ብላለች።
ወርቅነሽ አለሙ የምትባለው ይህች ወጣት የአባቷ ታላቅ እህት ከ3 ዓመቷ ጀምሮ ከባህር ዳር ወደ አ/አ አምጥታት ነው ያሳደገቻት።
እዚሁ ቤት እስከ 2016 ዓ/ም ማለቂያ ድረስ ነበሩ።
በ2016 ዓ/ም አሳዳጊ አክስቷ ከሞትች ከ40 ቀናት በኃላ ወረዳው " ወራሽ ልጅ ስላልሆሽ ልቀቂ " ይላታል።
ጉዳዩን ይዛ ፍርድ ቤት ሄደች። ፍርድ ቤትም ሄዳ መፍትሄ አልተሰጣትም።
" ወረዳ እኔን ጠዋት በግብረ ኃይል ከነእቃዬ አውጥቶ ጥሎኝ ከሰዓት በኋላ ራሱ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ቤቴ ውስጥ አስገባው " ስትል ቅሬታ አሰምታለች።
ከዚህ አለፍ ሲል ቤቱ ሁለት ክፍል ሆኖ ሳለ ወደ አራት ክፍል አስፋፍቶ ሰርቶት ዞር ብሎ የጠየቀው አካል የለም ብላለች።
ወረዳው ምን ምላሽ ሰጠ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታውን ይዞ የወረዳ 6 ጽ/ቤት አስተዳደር ኃላፊ አቶ ምስጋናው ሂጂቱን አነጋግሯል።
ቅሬታዋ አቅራቢዋ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብት እንዳላት አምነውበታል።
ኃላፊው ፤ " ባለመብት ናት የቀበሌ ቤት መውረስ የሚችለው ልጅ ነውና ልጅ ከሆነች መውረስ መብቷ ነው " ብለዋል።
" በሕጉ መሠረት የቀበሌ ቤት ፣ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብቷ የተጠበቀ ነው ፤ በዚያ ደረጃ ሆኖ ከነበረ እኔ ጋ ይምጡ እናስተካክላለን ይሄ የተነሳው ጉዳይ ትክክል ከሆነ " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ ጉዳይ ተጨማሪ ማብራሪያ እና ግልጽነት ስለሚፈልግ የሕግ ባለሙያ አነጋግሯል።
የሕግ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ምን አሉ ?
- ኑዛዜውን ማጽደቅ ትችላለች። ግን የቀበሌ ቤት ላይ ተወላጆች ካልሆኑ በስተቀር ከሕግ አንጻር በባዮሎጂካል ተወላጅ ያልሆነ ልጅ የጉጂፈቻ ማስረጃ ቀደም ሲል ሊኖር ይገባል።
- ለቀበሌ ቤት የጉዲፈቻ ማስረጃ ስሌላት ውርስ ተቀባዩዋን ከሞራልና ከአስተዳደራዊ አንጻር ካልሆነ በስተቀር ከሕግ አንጻር የወረዳው አስተደዳደር ሊያስተናግዳት አይችልም።
- ከሞራል አንጻር አሳዳጊዋ ስላረፉ፣ ልጅቷ ደግሞ ተተኪ ልጅ ናት፤ በሥነ ልቦና እናትና ልጅ ሆነው አብረው ኖረዋል። የቀበሌ ቤት የሚባለው ደግሞ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች የሚኖበት ነው። ስለዚህ ከሕግ አንጻር የኑዛዜ ተቀባይ መሆን ባትችልም አንዱ ወጥቶ ሌላው የሚገባበት፣ ለዜጎች የተሰራ ቤት በመሆኑ ልትኖርበት ይገባ ነበር ከሞራል አንጻር።
- ከሕግ አንጻር በቀበሌ ቤት ላይ ኑዛዜ ማድረግ አይቻልም።
- ለምሳሌ የፌደራል ኪራይ ቤቶችን አንድ ሰው ተከራይቶ ቢኖር ሲሞት ሊናዘዝበት አይችልም። ምክንያቱም የንብረቱ ባለቤት መንግስት ነው። በመሳሳይ ሁኔታ የቀበሌ ቤቶች ውስጥ የሚኖር ሰው ሲሞት ኑዛዜ ሊያደርግ አይችልም። ኑዛዜ ማድረጉ በሕግ ውጤት አያመጣም።
- በዜጎች ንብረትና ሕይወት ላይ ውሳኔ የሚሰጡ ሰዎች (ዳኞች) ከወረዳ ጋር በመመሳጠር ክርክር በተነሳበት የመንግስት ቤት ውስጥ መግባት የሕግ ጥሰት ነው። ሕግን ያልተከተለ አካሄድ ነው። በተወሰነ ደረጃ ሙስና ተብሎ ጉዳዩን ወደ ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ብታመለክትበት ዳኛው ከኃላፊነቱ የሚነሳበት ቀጥተኛ ማስረጃ ነው የሚሆነው።
- ክርክር በተነሳበት ጉዳይ ላይ የጥቅም ግንኙነት በመፍጠር እንዲህ ማድረግ ትልቅ የዲሲፒሊን ጥፋት ነው።
- ልጅቷ ቅጹ ላይ አለች፣ ደባል ናት፣ የቤተሰብ አባል ናት ቀጥተኛ ልጅ ባትሆንም፣ የቀበሌ ቤቶች ደግሞ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎቸ ነው የተዘጋጁት፣ ሜዳ ላይ መጣል የለባትም ብሎ የወረዳው አስተዳደር ወስኖ ወይ በዚያው ቤት ሊያስቀጥላት ይገባል የቀበሌ ቤቱ የሚፈርስ ከሆነም ምትክ የመንግስት ቤት እንድታገኝ ሁኔታዎችን ማመቻቸት አለበት።
- በህሊና ፍርድ ወይ አስተዳደራዊ በሆነ መንገድ የወረዳው አስተዳደር መፍትሄ ሊሰጣት ይገባል።
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-08
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል " -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ ዕዳ ያለባቸው 62 ግብር ከፋዮች ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ገልጿል፡፡
እግድ የተጣለባቸው 62 ግለሰቦች በተደጋጋሚ ጥሪ ቢደረግላቸውም ዕዳቸውን ለመክፈል ፈቃደኛ ያልሆኑ ናቸው ተብሏል።
" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል ዕዳቸውን የማይከፍሉ ከሆነም አዋጁ በሰጠን ሥልጣን መሰረትም በቀጣይ የንብረት እግድ እና ንብረታቸውን በሃራጅ የመሸጥ እርምጃዎች ይወሰዳሉ " ሲሉ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቢሮው በታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀፅ 44 ንዑስ አንቀፅ ከ1-3 ለተቋሙ በተሰጠ ስልጣን መሰረት ከሀገር እንዳይወጡ እግድ የተጣለባቸው ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ማስተላለፉን አሳውቋል፡፡
የ62ቱ ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተላከው በትላንትናው ዕለት ነው።
አቶ ሰውነት " በህጉ መሰረት የተቀመጠ ቀነ ገደብ አለ በአዋጁ በተቀመጠው ቀነ ገደብ መሰረት መጥተው እስካልከፈሉ ድረስ ለእዳው ማካካሻ በሚሆን መሰረት ንብረታቸው በሃራጅ ተሽጦ እዳው ይሸፈናል " ብለዋል።
ቢሮው የግብር ዕዳቸውን ሳይወጡ የሚሰወሩ ግብር ከፋዮችን በመከታተል ግዴታቸውን እንዲወጡ ለማስቻል የዕዳ ክትትልና አስተዳደር የስራ ክፍልን በ2017 በጀት ዓመት እንደ አዲስ አዋቅሯል።
በዚህም መሰረት ባለፉት 6 ወራት ከ 6.4 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ እዳ መሰብሰቡን አቶ ሰውነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
Welcome to Mikias Melak & Associates Law Office!
🔹 Facebook: AlehigOfficial
🔹 Telegram Channel: AleHig
🔹 Website: alehig.com
📧 Email: mikiasmelak.mm@gmail.com
📞 Direct Contact:
✅ WhatsApp: +251920666595
✅ Telegram: @MikiasMelak
For legal consultations and inquiries, feel free to reach out. We’ll get back to you as soon as possible!
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ ዕዳ ያለባቸው 62 ግብር ከፋዮች ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ገልጿል፡፡
እግድ የተጣለባቸው 62 ግለሰቦች በተደጋጋሚ ጥሪ ቢደረግላቸውም ዕዳቸውን ለመክፈል ፈቃደኛ ያልሆኑ ናቸው ተብሏል።
" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል ዕዳቸውን የማይከፍሉ ከሆነም አዋጁ በሰጠን ሥልጣን መሰረትም በቀጣይ የንብረት እግድ እና ንብረታቸውን በሃራጅ የመሸጥ እርምጃዎች ይወሰዳሉ " ሲሉ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቢሮው በታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀፅ 44 ንዑስ አንቀፅ ከ1-3 ለተቋሙ በተሰጠ ስልጣን መሰረት ከሀገር እንዳይወጡ እግድ የተጣለባቸው ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ማስተላለፉን አሳውቋል፡፡
የ62ቱ ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተላከው በትላንትናው ዕለት ነው።
አቶ ሰውነት " በህጉ መሰረት የተቀመጠ ቀነ ገደብ አለ በአዋጁ በተቀመጠው ቀነ ገደብ መሰረት መጥተው እስካልከፈሉ ድረስ ለእዳው ማካካሻ በሚሆን መሰረት ንብረታቸው በሃራጅ ተሽጦ እዳው ይሸፈናል " ብለዋል።
ቢሮው የግብር ዕዳቸውን ሳይወጡ የሚሰወሩ ግብር ከፋዮችን በመከታተል ግዴታቸውን እንዲወጡ ለማስቻል የዕዳ ክትትልና አስተዳደር የስራ ክፍልን በ2017 በጀት ዓመት እንደ አዲስ አዋቅሯል።
በዚህም መሰረት ባለፉት 6 ወራት ከ 6.4 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ እዳ መሰብሰቡን አቶ ሰውነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
Welcome to Mikias Melak & Associates Law Office!
🔹 Facebook: AlehigOfficial
🔹 Telegram Channel: AleHig
🔹 Website: alehig.com
📧 Email: mikiasmelak.mm@gmail.com
📞 Direct Contact:
✅ WhatsApp: +251920666595
✅ Telegram: @MikiasMelak
For legal consultations and inquiries, feel free to reach out. We’ll get back to you as soon as possible!
" አስተማሪ ተማሪውን የመምታት መብት የለውም በተማሪዋ ላይ ያደረሰችው ቅጣት ቀላልም ቢሆን እንኳ የአካል ጉዳት በማድረስ በህግ ያስጠይቃታል " - የህግ ባለሙያ
" የቤት ስራ አልሰራሽም " በማለት የሁለተኛ ክፍል ተማሪዋን ተገቢ ያልሆነና አጸያፊ የሆነ ቅጣት የቀጣችው መምህርት ከስራ ታግዳ በህግ ቁጥጥር ስር መደረጓ መገለፁ ይታወሳል።
በመሆኑም መምህርቷ በተማሪዋ ላይ የወሰደችው እርምጃ በህገመንግስቱ አንደት ይታያል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ጠይቋል።
የህግ አማካሪና ጠበቃ ሳሙኤል ግርማ መምህርቷ የወሰደችው እርምጃ " ቀላል የአካል ጉዳት በማድረስ በወንጀል ህጉ 5/ 35 እስከ 3 አመት ፅኑ እስራት ቅጣት " ሊጠብቃት አንደሚችል ተናግረዋል።
የህግ ባለሙያው ምን አሉ ?
" አስተማሪ ተማሪውን የመምታት መብት የለውም በተማሪዋ ላይ ያደረሰችው ቅጣት ቀላልም ቢሆን እንኳ የአካል ጉዳት በማድረስ በህግ ያስጠይቃታል፣ በወንጀል ህጉ ደግሞ 5/ 35 እስከ 3 አመት ያሳስራል፣ ይህ ድርጊት ግን ከዚህም ባለፈ ነው የሚታየው " ብለዋል።
አክለውም " በአስተማሪ የዲስፕሊን መመሪያ በአስተዳደራዊ እርምጃ ከስራዋ ልትሰናበት የሚያስችል ወንጀል ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የህግ ባለሙያው " መምህሯ ቅጣት ያደረሰችባት ተማሪ ከ13 አመት በታች ታዳጊ ከሆነች ይሄ ተገቢ ያልሆነ እና በወንጀል የሚያስጠይቅ ግልፅ የሆነ ጉዳይ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" መምህሯ ተማሪዋን የመታችበት መሳሪያ ወይም ቁስ የቅጣቱን መጠን ይወስነዋል " ያሉ ሲሆን በእንጨት፣ በድንጋይ እና በመሳሰሉት ሆኖ በልጅቷ አካል ላይ መፋፋቅ፣ መድማት የአጥንት መሰበር አይነት ጉዳት ከሆነ ያደረሰችባት ከዚህም ከፍ ያለ ቅጣት ሊጠብቃት እንደሚችል ጠቁመዋል።
በተለይም መምህር፣ ሹፌር እና ሀኪሞች በስራ ያገኟቸውን ሰዎች የበለጠ የመጠበቅ ሃላፊነት አለባቸው። ይሄም እንደ ወንጀል ማክበጃ ይታያል ብለዋል።
የህግ ባለሙያው ሳሙኤል ይሄ ጉዳይ ይፋ መደረጉ እና በመምህርቷ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ለሌሎች አስተማሪዎች መማሪያ የሚሆን ነው ሲሉ ገልጸዋል።
" በመጨረሻም አሁን ላይ ተማሪዎችን አንደድሮው አይነት ቅጣቶች መቅጣት አይቻልም፣ ምክንያቱም ከህፃናት መብት ጋር የሚጣረስ ነው " ሲሉ አመላክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የቤት ስራ አልሰራሽም " በማለት የሁለተኛ ክፍል ተማሪዋን ተገቢ ያልሆነና አጸያፊ የሆነ ቅጣት የቀጣችው መምህርት ከስራ ታግዳ በህግ ቁጥጥር ስር መደረጓ መገለፁ ይታወሳል።
በመሆኑም መምህርቷ በተማሪዋ ላይ የወሰደችው እርምጃ በህገመንግስቱ አንደት ይታያል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ጠይቋል።
የህግ አማካሪና ጠበቃ ሳሙኤል ግርማ መምህርቷ የወሰደችው እርምጃ " ቀላል የአካል ጉዳት በማድረስ በወንጀል ህጉ 5/ 35 እስከ 3 አመት ፅኑ እስራት ቅጣት " ሊጠብቃት አንደሚችል ተናግረዋል።
የህግ ባለሙያው ምን አሉ ?
" አስተማሪ ተማሪውን የመምታት መብት የለውም በተማሪዋ ላይ ያደረሰችው ቅጣት ቀላልም ቢሆን እንኳ የአካል ጉዳት በማድረስ በህግ ያስጠይቃታል፣ በወንጀል ህጉ ደግሞ 5/ 35 እስከ 3 አመት ያሳስራል፣ ይህ ድርጊት ግን ከዚህም ባለፈ ነው የሚታየው " ብለዋል።
አክለውም " በአስተማሪ የዲስፕሊን መመሪያ በአስተዳደራዊ እርምጃ ከስራዋ ልትሰናበት የሚያስችል ወንጀል ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የህግ ባለሙያው " መምህሯ ቅጣት ያደረሰችባት ተማሪ ከ13 አመት በታች ታዳጊ ከሆነች ይሄ ተገቢ ያልሆነ እና በወንጀል የሚያስጠይቅ ግልፅ የሆነ ጉዳይ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" መምህሯ ተማሪዋን የመታችበት መሳሪያ ወይም ቁስ የቅጣቱን መጠን ይወስነዋል " ያሉ ሲሆን በእንጨት፣ በድንጋይ እና በመሳሰሉት ሆኖ በልጅቷ አካል ላይ መፋፋቅ፣ መድማት የአጥንት መሰበር አይነት ጉዳት ከሆነ ያደረሰችባት ከዚህም ከፍ ያለ ቅጣት ሊጠብቃት እንደሚችል ጠቁመዋል።
በተለይም መምህር፣ ሹፌር እና ሀኪሞች በስራ ያገኟቸውን ሰዎች የበለጠ የመጠበቅ ሃላፊነት አለባቸው። ይሄም እንደ ወንጀል ማክበጃ ይታያል ብለዋል።
የህግ ባለሙያው ሳሙኤል ይሄ ጉዳይ ይፋ መደረጉ እና በመምህርቷ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ለሌሎች አስተማሪዎች መማሪያ የሚሆን ነው ሲሉ ገልጸዋል።
" በመጨረሻም አሁን ላይ ተማሪዎችን አንደድሮው አይነት ቅጣቶች መቅጣት አይቻልም፣ ምክንያቱም ከህፃናት መብት ጋር የሚጣረስ ነው " ሲሉ አመላክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ በህግ የሚገደዱ ግብር ከፋዮች ከመጪው ሀምሌ የግብር ማሳወቂያ ወር ጀምሮ የተሟላ የሂሳብ መዝገብ በመያዝ ካልመጡ በስተቀር አይስተናገዱም "- የገቢዎች ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከመጪው ዓመታዊ የግብር ማሳወቂያ ወር ጀምሮ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋይ ሆነው በህግ የሚገደዱ ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ የማይስተናገዱ መሆኑን አሳውቋል።
አይስተናገዱም የተባሉት በደረጃ "ሀ" እና "ለ" የግብር ከፋይነት የተመዝገቡ እና በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱትን ብቻ ነው።
የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱ ነጋዴዎች ከሚቀጥለው በጀት አመት በኋላ ግብር ለመክፈል ያላቸውን አጠቃላይ ወጪ እና ገቢያቸውን በዝርዝር የሚያሳይ መዝገብ መያዝ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
አቶ ሰውነት አየለ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የሂሳብ መዝገብ ማለት ያላቸውን አጠቃላይ ሽያጭ እና ወጪ በዝርዝር የሚያሳይ ሰነድ/መዝገብ ነው።
ህጋዊ የሆነ ግብይት የሚፈጸም ከሆነ እና በደረሰኝ ላይ የተመሰረተ ግብይት ካለ ከዚህ መዝገብ ጋር ተያይዞ ነው የሚቀርበው።
ይህ ህግ ከወጣ ረጅም ጊዜ ነው ነገር ግን አፈጻጸም ላይ የተለያዩ ክፍተቶች በመኖራቸው በቁርጥ ግብር የሚስተናገዱ ነበሩ።
ለእነዚህ ግብር ከፋዮች በተለያየ መንገድ መረጃዎችን እያደረስን ነው ያለነው ከሚቀጥለው በጀት አመት በኋላ ከዚህ ሂሳብ መዝገብ ውጪ እንደማናስተናግዳቸው እንዲያውቁ እያደረግን ነው።
ግብይቶቻቸውን በደረሰኝ ላይ ተመስርተው ፈጽመው በሂሳብ ባለሙያ አልያም የድርጅታቸው ተቀጣሪ በሆነ የሂሳብ ባለሙያ የተዘጋጀ የሂሳብ መዝገብ ማቅረብ አለባቸው።
ግብር ከፋዮች ከግምት የጸዳ የግብር አሰባሰብ ስርዓት የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱ ለማስቻል ይህንን የማሳወቅ ስራ እየሰራን ነው።
በደረጃ "ሀ" እና "ለ" ከ120 ሺ በላይ ግብር ከፋዮች አሉ ከእነዚህ ውስጥ ገቢ እና ወጪያቸውን በአግባቡ እየመዘገቡ ፣ደረሰኝ እየቆረጡ አመታዊ ግብራቸውን የሚያሳውቁ አሉ ነገር ግን ከዚህ ውጪ ሲስተናገዱ የቆዩ ግብር ከፋዮቾም ነበሩ።
ይህ አሰራር ተለምዶ ከአመት አመት ዝም ብሎ በቁርጥ ግብር ለመስተናገድ የመፈለግ አዝማሚያ ይታያል ህጉ ግን ይህንን አሰራር የማይፈቅድ በመሆኑ ከመጪው ሐምሌ ወር ጀምሮ ሲመጡ በተሟላ መንገድ ሂሳብ መዝገባቸውን ይዘው ካልመጡ በስተቀር አይስተናገዱም።
መያዝ አለባቸው እያልን ያለነው በደረጃ "ሀ" እና "ለ" የግብር ከፋይ ተመዝግበው በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱትን ብቻ ነው።
ሁሉንም ማለት አይደለም በተሰማሩበት የንግድ ዘርፋቸው ምክንያት እዚህ ውስጥ የማይካተቱ ይኖራሉ የሚመለከተው የተሰማሩበት የስራ ዘርፍ የሂሳብ መዝገብ መያዝ እያስገደዳቸው በተለያየ ምክንያት የማይዙትን እና በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ የነበሩ የንግዱን ማህበረሰብ ነው።
ይህ አይነቱ አሰራር ግብር በዛብኝ በማለት ለሚቀርቡ ቅሬታዎች መፍትሄ የሚሆን ነው " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከመጪው ዓመታዊ የግብር ማሳወቂያ ወር ጀምሮ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋይ ሆነው በህግ የሚገደዱ ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ የማይስተናገዱ መሆኑን አሳውቋል።
አይስተናገዱም የተባሉት በደረጃ "ሀ" እና "ለ" የግብር ከፋይነት የተመዝገቡ እና በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱትን ብቻ ነው።
የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱ ነጋዴዎች ከሚቀጥለው በጀት አመት በኋላ ግብር ለመክፈል ያላቸውን አጠቃላይ ወጪ እና ገቢያቸውን በዝርዝር የሚያሳይ መዝገብ መያዝ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
አቶ ሰውነት አየለ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የሂሳብ መዝገብ ማለት ያላቸውን አጠቃላይ ሽያጭ እና ወጪ በዝርዝር የሚያሳይ ሰነድ/መዝገብ ነው።
ህጋዊ የሆነ ግብይት የሚፈጸም ከሆነ እና በደረሰኝ ላይ የተመሰረተ ግብይት ካለ ከዚህ መዝገብ ጋር ተያይዞ ነው የሚቀርበው።
ይህ ህግ ከወጣ ረጅም ጊዜ ነው ነገር ግን አፈጻጸም ላይ የተለያዩ ክፍተቶች በመኖራቸው በቁርጥ ግብር የሚስተናገዱ ነበሩ።
ለእነዚህ ግብር ከፋዮች በተለያየ መንገድ መረጃዎችን እያደረስን ነው ያለነው ከሚቀጥለው በጀት አመት በኋላ ከዚህ ሂሳብ መዝገብ ውጪ እንደማናስተናግዳቸው እንዲያውቁ እያደረግን ነው።
ግብይቶቻቸውን በደረሰኝ ላይ ተመስርተው ፈጽመው በሂሳብ ባለሙያ አልያም የድርጅታቸው ተቀጣሪ በሆነ የሂሳብ ባለሙያ የተዘጋጀ የሂሳብ መዝገብ ማቅረብ አለባቸው።
ግብር ከፋዮች ከግምት የጸዳ የግብር አሰባሰብ ስርዓት የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱ ለማስቻል ይህንን የማሳወቅ ስራ እየሰራን ነው።
በደረጃ "ሀ" እና "ለ" ከ120 ሺ በላይ ግብር ከፋዮች አሉ ከእነዚህ ውስጥ ገቢ እና ወጪያቸውን በአግባቡ እየመዘገቡ ፣ደረሰኝ እየቆረጡ አመታዊ ግብራቸውን የሚያሳውቁ አሉ ነገር ግን ከዚህ ውጪ ሲስተናገዱ የቆዩ ግብር ከፋዮቾም ነበሩ።
ይህ አሰራር ተለምዶ ከአመት አመት ዝም ብሎ በቁርጥ ግብር ለመስተናገድ የመፈለግ አዝማሚያ ይታያል ህጉ ግን ይህንን አሰራር የማይፈቅድ በመሆኑ ከመጪው ሐምሌ ወር ጀምሮ ሲመጡ በተሟላ መንገድ ሂሳብ መዝገባቸውን ይዘው ካልመጡ በስተቀር አይስተናገዱም።
መያዝ አለባቸው እያልን ያለነው በደረጃ "ሀ" እና "ለ" የግብር ከፋይ ተመዝግበው በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱትን ብቻ ነው።
ሁሉንም ማለት አይደለም በተሰማሩበት የንግድ ዘርፋቸው ምክንያት እዚህ ውስጥ የማይካተቱ ይኖራሉ የሚመለከተው የተሰማሩበት የስራ ዘርፍ የሂሳብ መዝገብ መያዝ እያስገደዳቸው በተለያየ ምክንያት የማይዙትን እና በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ የነበሩ የንግዱን ማህበረሰብ ነው።
ይህ አይነቱ አሰራር ግብር በዛብኝ በማለት ለሚቀርቡ ቅሬታዎች መፍትሄ የሚሆን ነው " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia