#AddisAbaba #ንግድ
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ማህበረሰብ ያለወከባ በተረጋጋ መንፈስ የንግድ ተግባሩን ለማከናወን እንዲያስችል ዕድል ይፈጥርለታል የተባለ አዲስ መመሪያ ስራ ላይ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።
አዲሱ መመሪያ " በመንደር ንግድ ቁጥጥር አሰራር ስርዓት መመሪያ 159/2016 " እንደሚባል ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
መመሪያው በየትኛው አስተዳደር እርከን የትኛው አይነት እርምጃ እንደሚወሰድ በግልጽ ያስቀመጠ ሲሆን ይህም ሲታይ የነበረውን ግልጽ እና ፍትሃዊ ያልሆነ አሰራር ያስቀራል ተብሏል።
በአዲሱ የመንደር ንግድ መመሪያ መሰረት የወረዳ የንግድ ቁጥጥር ባለሙያ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ ህጉ የሚፈቅድለት በተመደበበት መንደር ላይ ፦
➡ ያለ ንግድ ፍቃድ
➡ ባልታደሰ ፍቃድ
➡ በታገደ አልያም በተሰረዘ ንግድ ፈቃድ የሚነግድ የንግድ ድርጅት ላይ #ብቻ_ነው። ይህን ሲያደርግም ለቅርብ ኃላፊ ማሳወቅ አለበት።
ከዚህ ወጪ ያሉት ጥፋቶች #በሙሉ እርምጃ ሳይወስድ ለቅርብ ኃላፊው በፅሁፍ በማሳወቅ ለውሳኔ ወደ ንግድ ቢሮ መላክ ይጠበቅበታል ፤ የተወሰነውን ውሳኔ የማስፈፀም ኃላፊነትም አለበት።
መመሪያው ፦ https://t.me/tikvahethiopia/87886
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
አማራጭ የሕግ እውቀት
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/
👉 LinkedIn 👈
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/
👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ማህበረሰብ ያለወከባ በተረጋጋ መንፈስ የንግድ ተግባሩን ለማከናወን እንዲያስችል ዕድል ይፈጥርለታል የተባለ አዲስ መመሪያ ስራ ላይ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።
አዲሱ መመሪያ " በመንደር ንግድ ቁጥጥር አሰራር ስርዓት መመሪያ 159/2016 " እንደሚባል ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
መመሪያው በየትኛው አስተዳደር እርከን የትኛው አይነት እርምጃ እንደሚወሰድ በግልጽ ያስቀመጠ ሲሆን ይህም ሲታይ የነበረውን ግልጽ እና ፍትሃዊ ያልሆነ አሰራር ያስቀራል ተብሏል።
በአዲሱ የመንደር ንግድ መመሪያ መሰረት የወረዳ የንግድ ቁጥጥር ባለሙያ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ ህጉ የሚፈቅድለት በተመደበበት መንደር ላይ ፦
➡ ያለ ንግድ ፍቃድ
➡ ባልታደሰ ፍቃድ
➡ በታገደ አልያም በተሰረዘ ንግድ ፈቃድ የሚነግድ የንግድ ድርጅት ላይ #ብቻ_ነው። ይህን ሲያደርግም ለቅርብ ኃላፊ ማሳወቅ አለበት።
ከዚህ ወጪ ያሉት ጥፋቶች #በሙሉ እርምጃ ሳይወስድ ለቅርብ ኃላፊው በፅሁፍ በማሳወቅ ለውሳኔ ወደ ንግድ ቢሮ መላክ ይጠበቅበታል ፤ የተወሰነውን ውሳኔ የማስፈፀም ኃላፊነትም አለበት።
መመሪያው ፦ https://t.me/tikvahethiopia/87886
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
አማራጭ የሕግ እውቀት
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/
👉 LinkedIn 👈
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/
👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
#ጉምሩክ
🔴 “ በኢንቮይስም ከፍለን እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ አሉን ” - አስመጪዎች
⚫️ “ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም” - ኮሚሽኑ
ጉምሩክ ኮሚሽን ከማክሮ ኢኮኖሚ ፓሊሲ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ባወጣው አዲስ መመሪያ "ከእጥፍ በላይቀረጥ ክፈሉ'' እየተባሉ መሆኑን አስመጪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ኮሚሽኑም ከቅሬታው በኋላ ማሻሻያ ማድረጉን መረጃ ነግረናችሁ ነበር።
ሆኖም ከ150 በላይ የሚሆኑ “ በኢነቮይስ ከፍለናል ” የሚሉ አስመጪዎች፣ ኮሚሽኑ ከማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ትግበራወሰ በኋላ ያወረደውና በአስመጪዎች በኩል “ አዋጅን በደብዳቤ ሽሯል ” በሚል ቅሬታ ቀርቦበት ኮሚሽኑ በድጋሚ ማሻሻያ አደረኩበት ያለው ደብዳቤም ቅሬታቸውን እንዳልፈታላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
በዚህም እንዲያወያያቸው ጭምር ኮሚሽኑን በደብዳቤ እንደጠቁ ሆኖም ምላሽ እንዳልጠሰጣቸው ገልጸው፤ ጉዳዩን በድጋሚ እንዲያጤነው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።
አስመጪዎች በዝርዝር ያቀረቡት ቅሬታ ምንድን ነው ?
“ ደብዳቤው (ማስተካከያ የተደረገበት) መልስ ስላልሰጠን መልሰን ደብዳቤ ፃፍንላቸው፡፡ ምክንያቱም ከማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ በፊት የገቡ እቃዎች እንዲስተካከሉ ተብሎ ብዙዎቹም አውጥተዋል፡፡
የእኛ ጥያቄ፤ ቅድሚያ እቃው ዶኩሜንት እንደደረሰን ጂቡቲ ላይ እንዳለ በኢንቮይስ ዲክላራሲዮን ይቆረጣል። ጂቡቲ ጭነት ሊዘገይ ስለሚችል ፤ በየሳምንቱ ደግሞ ሬት ስለሚቀይር ያንን ነገር እንዳይነካው ሁሉም ነጋዴ ከዚህ በፊት ለዓመታት የሰራው በዚህ አይነት አካሄድ ነው፡፡
እቃው ጂቡቲ እያለ ዶኩሜንቱ ከመጣ በኢንቮይስ ይከፈላል። ቀሪ ሂሳብ ደግሞ ከፍተሻ በኋላ 'ይለቀቅ' ሲባል ያኔ ተከፍሎ ይመጣል፡፡ አሁን ግን በኢንቮይስም ከፍለን 'እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ' አሉን፡፡
እኛ ደግሞ አልተስማማንም፡፡ ጉምሩክ በገባበት ሳይሆን ዶኩሜንት ባስገባንበት፤ ዲክራላሲዮን ባስቆረጥንበት ነው መስተናገድ ያለብን፡፡ 5 ሚሊዮን ስንከፍል የነበርነው 10 ሚሊዮን፣ 10 ሚሊዮን ይከፍል የነበረ 20 ሚሊዮን ብር ከፈሉ እየተባልን ነው፡፡
አሁን ጠዋት አንድ ሬት ከሰዓት ሌላ ሬት አለው ጉምሩክ፤ ድሮ ግን በየሳምንቱ አንድ ሬት ነበረው፡፡ ሐሙስ ቀን የሚቀየር ሬት ብቻ ነበር የሚሰጡት፡፡
ይህ ደግሞ ኪሳራና ተጠቃሚውም ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚጣመጣበት ጉምሩክም ይገነዘባል፡፡ ይህን ነገር ቢያስተካካል ባለው ዋጋ መሸጥ ይቻላል ” ነው ያሉት፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቀረበው ቅሬታ የኮሚሽኑ ምላሽ ምንድን ነው ? ኮሚሽኑ ባለፈው አደረኩት ባለው ማሻሻያ የአሁኖቹ ቅሬታ አቅራቢዎችን ጉዳይ አካቶ ምላሽ ሰጥቷል? ከሆነ እንዴት ? ሲል ጉምሩክ ኮሚሽኑንን ጠይቋል።
የኮሚሽን ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።
“ ኮሚሽኑ የተለዬ ምላሽ የለውም ከዚያ ጉዳይ ጋር በተያያዘ። የተሰጠው ምላሽ ሁሉንም ጉዳዮች ከቨር ያደረገ ስለሆነ ቀደም ሲል በወጣ ደብዳቤ ምላሽ የተሰጠበት ጉዳይ ነው፡፡
የተለዬ ኮሚሽኑ የሚያየው ጉዳይ የሌለ መሆኑን ነው የማውቀው። ሁሉም ጉዳዮች እዛ ላይ ቴኪኒካሊ ከጉምሩክ አዋጅ አንጻር ታይተው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
አጠቃላይ ነው ባለፈውም አቤቱታ የቀረበው፡፡ ስለዚህ ምላሽ የተሰጠበት አግባብ አለ፡፡ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም፤ ይታወቃል።
'መስተናገድ የለብን በዚህ የሚል ጉዳይ' ካለ ኮሚሽኑ የሰጠውን ምላሽ መቃወም መብት ነው። ተራ ቁጥር 1፣ 2፣ 3፣ 4 በሚሉ ተራ ቁጥሮች ላይ ተገልጿል፡፡
የተቀመጡት ኮንዲሽኖች ጂቡቲ ላሉት እቃዎች፣ አገር ውስጥ ላልገባ እቃ በነባሩ የውጭ ምንዛሪ እንስተናገድ ነው ጥያቄያቸው። ያነም ኮሚሽኑ ደብዳቤው ላይ በገለጸው ልክ (ተራቁጥር አራት ይመስለኛል) በግለጽ የተቀመጠ ጉዳይ ነው።
እነርሱ አቤቱታቸውን መቀጠል ይችላሉ፤ ኮሚሽኑ እኮ ከዚህ አንጻር የከለከለው ነገር የለም፡፡ ስለዚህ የተሰተው ምላሽ ይሄው ነው ከዚያ ውጪ የተለየ የሚሰጥ ምላሽ የለንም በዚያ ደብዳቤ ተመልሶ ያለፈ ጉዳይ ስለሆነ” ብለዋል።
#TikvahethiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ በኢንቮይስም ከፍለን እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ አሉን ” - አስመጪዎች
⚫️ “ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም” - ኮሚሽኑ
ጉምሩክ ኮሚሽን ከማክሮ ኢኮኖሚ ፓሊሲ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ባወጣው አዲስ መመሪያ "ከእጥፍ በላይቀረጥ ክፈሉ'' እየተባሉ መሆኑን አስመጪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ኮሚሽኑም ከቅሬታው በኋላ ማሻሻያ ማድረጉን መረጃ ነግረናችሁ ነበር።
ሆኖም ከ150 በላይ የሚሆኑ “ በኢነቮይስ ከፍለናል ” የሚሉ አስመጪዎች፣ ኮሚሽኑ ከማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ትግበራወሰ በኋላ ያወረደውና በአስመጪዎች በኩል “ አዋጅን በደብዳቤ ሽሯል ” በሚል ቅሬታ ቀርቦበት ኮሚሽኑ በድጋሚ ማሻሻያ አደረኩበት ያለው ደብዳቤም ቅሬታቸውን እንዳልፈታላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
በዚህም እንዲያወያያቸው ጭምር ኮሚሽኑን በደብዳቤ እንደጠቁ ሆኖም ምላሽ እንዳልጠሰጣቸው ገልጸው፤ ጉዳዩን በድጋሚ እንዲያጤነው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።
አስመጪዎች በዝርዝር ያቀረቡት ቅሬታ ምንድን ነው ?
“ ደብዳቤው (ማስተካከያ የተደረገበት) መልስ ስላልሰጠን መልሰን ደብዳቤ ፃፍንላቸው፡፡ ምክንያቱም ከማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ በፊት የገቡ እቃዎች እንዲስተካከሉ ተብሎ ብዙዎቹም አውጥተዋል፡፡
የእኛ ጥያቄ፤ ቅድሚያ እቃው ዶኩሜንት እንደደረሰን ጂቡቲ ላይ እንዳለ በኢንቮይስ ዲክላራሲዮን ይቆረጣል። ጂቡቲ ጭነት ሊዘገይ ስለሚችል ፤ በየሳምንቱ ደግሞ ሬት ስለሚቀይር ያንን ነገር እንዳይነካው ሁሉም ነጋዴ ከዚህ በፊት ለዓመታት የሰራው በዚህ አይነት አካሄድ ነው፡፡
እቃው ጂቡቲ እያለ ዶኩሜንቱ ከመጣ በኢንቮይስ ይከፈላል። ቀሪ ሂሳብ ደግሞ ከፍተሻ በኋላ 'ይለቀቅ' ሲባል ያኔ ተከፍሎ ይመጣል፡፡ አሁን ግን በኢንቮይስም ከፍለን 'እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ' አሉን፡፡
እኛ ደግሞ አልተስማማንም፡፡ ጉምሩክ በገባበት ሳይሆን ዶኩሜንት ባስገባንበት፤ ዲክራላሲዮን ባስቆረጥንበት ነው መስተናገድ ያለብን፡፡ 5 ሚሊዮን ስንከፍል የነበርነው 10 ሚሊዮን፣ 10 ሚሊዮን ይከፍል የነበረ 20 ሚሊዮን ብር ከፈሉ እየተባልን ነው፡፡
አሁን ጠዋት አንድ ሬት ከሰዓት ሌላ ሬት አለው ጉምሩክ፤ ድሮ ግን በየሳምንቱ አንድ ሬት ነበረው፡፡ ሐሙስ ቀን የሚቀየር ሬት ብቻ ነበር የሚሰጡት፡፡
ይህ ደግሞ ኪሳራና ተጠቃሚውም ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚጣመጣበት ጉምሩክም ይገነዘባል፡፡ ይህን ነገር ቢያስተካካል ባለው ዋጋ መሸጥ ይቻላል ” ነው ያሉት፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቀረበው ቅሬታ የኮሚሽኑ ምላሽ ምንድን ነው ? ኮሚሽኑ ባለፈው አደረኩት ባለው ማሻሻያ የአሁኖቹ ቅሬታ አቅራቢዎችን ጉዳይ አካቶ ምላሽ ሰጥቷል? ከሆነ እንዴት ? ሲል ጉምሩክ ኮሚሽኑንን ጠይቋል።
የኮሚሽን ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።
“ ኮሚሽኑ የተለዬ ምላሽ የለውም ከዚያ ጉዳይ ጋር በተያያዘ። የተሰጠው ምላሽ ሁሉንም ጉዳዮች ከቨር ያደረገ ስለሆነ ቀደም ሲል በወጣ ደብዳቤ ምላሽ የተሰጠበት ጉዳይ ነው፡፡
የተለዬ ኮሚሽኑ የሚያየው ጉዳይ የሌለ መሆኑን ነው የማውቀው። ሁሉም ጉዳዮች እዛ ላይ ቴኪኒካሊ ከጉምሩክ አዋጅ አንጻር ታይተው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
አጠቃላይ ነው ባለፈውም አቤቱታ የቀረበው፡፡ ስለዚህ ምላሽ የተሰጠበት አግባብ አለ፡፡ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም፤ ይታወቃል።
'መስተናገድ የለብን በዚህ የሚል ጉዳይ' ካለ ኮሚሽኑ የሰጠውን ምላሽ መቃወም መብት ነው። ተራ ቁጥር 1፣ 2፣ 3፣ 4 በሚሉ ተራ ቁጥሮች ላይ ተገልጿል፡፡
የተቀመጡት ኮንዲሽኖች ጂቡቲ ላሉት እቃዎች፣ አገር ውስጥ ላልገባ እቃ በነባሩ የውጭ ምንዛሪ እንስተናገድ ነው ጥያቄያቸው። ያነም ኮሚሽኑ ደብዳቤው ላይ በገለጸው ልክ (ተራቁጥር አራት ይመስለኛል) በግለጽ የተቀመጠ ጉዳይ ነው።
እነርሱ አቤቱታቸውን መቀጠል ይችላሉ፤ ኮሚሽኑ እኮ ከዚህ አንጻር የከለከለው ነገር የለም፡፡ ስለዚህ የተሰተው ምላሽ ይሄው ነው ከዚያ ውጪ የተለየ የሚሰጥ ምላሽ የለንም በዚያ ደብዳቤ ተመልሶ ያለፈ ጉዳይ ስለሆነ” ብለዋል።
#TikvahethiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔈 #የዜጎችድምጽ
" ወረዳው ከነእቃዬ ሜዳ ላይ ጥሎኝ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " - እንባ የሚተናነቃት ወጣት
በአዲስ አበባ አስተዳደር የካ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ቀበሌ 9/10 የምትገኝ ወጣት ከአሳዳጊ አክስቷ ጋር ትኖርበት ከነበረው የቀበሌ ቤት አሳዳጊዋ ስትሞት ከቤቱ እንድትወጣ ተደርጋ ጎዳና እንደወጣች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል እሮሮ አሰምታለች።
" ወረዳው ከነእቃዬን ሜዳ ጥሎ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " ብላለች።
ወርቅነሽ አለሙ የምትባለው ይህች ወጣት የአባቷ ታላቅ እህት ከ3 ዓመቷ ጀምሮ ከባህር ዳር ወደ አ/አ አምጥታት ነው ያሳደገቻት።
እዚሁ ቤት እስከ 2016 ዓ/ም ማለቂያ ድረስ ነበሩ።
በ2016 ዓ/ም አሳዳጊ አክስቷ ከሞትች ከ40 ቀናት በኃላ ወረዳው " ወራሽ ልጅ ስላልሆሽ ልቀቂ " ይላታል።
ጉዳዩን ይዛ ፍርድ ቤት ሄደች። ፍርድ ቤትም ሄዳ መፍትሄ አልተሰጣትም።
" ወረዳ እኔን ጠዋት በግብረ ኃይል ከነእቃዬ አውጥቶ ጥሎኝ ከሰዓት በኋላ ራሱ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ቤቴ ውስጥ አስገባው " ስትል ቅሬታ አሰምታለች።
ከዚህ አለፍ ሲል ቤቱ ሁለት ክፍል ሆኖ ሳለ ወደ አራት ክፍል አስፋፍቶ ሰርቶት ዞር ብሎ የጠየቀው አካል የለም ብላለች።
ወረዳው ምን ምላሽ ሰጠ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታውን ይዞ የወረዳ 6 ጽ/ቤት አስተዳደር ኃላፊ አቶ ምስጋናው ሂጂቱን አነጋግሯል።
ቅሬታዋ አቅራቢዋ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብት እንዳላት አምነውበታል።
ኃላፊው ፤ " ባለመብት ናት የቀበሌ ቤት መውረስ የሚችለው ልጅ ነውና ልጅ ከሆነች መውረስ መብቷ ነው " ብለዋል።
" በሕጉ መሠረት የቀበሌ ቤት ፣ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብቷ የተጠበቀ ነው ፤ በዚያ ደረጃ ሆኖ ከነበረ እኔ ጋ ይምጡ እናስተካክላለን ይሄ የተነሳው ጉዳይ ትክክል ከሆነ " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ ጉዳይ ተጨማሪ ማብራሪያ እና ግልጽነት ስለሚፈልግ የሕግ ባለሙያ አነጋግሯል።
የሕግ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ምን አሉ ?
- ኑዛዜውን ማጽደቅ ትችላለች። ግን የቀበሌ ቤት ላይ ተወላጆች ካልሆኑ በስተቀር ከሕግ አንጻር በባዮሎጂካል ተወላጅ ያልሆነ ልጅ የጉጂፈቻ ማስረጃ ቀደም ሲል ሊኖር ይገባል።
- ለቀበሌ ቤት የጉዲፈቻ ማስረጃ ስሌላት ውርስ ተቀባዩዋን ከሞራልና ከአስተዳደራዊ አንጻር ካልሆነ በስተቀር ከሕግ አንጻር የወረዳው አስተደዳደር ሊያስተናግዳት አይችልም።
- ከሞራል አንጻር አሳዳጊዋ ስላረፉ፣ ልጅቷ ደግሞ ተተኪ ልጅ ናት፤ በሥነ ልቦና እናትና ልጅ ሆነው አብረው ኖረዋል። የቀበሌ ቤት የሚባለው ደግሞ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች የሚኖበት ነው። ስለዚህ ከሕግ አንጻር የኑዛዜ ተቀባይ መሆን ባትችልም አንዱ ወጥቶ ሌላው የሚገባበት፣ ለዜጎች የተሰራ ቤት በመሆኑ ልትኖርበት ይገባ ነበር ከሞራል አንጻር።
- ከሕግ አንጻር በቀበሌ ቤት ላይ ኑዛዜ ማድረግ አይቻልም።
- ለምሳሌ የፌደራል ኪራይ ቤቶችን አንድ ሰው ተከራይቶ ቢኖር ሲሞት ሊናዘዝበት አይችልም። ምክንያቱም የንብረቱ ባለቤት መንግስት ነው። በመሳሳይ ሁኔታ የቀበሌ ቤቶች ውስጥ የሚኖር ሰው ሲሞት ኑዛዜ ሊያደርግ አይችልም። ኑዛዜ ማድረጉ በሕግ ውጤት አያመጣም።
- በዜጎች ንብረትና ሕይወት ላይ ውሳኔ የሚሰጡ ሰዎች (ዳኞች) ከወረዳ ጋር በመመሳጠር ክርክር በተነሳበት የመንግስት ቤት ውስጥ መግባት የሕግ ጥሰት ነው። ሕግን ያልተከተለ አካሄድ ነው። በተወሰነ ደረጃ ሙስና ተብሎ ጉዳዩን ወደ ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ብታመለክትበት ዳኛው ከኃላፊነቱ የሚነሳበት ቀጥተኛ ማስረጃ ነው የሚሆነው።
- ክርክር በተነሳበት ጉዳይ ላይ የጥቅም ግንኙነት በመፍጠር እንዲህ ማድረግ ትልቅ የዲሲፒሊን ጥፋት ነው።
- ልጅቷ ቅጹ ላይ አለች፣ ደባል ናት፣ የቤተሰብ አባል ናት ቀጥተኛ ልጅ ባትሆንም፣ የቀበሌ ቤቶች ደግሞ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎቸ ነው የተዘጋጁት፣ ሜዳ ላይ መጣል የለባትም ብሎ የወረዳው አስተዳደር ወስኖ ወይ በዚያው ቤት ሊያስቀጥላት ይገባል የቀበሌ ቤቱ የሚፈርስ ከሆነም ምትክ የመንግስት ቤት እንድታገኝ ሁኔታዎችን ማመቻቸት አለበት።
- በህሊና ፍርድ ወይ አስተዳደራዊ በሆነ መንገድ የወረዳው አስተዳደር መፍትሄ ሊሰጣት ይገባል።
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-08
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ወረዳው ከነእቃዬ ሜዳ ላይ ጥሎኝ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " - እንባ የሚተናነቃት ወጣት
በአዲስ አበባ አስተዳደር የካ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ቀበሌ 9/10 የምትገኝ ወጣት ከአሳዳጊ አክስቷ ጋር ትኖርበት ከነበረው የቀበሌ ቤት አሳዳጊዋ ስትሞት ከቤቱ እንድትወጣ ተደርጋ ጎዳና እንደወጣች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል እሮሮ አሰምታለች።
" ወረዳው ከነእቃዬን ሜዳ ጥሎ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " ብላለች።
ወርቅነሽ አለሙ የምትባለው ይህች ወጣት የአባቷ ታላቅ እህት ከ3 ዓመቷ ጀምሮ ከባህር ዳር ወደ አ/አ አምጥታት ነው ያሳደገቻት።
እዚሁ ቤት እስከ 2016 ዓ/ም ማለቂያ ድረስ ነበሩ።
በ2016 ዓ/ም አሳዳጊ አክስቷ ከሞትች ከ40 ቀናት በኃላ ወረዳው " ወራሽ ልጅ ስላልሆሽ ልቀቂ " ይላታል።
ጉዳዩን ይዛ ፍርድ ቤት ሄደች። ፍርድ ቤትም ሄዳ መፍትሄ አልተሰጣትም።
" ወረዳ እኔን ጠዋት በግብረ ኃይል ከነእቃዬ አውጥቶ ጥሎኝ ከሰዓት በኋላ ራሱ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ቤቴ ውስጥ አስገባው " ስትል ቅሬታ አሰምታለች።
ከዚህ አለፍ ሲል ቤቱ ሁለት ክፍል ሆኖ ሳለ ወደ አራት ክፍል አስፋፍቶ ሰርቶት ዞር ብሎ የጠየቀው አካል የለም ብላለች።
ወረዳው ምን ምላሽ ሰጠ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታውን ይዞ የወረዳ 6 ጽ/ቤት አስተዳደር ኃላፊ አቶ ምስጋናው ሂጂቱን አነጋግሯል።
ቅሬታዋ አቅራቢዋ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብት እንዳላት አምነውበታል።
ኃላፊው ፤ " ባለመብት ናት የቀበሌ ቤት መውረስ የሚችለው ልጅ ነውና ልጅ ከሆነች መውረስ መብቷ ነው " ብለዋል።
" በሕጉ መሠረት የቀበሌ ቤት ፣ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብቷ የተጠበቀ ነው ፤ በዚያ ደረጃ ሆኖ ከነበረ እኔ ጋ ይምጡ እናስተካክላለን ይሄ የተነሳው ጉዳይ ትክክል ከሆነ " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ ጉዳይ ተጨማሪ ማብራሪያ እና ግልጽነት ስለሚፈልግ የሕግ ባለሙያ አነጋግሯል።
የሕግ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ምን አሉ ?
- ኑዛዜውን ማጽደቅ ትችላለች። ግን የቀበሌ ቤት ላይ ተወላጆች ካልሆኑ በስተቀር ከሕግ አንጻር በባዮሎጂካል ተወላጅ ያልሆነ ልጅ የጉጂፈቻ ማስረጃ ቀደም ሲል ሊኖር ይገባል።
- ለቀበሌ ቤት የጉዲፈቻ ማስረጃ ስሌላት ውርስ ተቀባዩዋን ከሞራልና ከአስተዳደራዊ አንጻር ካልሆነ በስተቀር ከሕግ አንጻር የወረዳው አስተደዳደር ሊያስተናግዳት አይችልም።
- ከሞራል አንጻር አሳዳጊዋ ስላረፉ፣ ልጅቷ ደግሞ ተተኪ ልጅ ናት፤ በሥነ ልቦና እናትና ልጅ ሆነው አብረው ኖረዋል። የቀበሌ ቤት የሚባለው ደግሞ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች የሚኖበት ነው። ስለዚህ ከሕግ አንጻር የኑዛዜ ተቀባይ መሆን ባትችልም አንዱ ወጥቶ ሌላው የሚገባበት፣ ለዜጎች የተሰራ ቤት በመሆኑ ልትኖርበት ይገባ ነበር ከሞራል አንጻር።
- ከሕግ አንጻር በቀበሌ ቤት ላይ ኑዛዜ ማድረግ አይቻልም።
- ለምሳሌ የፌደራል ኪራይ ቤቶችን አንድ ሰው ተከራይቶ ቢኖር ሲሞት ሊናዘዝበት አይችልም። ምክንያቱም የንብረቱ ባለቤት መንግስት ነው። በመሳሳይ ሁኔታ የቀበሌ ቤቶች ውስጥ የሚኖር ሰው ሲሞት ኑዛዜ ሊያደርግ አይችልም። ኑዛዜ ማድረጉ በሕግ ውጤት አያመጣም።
- በዜጎች ንብረትና ሕይወት ላይ ውሳኔ የሚሰጡ ሰዎች (ዳኞች) ከወረዳ ጋር በመመሳጠር ክርክር በተነሳበት የመንግስት ቤት ውስጥ መግባት የሕግ ጥሰት ነው። ሕግን ያልተከተለ አካሄድ ነው። በተወሰነ ደረጃ ሙስና ተብሎ ጉዳዩን ወደ ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ብታመለክትበት ዳኛው ከኃላፊነቱ የሚነሳበት ቀጥተኛ ማስረጃ ነው የሚሆነው።
- ክርክር በተነሳበት ጉዳይ ላይ የጥቅም ግንኙነት በመፍጠር እንዲህ ማድረግ ትልቅ የዲሲፒሊን ጥፋት ነው።
- ልጅቷ ቅጹ ላይ አለች፣ ደባል ናት፣ የቤተሰብ አባል ናት ቀጥተኛ ልጅ ባትሆንም፣ የቀበሌ ቤቶች ደግሞ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎቸ ነው የተዘጋጁት፣ ሜዳ ላይ መጣል የለባትም ብሎ የወረዳው አስተዳደር ወስኖ ወይ በዚያው ቤት ሊያስቀጥላት ይገባል የቀበሌ ቤቱ የሚፈርስ ከሆነም ምትክ የመንግስት ቤት እንድታገኝ ሁኔታዎችን ማመቻቸት አለበት።
- በህሊና ፍርድ ወይ አስተዳደራዊ በሆነ መንገድ የወረዳው አስተዳደር መፍትሄ ሊሰጣት ይገባል።
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-08
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia