አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
February 9
February 10
230493 (2).pdf
881.9 KB
February 10
የብድር ውል ይፍረስልኝ በሚል ከሚቀርብ ክስ ጋር በተያያዘ የተወሰነ አስተማሪ ጠቃሚ የሰበር ውሳኔ
በጋብቻ መካከል አንደኛው ተጋቢ የውል ግደታ ሲገባ በስምምነት ተሳታፊ ያልሆነ ተጋቢ ውል ይፍረስልኝ ክስ ሊያቀርብ በሚያስችል ልክ ስለውሉ መኖር የተሟላ እዉቀት ሊኖረው ስለሚገባ በአንደኘው ተጋቢ የተደረገ የብድር ውል መኖሩን ሌላኛው ተጋቢ አወቀ ሊባል የሚችለው ቢያንስ የገንዘብ ብድር ዉሉ ከማን ጋር እንደተደረገ፣ የምን ያህል ገንዘብ ብድር ውል እንደሆነ፣ መቼ የተደረገ ውል እንደሆነ ማወቅ ሲችል ነው፡፡በሌላ በኩል በፌደራል የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 68/መ እና 69/1 መሰረት የገንዘብ ብድር ውል ሲደረግ ያልተሳተፈ ተጋቢ እንድፈርስ በመጠየቅ ምክንያት ሊያደርግ የሚገባው እና ውሉ እንዲፈርስ ከመወሰኑ በፊት በፍሬ ነገር ደረጃ ሊረጋገጥ የሚገባው በገንዘብ ብድር ውል ግደታው በተዋናይነት አለመሳተፉ ብቻ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ የብድር ውል ይፍረስልኝ በሚል ከሚቀርብ ክስ ጋር በተያያዘ በብድር ተገኘ የተባለው ገንዘብ ለትዳር ጥቅም ውሏል ወይስ አልዋለም በሚል ጭብጥ ላይ በማከራከርነወ ውሳኔ መስጠት አይቻልም፡፡ ይህ አይነት ክርክር ሊቀርብ የሚገባው የጋብቻ ፍች ተከትሎ በሚደረግ የባል እና ሚስት ንብረት ክፍፍል ጊዜ ነው፡፡ ስለሆነም ፍረድ ቤቶች የብድር ውል ይፍረስልኝ ተብሎ በቀረበ ክስ ክርክር ላይ ለክርክሩ መነሻ የሆነው በብድር የተገኘው ገንዘብ ለትዳር ጥቅም ውሏል ወይስ አልዋለም የሚለውን ጭብጥ ላይ አከራክረው መወሰናቸው ሊታረም የሚገባው የክርክር አመራር ጉድለት ነው ፡፡
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቅጽ 26 በመ/ቁ 208197
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alehig.com @Alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
February 10
February 10
ታዋቂው ኢትዮጵያዊ ጠበቃ በአሜሪካ የተከሰሰውን ቻይናዊ ነፃ አወጡ፡፡ የስልሳ አምስት አመቱ ቻይናዊ ሊታንግ ሊያንግ በአሜሪካ ፌዴራል ፍርድ ቤት የተከሰሱት የቻይና ሰላይ ናቸው በሚል ነበር፡፡

እ.ኤ.አ በ2023 የቀረበባቸው ይህ ክስ በቦስተን የሚገኙ የቻይና ኮሚኒቲ አባላትንና ቡድኖችን እንዲሁም የመንግስት ተቃዋሚዎችን የግል መረጃ ለቻይና ባለስልጣናት እየሰጡ መሆኑን የሚገልፅ ነው፡፡ በክሱ ላይ የቻይና መንግስት በውጭ አገር የሚገኙ ተቺዎቹን ድምፅ ዝም ለማስባል በሚያደርገው እንቅስቃሴ እኚህ ቻይናዊ በድብቅ ለአገራቸው መንግስት እየሰለሉ መሆናቸው ተገልፆ ነበር፡፡

በቻይና የተወለዱትና የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው እኚህ ቻይናዊ ክሱ እንደቀረበባቸው የተባለውን ድርጊት እንዳልፈፀሙ ገልፀው ታዋቂውን ኢትዮጵያዊ የህግ ባለሙያ አቶ ደረጀ ደምሴን ጠበቃቸው አድርገው ሲሟገቱ ቆይተዋል፡፡ ጉዳዩ ትላንት በጁሪ ከታየ በኋላ ተከሳሹ ነፃ መሆናቸው ተገልፆላቸዋል፡፡

ይህ ውሳኔ ከተሰማ በኋላ የአሜሪካ መንግስት አቃቤ ህግ በመሆን ሲሟገቱ የቆዩት ሊህ ፎሊ ‹‹የጁሪውን ውሳኔ እናከብራለን፡፡ በመሆኑም ከዚህ በኋላ ክሳችንን አቋርጠናል›› ብለዋል፡፡ የተከሳሹ ጠበቃ አቶ ደረጄ ደምሴ እንደገለፁት ይህ ክስ የቀረበባቸው ቻይናዊ በቦስተን የሚገኘው የአሜሪካዊ ቻይናዊያን ኮሚኒቲ አስተባባሪና አክቲቪስት ናቸው፡፡

ብዙውን ጊዜ የቻይናን አንድነት ማለትም የታይዋንን መጠቃለል የተመለከቱ አስተያየቶችን እንደሚሰጡ የጠቀሱት አቶ ደረጄ ይህ ሀሳብ ከቻይና መንግስት አቋም ጋር ስለሚመሳል ብቻ የቻይና ሰላይ ተብለው መከሰሳቸውን አስረድተዋል፡፡ ጨምረውም ይህ ክስ የሰዎችን የመናገር ነፃነትን የሚገድብና ሌሎች ሰዎችን ለማስፈራራት ሲባል የቀረበ መሆኑን በመግለፅም ተከራክረዋል፡፡

ክርክሩን የተመለከቱት የጁሪ አባላትም የአቶ ደምሴን ሙግት ተቀብለው ተከሳሹ ላይ የቀረበው ክስ ውቅድ መሆን እንዳለበት ውሳኔ ካሳለፉ በኋላ ቻይናዊው ተከሳሽ ‹‹ትክክለኛ ፍትህ ዛሬ አግኝቻለሁ›› በማለት መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
(ዘ-ሐበሻ ዜና)
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
February 12
February 12
February 13