አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.55K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል " -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ ዕዳ ያለባቸው 62 ግብር ከፋዮች ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ገልጿል፡፡

እግድ የተጣለባቸው 62 ግለሰቦች በተደጋጋሚ ጥሪ ቢደረግላቸውም ዕዳቸውን ለመክፈል  ፈቃደኛ ያልሆኑ ናቸው ተብሏል።

" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል ዕዳቸውን የማይከፍሉ ከሆነም አዋጁ በሰጠን ሥልጣን መሰረትም በቀጣይ የንብረት እግድ እና ንብረታቸውን በሃራጅ የመሸጥ እርምጃዎች ይወሰዳሉ " ሲሉ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቢሮው በታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀፅ 44 ንዑስ አንቀፅ ከ1-3 ለተቋሙ በተሰጠ ስልጣን መሰረት ከሀገር እንዳይወጡ እግድ የተጣለባቸው ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ማስተላለፉን አሳውቋል፡፡

የ62ቱ ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተላከው በትላንትናው ዕለት ነው።

አቶ ሰውነት " በህጉ መሰረት የተቀመጠ ቀነ ገደብ አለ በአዋጁ በተቀመጠው ቀነ ገደብ መሰረት መጥተው እስካልከፈሉ ድረስ ለእዳው ማካካሻ በሚሆን መሰረት ንብረታቸው በሃራጅ ተሽጦ እዳው ይሸፈናል " ብለዋል።

ቢሮው የግብር ዕዳቸውን ሳይወጡ የሚሰወሩ ግብር ከፋዮችን በመከታተል ግዴታቸውን እንዲወጡ ለማስቻል የዕዳ ክትትልና አስተዳደር የስራ ክፍልን በ2017 በጀት ዓመት እንደ አዲስ አዋቅሯል።

በዚህም መሰረት ባለፉት 6 ወራት ከ 6.4 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ እዳ መሰብሰቡን አቶ ሰውነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
Welcome to Mikias Melak & Associates Law Office!

🔹 Facebook: AlehigOfficial
🔹 Telegram Channel: AleHig
🔹 Website: alehig.com
📧 Email: mikiasmelak.mm@gmail.com

📞 Direct Contact:
WhatsApp: +251920666595
Telegram: @MikiasMelak

For legal consultations and inquiries, feel free to reach out. We’ll get back to you as soon as possible!