አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Adidas Internships 2023 (Paid Internship)

Offered by: Adidas
Duration: 1 Year
Internship coverage: Paid
Eligible nationality: All Nationalities
Award country: UK and USA
Last Date: Open around the year

Apply Link:  https://shegeronline.com/2023/09/30/adidas-internships-2023-paid-internships/
Deakin University Scholarship 2024-25 in Australia (Fully Funded)

University: Deakin University
Degree level: Masters, PhD
Scholarship coverage: Fully Funded
Eligible nationality: All Nationalities
Award country: Australia
Last Date: Accepted all the Year.

Apply Link: https://shegeronline.com/2023/10/01/deakin-university-scholarship-2024-25-in-australia/
=========== የዉል ህግ ======
============== የዉል ምንነት
==
ዉል ማለት አንድ ሰዉ፣ተፈጥሮአዊ ሆነ በህግ ሰዉነት የተሰጠዉ፣ አንድን ተግባር ለመፈጸም ወይም ከመፈጸም ለመቆጠብ የሚገባዉን ግዴታ የሚያስርበት የስምምነት አይነት ነዉ፡፡ ይህ ዉል እቃዎችን ለመግዛት፣ ለመሸጥ ወይም አገልግሎት ለመስጠት፣ መብት ለመስጠት ወይም መብት ለማስቀረት፣ ስጦታ ለመስጠት፣ የስራ ቅጥር ለመፈጸም እንዲሁም የተለያዩ ተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ ተመስርቶ ሊፈጸም ይችላል፡፡
አንድ ዉል ምን አይነት ሁኔታዎችን ማሟላት አለበት?
የዉል ህግ የሚገዛዉ በሀገራችን የፍትሐብሔር ህግ ስር ነዉ፤ የተለያዩ ልዩ ሁኔታዎች እሚያስቀምጡ ህጎች ካሉ የእነሱ ተፈጻሚነት እንደተጠበቀ ሆኖ፡፡ ይህም የሆነዉ ከጠቅላላ ህግ ልዩ ህግ ቅድሚያ ስለሚሰጠዉ ነዉ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የአገራችን ዉል ህግ በአራተኛዉ መጽሃፍ ስር ከአንቀጽ 1675 ጀምሮ ባለዉ ይገዛል፡፡ አንቀጽ 1675 ዉልን ሲተረጉም “ዉል ማለት ንብረታቸዉን የሚመለከቱ ግዴታዎችን ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸዉ ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መካከል የሚደረግ ስምምነት ነዉ፡” በማለት ያስቀምጠዋል፡፡ ከዚህ ትርጉም መረዳት እንደምንችለዉ ዉል አንዱ ንብረት መፍጠሪያ መንገድ ነዉ፡፡ ይህም መብት የሚፈጠረዉ ሁለት ወይም ከሁለት በላይ በሆኑ ሰዎች ሆኖ ግዴታዎች ላይ በመመርኮዝ ነዉ፡፡ ግዴታ ተቋቋመ ፣ተለወጠ ወይም ቀረ የሚባለዉ እነዚህ ሰዎች በሚገቡት ዉል ላይ በሚያስቀምጡት መዘርዝር ነዉ፡፡ በመሆኑም አንድ ዉል እነዚህን መብቶች መፍጠሩን በግልጽ ማሳየት አለበት፡፡
አንድ ዉልም ዉል ለመባል፡-
1. ዉሉ ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች የተፈጸመ መሆን አለበት፡፡
አንድ ሰዉ ችሎታ አለዉ የሚባለዉ በህጉ የተቀመጠዉን የእድሜ ገደብ ሲሞላ ወይም ምንም አይነት የአእምሮ እክል ከሌለበት፣ ወይም በህግ የተከለከለ ካልሆነ ነዉ፡፡ እነዚህ ሁኔታዎችም ተሟልተዉ ቢሆን ዉሉን የሚገባዉ ሰዉ ሙሉ ፈቃዱን የሰጠ መሆን አለበት፡፡ ማንም ሰዉ ቢሆን በማስፈራራት፣ በመደለል፣ በማታለል ሆነ በማስገደድ የዉል ግዴታ ዉስጥ ማስገባት አይቻልም፡፡
2. በዉሉ ላይ እንዲፈጸም የተቀመጠዉ ጉዳይ በአግባቡ ትርጉም የተሰጠዉ ወይም እርግጠኝነት ያለዉ፣ ሊፈጸም የሚቻልና ህጋዊ የሆነ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ አለም ዉጪ የሆነ ወይም ለመፈጸም በማንኛዉም መልኩ ቢሆን አዳጋች የሆነ እንዲሁም ህገ-ወጥ ተግባር ለመፈጸም ዉል መግባት አይቻልም፡፡
3. በህጉ በአንድ በተለየ ፎርም እንዲፈጸም የተቀመጠ ዉል ከሆነና ይህንም ፎርም ያልተከተለ ከሆነ የሚጸና ዉል አይሆንም፡፡ ህጎች ብዙ ግዜ አንድን ዉል በጽሁፍ መሆን አለበት ካሉ በኋላ መልሰዉ የተለየ ሁኔታ የሚያስቀምጡበት ሁኔታ አለ፡፡ ለምሳሌ አንድ ዉል በጽሁፍ የሰፈረ መሆን አለበት ካለ በኋላ መልሶ ደግሞ ዉሉ መፈጸሙን በምስክር ማስረዳት ይቻላል ሲል ሊያስቀምጥ ይችላል፡፡ ይህም ሆኖ ግን ህጉ የተለየ ፎርም አስቀምጦ ከሆነ በዛዉ መልኩ መፈጸሙ ወደፊት ሊነሱ የሚችሉ ክርክሮች ሊያስቀርና የህግም ድጋፍ  ያገኛል።
ውብአለም መስፍን
የቦሌ/ክ/ከ/የህ/ስ/ም/መ ዳይሬክቶሬት ዐ/ህግ

👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
አለ_ህግ🔵Ale_Hig:
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ
#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ