አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.86K photos
25 videos
1.86K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
January 22, 2023
January 22, 2023
January 22, 2023
January 22, 2023
January 22, 2023
January 22, 2023
January 23, 2023
January 23, 2023
January 23, 2023
January 23, 2023
January 23, 2023
ተወካይ ተጠያቂ የሚሆንበት አግባብ
የድርጅቱን አስተዳደር በሚመለከት በውክልና ያለው ሰው ያስተላለፈ መሆኑ እና ተወካዩም በተቀበለው ውክልና መሠረት ሥራውን የሚያከናውን መሆኑ በተረጋገጠ ጊዜ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ሆኖ ያለተጨማሪ እሴት ታክስ ደረሰኝ ግብይት ማከናወኑ ሲረጋገጥ ተጠያቂ የሚሆነው ውክልናውን ተቀብሎ ስራውን በውክልና የሚያስተዳድረው ሰው እንጂ ስራ አስኪያጁ ወይም የድርጅቱ ባለቤት ሊሆን አይገባም፡፡
የሰ.መ.ቁ 211028/ያልታተመ/  - ፍርድ ቤት ቅጣት እንዲገደብ የቀረበ ጥያቄ ካለ ምክንያት ሳይሰጥ ተቀባይነት የለውም በሚል ውደቅ ማድረጉ አግባብነት ያለው የውሳኔ አሰጣጥ አይደለም።
በአዋጅ ቁጥር 285/94 በአዋጅ ቁጥር 609/2001 እንደተሻሻለው አንቀጽ 56/1/ አንቀጽ 22/1/ እና አንቀጽ 50/ለ/1 መሠረት የአንድ የንግድ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ በወንጀል ተጠያቂ የሚሆነው እሱ የሚመራው ድርጅት የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ሆኖ ያለተጨማሪ እሴት ታክስ ደረሰኝ ግብይት ማከናወኑ ሲረጋገጥ እንደሆነ፤ የድርጅቱ ሃላፊነት ከተረጋገጠ የሥራ አስኪያጁ ሃላፊነት የሕግ ግምት የሚወሰድበት ስለመሆኑ እንገነዘባለን፡፡ ሆኖም የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ የድርጅቱን አስተዳደር በሚመለከት በውክልና ያለው ሰው ያስተላለፈ መሆኑ እና ተወካዩም በተቀበለው ውክልና መሠረት ሥራውን የሚያከናውን መሆኑ በተረጋገጠ ጊዜ ተጠያቂ የሚሆነው ውክልናውን ተቀብሎ ስራውን በውክልና የሚያስተዳድረው ሰው እንጂ ስራ አስኪያጁ ወይም የድርጅቱ ባለቤት ሊሆን አይገባም፡፡

የልዩነት ሃሳብ- አንድ ስራ አስኪያጅ ከአዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀፅ 132/1/ከተመለከተው የወንጀል ሀላፊነት ነፃ ሊሆኑ የሚችለት ወንጀሉ የተፈፀመው ሳይፈቅዱ ወይም ሳያውቁ መሆኑን አሊያም በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ ያለና ነገሮችን በጥንቃቄ የሚያይ ሰው የጥፋቱን መፈፀም ለመከላከል ይወስዳቸዋል ተብለው የሚገመቱ ጥንቃቄዎችን ለማድረግ ተገቢውን ትጋትና የአሰራር ጥበብ የተሞላበት እርምጃ መውሰዳቸውን በአንቀፅ 132/2/ አግባብ ሲያስረዱ ቢሆንም በዚህ አግባብ ለማስረዳታቸው የሥር ፍርድ ቤት መዝገብ አያሳይም፡፡
Via #Danielfikadu law office
https://t.me/lawsocieties
January 23, 2023
January 23, 2023