ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (One-person private limited Company) እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር (Limited Liability Partnership) በአዲሱ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013
በ:- አበጀ ካሣሁን
ባሳለፍነው ዓመት ኢትዮጵያ ላለፉት ስድስት አስር አመታት ስትጠቀምበት የነበረውን የንግድ ሕግ በማሻሻል በአዲሱ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 ተክታለች፡፡ በቀድሞ የንግድ ህግ አንድ ነጋዴ ሊመሠርት የሚችለው የንግድ ማህበር ወይም ድርጅት ስድስት ዓይነት ሲሆን እነዚህም ተራ የሽርክና ማህበር (ordinary partnership) ፣ የህብረት ሽርክና ማህበር (general partnership) ፣ ሁለት ዓይነት ኃላፊነት ያለበት የሽርክና ማኅበር (limited Partnership)፣ የእሽሙር ሽርክና ማህበር (joint venture) ፣ የአክሲዮን ማህበር (share company) እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል (private limited company) ማህበር ናቸው፡፡
በአዲሱ የንግድ ሕግ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (One-person private limited Company) እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር (Limited Liability Partnership) አዲስ የተጨመሩ ማህበራት ሲሆኑ ተራ የሽርክና ማህበር ደግሞ ከአማራጭ ማህበርነት ተቀንሷል፡፡ የዚህ አጭር ፅሁፍ ዓላማ አዳዲስ የተጨመሩትን እንግዳ የንግድ ማህበራት በመመርመር ማስተዋወቅ ነው፡፡
መልካም ንባብ!
https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2008-one-person-private-limited-company-vs-limited-liability-partnership-under-the-new-commercial-code-of-ethiopia
በ:- አበጀ ካሣሁን
ባሳለፍነው ዓመት ኢትዮጵያ ላለፉት ስድስት አስር አመታት ስትጠቀምበት የነበረውን የንግድ ሕግ በማሻሻል በአዲሱ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 ተክታለች፡፡ በቀድሞ የንግድ ህግ አንድ ነጋዴ ሊመሠርት የሚችለው የንግድ ማህበር ወይም ድርጅት ስድስት ዓይነት ሲሆን እነዚህም ተራ የሽርክና ማህበር (ordinary partnership) ፣ የህብረት ሽርክና ማህበር (general partnership) ፣ ሁለት ዓይነት ኃላፊነት ያለበት የሽርክና ማኅበር (limited Partnership)፣ የእሽሙር ሽርክና ማህበር (joint venture) ፣ የአክሲዮን ማህበር (share company) እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል (private limited company) ማህበር ናቸው፡፡
በአዲሱ የንግድ ሕግ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (One-person private limited Company) እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር (Limited Liability Partnership) አዲስ የተጨመሩ ማህበራት ሲሆኑ ተራ የሽርክና ማህበር ደግሞ ከአማራጭ ማህበርነት ተቀንሷል፡፡ የዚህ አጭር ፅሁፍ ዓላማ አዳዲስ የተጨመሩትን እንግዳ የንግድ ማህበራት በመመርመር ማስተዋወቅ ነው፡፡
መልካም ንባብ!
https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2008-one-person-private-limited-company-vs-limited-liability-partnership-under-the-new-commercial-code-of-ethiopia
Forwarded from አለሕግ🔵AleHig
ባለአንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር በአዲሱ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013
1. አጭር መግቢያ
ባሳለፍነው ዓመት ኢትዮጵያ ላለፉት ስድስት አስር አመታት ስትጠቀምበት የነበረውን የንግድ ሕግ በማሻሻል በአዲሱ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 ተክታለች፡፡ ለቀድሞ ንግድ ህግ መሻሻል የተለያዩ ምክንያቶች ቢጠቀሱም በሌላው ዓለም የተለመዱ እና ለንግዱ ማህበረሰቡ አስፈላጊ የሆኑ አዳዲስ የንግድ ማህበራትን ማካተት አንዱ እና ዋነኛው ነው፡፡ በቀድሞ የንግድ ህግ አንድ ነጋዴ ሊመሠርት የሚችለው የንግድ ማህበር ወይም ድርጅት ስድስት ዓይነት ሲሆን እነዚህም ተራ የሽርክና ማህበር (ordinary partnership)፣ የህብረት ሽርክና ማህበር (general partnership)፣ ሁለት ዓይነት ኃላፊነት ያለበት የሽርክና ማኅበር (limited Partnership)፣ የእሽሙር ሽርክና ማህበር (joint venture) ፣ የአክሲዮን ማህበር (share compary) እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል (private limited company) ማህበር ናቸው፡፡
በአዲሱ የንግድ ሕግ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (One person private limited Company) እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር (Limited Liability Partnership) አዲስ የተጨመሩ ማህበራት ሲሆኑ ተራ የሽርክና ማህበር ደግሞ ከአማራጭ ማህበርነት ተቀንሷል፡፡ የዚህ አጭር ፅሁፍ ዓላማ አዳዲስ የተጨመሩትን እንግዳ የንግድ ማህበራት በመመርመር ማስተዋወቅ ነው፡፡
ይህ ፅሁፍ የህግ አስተያየትን እንዲተካ በማሰብ የተዘጋጀ ባለመሆኑ በዚህ ፅሁፍ የሠፈሩትን ሃሳቦች መሠረት በማድረግ ውሳኔ ለመስጠት የህግ አስተያየት መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡
2. ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (One person private limited Company)፣
2.1 ስለ ማህበሩ ባህሪያት እና አመሠራረት
ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ማለት አንድ ሰው በግሉ በሚሰጠው መግለጫ (Unilateral Declaration) መሠረት የተቋቋመ የንግድ ማህበር ነው:: ማህበሩ ከአባላት የተለየና የተነጠለ የራሱ የህግ ሰውነት ወይም corporate existence አለው፡፡ ይህን ማህበር ለማቋቋም የሚያስፈልገው አነስተኛ ካፒታል መጠን ብር 15,000 (አስራ አምስት ሺህ) ነው፡፡
ይህ የንግድ ማህበር በአገራችን ከተለመዱት የንግድ ማህበራት የተለየ ሲሆን በአዲሱ የንግድ ህግ የተካተተበት ምክንያት አንድ ማህበር (ኩባንያ) ለመመስረት በቂ ካፒታል የያዘ ባለሃብት የግድ ምናባዊ (fictitious) ማህበርተኛ መፈለግ እንዳይገደድ ፤ የተለያየ ካፒታል በመመደብ ለሥራ የሚውለውን ገንዘብ ነጥለው ሥራ መስራት ለሚፈልጉ ባለሃብቶች እድል ማመቻቸት፤ በሌሎች ሃገራት የተለመዱ የንግድ ማህበራት ወደ ሃገራች ማካተት ተጠቃሾች ናቸው፡፡
ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የሚመሠረተው አባሉ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ፅ/ቤት በመቅረብ በሚሠጠው መግለጫ መሰረት ነው፡፡ ይህን መግለጫ መመስረቻ ፅሁፍን የተካ ነው፡፡ መግለጫው ማህበሩ ከተለመዱት ዝርዝሮች በተጨማሪ አንድ አባል ብቻ ያለው መሆኑን፣አባሉ የሞተ፣ የጠፋ ወይም በፍርድ የተከለከለ እንደሆነ ስለ ወራሾች ወይም ስለአባሉ ሆኖ ሕጋዊ ተግባራትን እዲፈፅም የታጨው የንብረት ጠባቂ ሰው ስም እና ዕጩ ንብረት ጠባቂው ፍቃደኛ ሆኖ ኃላፊነቱን የተቀበለ መሆኑ ሊያካትት ይገባል፡፡
ዕጩ ንብረት ጠባቂ መሰየም የምስረታ ቅድመ ሁኔታ በመሆኑ ዕጩ ንብረት ጠባቂው ዕጩነቱን ለመቀበል ፈቃደኛ መሆኑን በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ፅ/ቤት ቀርቦ ካላረጋገጠ ማህበሩ ሊመሰረት አይችልም፡፡ አንድ ንብረት ጠባቂ በአንድ ጊዜ ለተለያዩ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለሆኑ ማህበራት ንብረት ጠባቂ ሆኖ ሊሾም አይችልም፡፡
አንድ ባለአንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሌላ ባለአንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሊያቋቋም አይችልም ይህን ተላላፎ የተቋቋም ማህበር ያገባኛል በሚል ሰው ጠያቂነት ሊፈር እንዲሁም በምስረታው ምክንያት እና በኋላ ለሶስተኛ ወገኖች ላይ ለሚደርሰው ጉዳት አባሉና ማህበሩ በአንድነትና በተናጠል ኃላፊ ይሆናሉ፡፡
አንድ ግለሰብ ነጋዴ (Sole proprietor) ወደ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ ግል ማህበር መለወጥ የሚችል ሲሆን ግለሰቡ ማህበሩን ከመመስረቱ በፊት ለገባበት ዕዳ ሁሉ ከማህበሩ ጋር በአንድነትና በተናጠል ኃላፊ ይሆናል፡፡
2.2 ስለ ማህበሩ ሥራ አመራር እና ኃላፊነት ወሰን፣
ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እንደ ማንኛውም ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊኖረው ግዴታ ሲሆን ፤ አባሉ ራሱ ወይም ሌላ ሰው የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ ሊሆን ይችላል፡፡ ዋና ሥራ አስኪያጁ አንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሥራ አስኪያጅ በህግ የተሠጠው ሥልጣን ይኖረዋል፡፡
አባሉ በንግድ ሕጉ ለአንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጠቅላላ ጉባዬ የተሠጠው ሥልጣን ይኖረዋል፡፡ አባሉ በጠቅላላ ጉባዔ ሥልጣኑ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ቃለጉባዔ ስበሰባው በተደረገ ከሦስት ሣምንታት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ በፅሁፍ ተዘጋጅተው የማህበር ማህደሩ ውስጥ ሊቀመጡ እንዲሁም ውሳኔዎቹ የማህበሩን ማቋቋሚያ መግለጫ የሚለውጡ ከሆነ ውሳኔው ከተሠጠበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በንግድ መዝገብ ውስጥ መግባት አለበት፡፡ ይህን ቅድመ ሁኔታ ባይሟላ እንኳን ውሳኔዎቹ በሕግ የሚፀኑ ቢሆንም ጉድለቱ በሦስተኛ ወገኖች ላይ ለሚያደርሰው ጉዳት አባሉና ማህበሩ በአንድነት እና በተናጠል ተጠያቂዎች ናቸው፡፡
ምንም እንኳን የአባሉ ኃላፊነት የተወሰነ (Limited Liability) ቢሆንም አባሉ ወይም በማህበሩ ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ቁጥጥር ያለው ሌላ ሰው ማህበሩን፣ ወይም የማህበሩን ገንዘብ ጠያቂዎች ጉዳት ላይ የሚጥል ሕገ ወጥ ድርጊት ሆን ብሎ ከፈፀመ፤ የማህበሩን ንብረትን ከራሱ ንብረት ጋር ከቀላቀለ፤ የማህበሩን እና የራሱን ማንነት ካልነጣጠለ፤ ስለማህበሩ የፋይናንስ አቋም የማህበሩን ገንዘብ ጠያቂዎች ሊያሳስት የሚችል መረጃ ሆን ብሎ ካወጣ፤ ያለ ተመጣጣኝ ክፍያ የማህበሩን ሀብት ለራሱ ወይም ለሦስተኛ ወገኖች የግል ጥቅም ካዋለ፤ በሕግ ሊከፈል ከሚችለው በላይ የትርፍ ክፍያ ከፈፀመ ወይም ተመሳሳይ ተግባራት ከፈፀመ ከማህበሩ ጋር በአንድነት እና በተናጠል ተጠያቂ ይሆናል ወይም በሌላ አገላለፅ የኩባንያን ጭምብል መግለጥ መርህ ወይም piercing the corporate veil principle ተግባራዊ ይሆናል፡፡
2.3 ስለማህበሩ መፍረስ፣
ስለ ማህበራት መፍረስ ከተጠቀሱት ጠቅላላ ድንጋጌዎች በተጨማሪ አባሉ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሂሳቡ ሳይጣራ እንዲፈርስ ከፈለገ ሂሳብ ሳይጣራ ሊፈርስ ይችላል፡፡ ማህበሩ ሂሳቡ ሳይጣራ የፈረሰ እንደሆነ የማህበሩ ሃብት በጠቅላላው ለአባሉ ይተላለፋል፡፡ በማናቸውም ምክንያት ማህበሩ ከፈረሰ በኋላ ገንዘብ ጠያቂዎች የቀረቡ እንደሆነ አባሉ በግሉ ተጠያቂ ይሆናል፡፡
ማህበሩ ከፈረሰ በኃላ የሚቀርብ ገንዘብ ጠያቂ የሚያቀርበው ጥያቄ ማህበሩ መፍረሱን ካወቀ በአምስት ዓመት ወይም የማህበሩ ሀብት ለአባሉ ከተከፋፈለ በምንም ዓይነት ከአስር ዓመት በኋላ ሊቀርብ አይችልም፡፡
1. አጭር መግቢያ
ባሳለፍነው ዓመት ኢትዮጵያ ላለፉት ስድስት አስር አመታት ስትጠቀምበት የነበረውን የንግድ ሕግ በማሻሻል በአዲሱ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 ተክታለች፡፡ ለቀድሞ ንግድ ህግ መሻሻል የተለያዩ ምክንያቶች ቢጠቀሱም በሌላው ዓለም የተለመዱ እና ለንግዱ ማህበረሰቡ አስፈላጊ የሆኑ አዳዲስ የንግድ ማህበራትን ማካተት አንዱ እና ዋነኛው ነው፡፡ በቀድሞ የንግድ ህግ አንድ ነጋዴ ሊመሠርት የሚችለው የንግድ ማህበር ወይም ድርጅት ስድስት ዓይነት ሲሆን እነዚህም ተራ የሽርክና ማህበር (ordinary partnership)፣ የህብረት ሽርክና ማህበር (general partnership)፣ ሁለት ዓይነት ኃላፊነት ያለበት የሽርክና ማኅበር (limited Partnership)፣ የእሽሙር ሽርክና ማህበር (joint venture) ፣ የአክሲዮን ማህበር (share compary) እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል (private limited company) ማህበር ናቸው፡፡
በአዲሱ የንግድ ሕግ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (One person private limited Company) እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር (Limited Liability Partnership) አዲስ የተጨመሩ ማህበራት ሲሆኑ ተራ የሽርክና ማህበር ደግሞ ከአማራጭ ማህበርነት ተቀንሷል፡፡ የዚህ አጭር ፅሁፍ ዓላማ አዳዲስ የተጨመሩትን እንግዳ የንግድ ማህበራት በመመርመር ማስተዋወቅ ነው፡፡
ይህ ፅሁፍ የህግ አስተያየትን እንዲተካ በማሰብ የተዘጋጀ ባለመሆኑ በዚህ ፅሁፍ የሠፈሩትን ሃሳቦች መሠረት በማድረግ ውሳኔ ለመስጠት የህግ አስተያየት መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡
2. ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (One person private limited Company)፣
2.1 ስለ ማህበሩ ባህሪያት እና አመሠራረት
ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ማለት አንድ ሰው በግሉ በሚሰጠው መግለጫ (Unilateral Declaration) መሠረት የተቋቋመ የንግድ ማህበር ነው:: ማህበሩ ከአባላት የተለየና የተነጠለ የራሱ የህግ ሰውነት ወይም corporate existence አለው፡፡ ይህን ማህበር ለማቋቋም የሚያስፈልገው አነስተኛ ካፒታል መጠን ብር 15,000 (አስራ አምስት ሺህ) ነው፡፡
ይህ የንግድ ማህበር በአገራችን ከተለመዱት የንግድ ማህበራት የተለየ ሲሆን በአዲሱ የንግድ ህግ የተካተተበት ምክንያት አንድ ማህበር (ኩባንያ) ለመመስረት በቂ ካፒታል የያዘ ባለሃብት የግድ ምናባዊ (fictitious) ማህበርተኛ መፈለግ እንዳይገደድ ፤ የተለያየ ካፒታል በመመደብ ለሥራ የሚውለውን ገንዘብ ነጥለው ሥራ መስራት ለሚፈልጉ ባለሃብቶች እድል ማመቻቸት፤ በሌሎች ሃገራት የተለመዱ የንግድ ማህበራት ወደ ሃገራች ማካተት ተጠቃሾች ናቸው፡፡
ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የሚመሠረተው አባሉ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ፅ/ቤት በመቅረብ በሚሠጠው መግለጫ መሰረት ነው፡፡ ይህን መግለጫ መመስረቻ ፅሁፍን የተካ ነው፡፡ መግለጫው ማህበሩ ከተለመዱት ዝርዝሮች በተጨማሪ አንድ አባል ብቻ ያለው መሆኑን፣አባሉ የሞተ፣ የጠፋ ወይም በፍርድ የተከለከለ እንደሆነ ስለ ወራሾች ወይም ስለአባሉ ሆኖ ሕጋዊ ተግባራትን እዲፈፅም የታጨው የንብረት ጠባቂ ሰው ስም እና ዕጩ ንብረት ጠባቂው ፍቃደኛ ሆኖ ኃላፊነቱን የተቀበለ መሆኑ ሊያካትት ይገባል፡፡
ዕጩ ንብረት ጠባቂ መሰየም የምስረታ ቅድመ ሁኔታ በመሆኑ ዕጩ ንብረት ጠባቂው ዕጩነቱን ለመቀበል ፈቃደኛ መሆኑን በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ፅ/ቤት ቀርቦ ካላረጋገጠ ማህበሩ ሊመሰረት አይችልም፡፡ አንድ ንብረት ጠባቂ በአንድ ጊዜ ለተለያዩ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለሆኑ ማህበራት ንብረት ጠባቂ ሆኖ ሊሾም አይችልም፡፡
አንድ ባለአንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሌላ ባለአንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሊያቋቋም አይችልም ይህን ተላላፎ የተቋቋም ማህበር ያገባኛል በሚል ሰው ጠያቂነት ሊፈር እንዲሁም በምስረታው ምክንያት እና በኋላ ለሶስተኛ ወገኖች ላይ ለሚደርሰው ጉዳት አባሉና ማህበሩ በአንድነትና በተናጠል ኃላፊ ይሆናሉ፡፡
አንድ ግለሰብ ነጋዴ (Sole proprietor) ወደ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ ግል ማህበር መለወጥ የሚችል ሲሆን ግለሰቡ ማህበሩን ከመመስረቱ በፊት ለገባበት ዕዳ ሁሉ ከማህበሩ ጋር በአንድነትና በተናጠል ኃላፊ ይሆናል፡፡
2.2 ስለ ማህበሩ ሥራ አመራር እና ኃላፊነት ወሰን፣
ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እንደ ማንኛውም ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊኖረው ግዴታ ሲሆን ፤ አባሉ ራሱ ወይም ሌላ ሰው የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ ሊሆን ይችላል፡፡ ዋና ሥራ አስኪያጁ አንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሥራ አስኪያጅ በህግ የተሠጠው ሥልጣን ይኖረዋል፡፡
አባሉ በንግድ ሕጉ ለአንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጠቅላላ ጉባዬ የተሠጠው ሥልጣን ይኖረዋል፡፡ አባሉ በጠቅላላ ጉባዔ ሥልጣኑ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ቃለጉባዔ ስበሰባው በተደረገ ከሦስት ሣምንታት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ በፅሁፍ ተዘጋጅተው የማህበር ማህደሩ ውስጥ ሊቀመጡ እንዲሁም ውሳኔዎቹ የማህበሩን ማቋቋሚያ መግለጫ የሚለውጡ ከሆነ ውሳኔው ከተሠጠበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በንግድ መዝገብ ውስጥ መግባት አለበት፡፡ ይህን ቅድመ ሁኔታ ባይሟላ እንኳን ውሳኔዎቹ በሕግ የሚፀኑ ቢሆንም ጉድለቱ በሦስተኛ ወገኖች ላይ ለሚያደርሰው ጉዳት አባሉና ማህበሩ በአንድነት እና በተናጠል ተጠያቂዎች ናቸው፡፡
ምንም እንኳን የአባሉ ኃላፊነት የተወሰነ (Limited Liability) ቢሆንም አባሉ ወይም በማህበሩ ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ቁጥጥር ያለው ሌላ ሰው ማህበሩን፣ ወይም የማህበሩን ገንዘብ ጠያቂዎች ጉዳት ላይ የሚጥል ሕገ ወጥ ድርጊት ሆን ብሎ ከፈፀመ፤ የማህበሩን ንብረትን ከራሱ ንብረት ጋር ከቀላቀለ፤ የማህበሩን እና የራሱን ማንነት ካልነጣጠለ፤ ስለማህበሩ የፋይናንስ አቋም የማህበሩን ገንዘብ ጠያቂዎች ሊያሳስት የሚችል መረጃ ሆን ብሎ ካወጣ፤ ያለ ተመጣጣኝ ክፍያ የማህበሩን ሀብት ለራሱ ወይም ለሦስተኛ ወገኖች የግል ጥቅም ካዋለ፤ በሕግ ሊከፈል ከሚችለው በላይ የትርፍ ክፍያ ከፈፀመ ወይም ተመሳሳይ ተግባራት ከፈፀመ ከማህበሩ ጋር በአንድነት እና በተናጠል ተጠያቂ ይሆናል ወይም በሌላ አገላለፅ የኩባንያን ጭምብል መግለጥ መርህ ወይም piercing the corporate veil principle ተግባራዊ ይሆናል፡፡
2.3 ስለማህበሩ መፍረስ፣
ስለ ማህበራት መፍረስ ከተጠቀሱት ጠቅላላ ድንጋጌዎች በተጨማሪ አባሉ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሂሳቡ ሳይጣራ እንዲፈርስ ከፈለገ ሂሳብ ሳይጣራ ሊፈርስ ይችላል፡፡ ማህበሩ ሂሳቡ ሳይጣራ የፈረሰ እንደሆነ የማህበሩ ሃብት በጠቅላላው ለአባሉ ይተላለፋል፡፡ በማናቸውም ምክንያት ማህበሩ ከፈረሰ በኋላ ገንዘብ ጠያቂዎች የቀረቡ እንደሆነ አባሉ በግሉ ተጠያቂ ይሆናል፡፡
ማህበሩ ከፈረሰ በኃላ የሚቀርብ ገንዘብ ጠያቂ የሚያቀርበው ጥያቄ ማህበሩ መፍረሱን ካወቀ በአምስት ዓመት ወይም የማህበሩ ሀብት ለአባሉ ከተከፋፈለ በምንም ዓይነት ከአስር ዓመት በኋላ ሊቀርብ አይችልም፡፡
Forwarded from አለሕግ🔵AleHig
ከላይ በዝርዝር ከተመለከትናቸው ነጥቦች ውጪ ስለ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የተደነገጉት ህጎች ለባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበርም የሚያገለግሉ በመሆኑ ክፍተቶችን ለመሙላት ልንጠቀምባቸው እንችላለን፡፡
3. ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር (Limited Liability Partnership)፣
3.1 ስለ ማህበሩ ባህሪያት እና አመሠራረት
ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር ማለት ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች የሙያና ለሙያው ደጋፊ የሆነ አገልግሎት (professional and complementary service) ለመስጠት የሚያቋቁሙት የማህበርተኞች ኃላፊነት በመዋጮዋቸው የተወሰነ የንግድ ማህበር ነው፡፡ ይህን ማህበር ሊያቋቁሙ የሚችሉት ሥልጣን ባለው መስሪያ ቤት የሙያ ፈቃድ ወይም ለሙያ ደጋፊ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት የሚችሉ ለምሳሌ እንደ ህግ ባለሙያ፣ ጤና ባለሙያ ፣ የሂሣብ ባለሙያ አይነት የተፈጥሮ ሰዎች አሊያም ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበራት ናቸው፡፡
ይህ ማህበር ከአባላቱ የተለየ የህግ ሰውነት ያለው ፤ እንደ መክሰስ መከሰስእና በራሱ ስም ውል መዋዋል የመሳሰሉ ህጋዊ ድርጊቶች በራሱ ስም መፈፀም የሚችል ሲሆን የሽሪኮቹ መሞት ፣ መክሰር፣ ከማህበሩ መውጣት ወይም በሽርኮቹ ላይ የሚደረግ ማንኛውም ለውጥ በማህበሩ ሕልውና፣ መብት ወይም ግዴታ ላይ ተፅዕኖ አይኖረውም፡፡ ማህበሩ ስም ለማውጣት የተቀመጡት ማለትም ለሞራል ተቃራኒ አለመሆን ፣ የሌሎች ነጋዴዎችን መብት አለመጋፋት ወዘተ… የመሳሰሉ የህግ መስፈርቶች እንደተጠበቁ ሆነው የመረጠውን ሥም (Assumed Name) መጠቀም የሚችል ሲሆን ከስሙ በስተመጨረሻ ግን "ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር" የሚል ሐረግ መጨመር አለበት፡፡
በአዲሱ የንግድ ሕግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበርን ጨምሮ ከባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ውጪ ያሉት ማህበራት በሙሉ የሚቋቋሙት በመመስረቻ ፅሁፍ ብቻ ነው፡፡ ከዚህ በፊት በቀድሞ ሕግ የነበረው መተዳደሪያ ደንብ በአዲሱ ሕግ ቀሪ ተደርጓል፡፡ የዚህን ዓይነት ማህበር መመስረት የሚችሉት የሙያ ፈቃድ ያላቸው የተፈጥሮ ሰዎች ወይም ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበራት ናቸው፡፡
3.2 ሥለ ማህበሩ ሥራ አመራር እና ኃላፊነት ወሰን
ማህበሩ ምንም እንኳን ከተፈጥሮ ሰው በተጨማሪ ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበርን በአባልነት መያዝ የሚችል ቢሆንም ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ መሾም የሚችለው የተፈጥሮ ሰው የሆነ እና ማህበሩ አገልግሎት በሚሰጥበት ሞያ ፈቃድ ያለው ሸሪክ ብቻ ነው፡፡ የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ የማህበሩን ዓላማ ለማሳካት በማህበሩ ስም ማንኛውንም ሕጋዊ ተግባር ለማከናወን የሚችል ሲሆን ይህን ሥልጣን የሚገድቡ ስምምነቶች ሶስተኛ ወገኖችን መቃወሚያ የሚሆኑት በንግድ መዝገብ የተመዘገቡ ወይም ሦስተኛ ወገኖች የሥራ ኃላፊነቱን የሚያውቁ መሆናቸው የተረጋገጠ እንደሆነ ነው፡፡
የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ ሥልጣንና ተግባር የሚደነግገው የማህበሩ መመስረቻ ፅሁፍ ሲሆን ይህም መመስረቻ ፅሁፍ ተቃራኒ ስምምነተ ከሌለ በአባላት ሁለት ሶስተኛ (2/3) ድምፅ በሚሰጥ ውሳኔ ሊሻሻል ይችላል፡፡ ሌላ ማንኛውም ውሳኔ በአብዛኛዎቹ አባላት የድምፅ ድጋፍ ማለትም (50+1) ሊፀድቅ ይችላል፡፡ የማህበሩ ዜግነት ወይም የሥራ መስክ ለመለወጥ የሚሰጥ ውሳኔ የሚፀናው በ3/4ኛ (ሶስት አራተኛ) ድጋፍ ድምፅ ነው፡፡
የማህበሩ እና የአባላት ኃላፊነት ሌላኛው ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ነጥብ ነው ፡፡ በመሠረቱ ህጋዊ ሰውነት እና የማህበሩ ኃላፊነት ውስንነት የማይነጣጠኑ ሀሳቦች ናቸው (corporate existence and limited liability are inseparable):: ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበርን የሚለው ስም በቁሙ ስንመለከተው ኃላፊነቱ የተወሰነው የሚመስለው የማህበሩ ነው ነገር ግን ዝርዝሩን ስንመለከት ኃላፊነቱ የተወሰነው የሽሪኮች ነው ምክንያቱም የሽሪኮች ኃላፊነት በመዋጮዋቸው የተወሰነ ነው፡፡ በእርግጥ የማህበሩ ኃላፊነትም ቢሆን በግልፅ አልተጠቀሰም እንጂ የኃላፊነቱ መጠን በማህበሩ ሀብት (Asset) ልክ ነው፡፡
ሥራ አስኪያጅ ወይም ሸሪክ ከመዋጮ ባለፈ ኃላፊ ሊሆን የሚችልበት አግባብ አለ፡፡ እንዲህ አይነት ሁኔታዎች የኩባንያውን ጭምብል መግለጥ ወይም (Pericing the corporate Veil) ይባላል፡፡ ሥራ አስኪያጁ ከሥልጣኑ በላይ ለሚሠራው ሥራ ሁሉ ኃላፊነቱ የማህበሩ ሳይሆን የሥራ አስኪያጁ ብቻ ነው፡፡ ሸሪኩ ወይም ሠራተኛው የማህበሩን ሥራ በሚያከናውንበት ወቅት ሆን ብሎ ወይም የማታለል ተግባር በመፈፀም ወይም በቸልተኝነት ለሚፈፅመው ጥፋት ወይም ለሚያደርሰው ጉዳት ጥፋቱን ካደረሰው ሸሪክ ወይም ሠራተኛ ጋር ማህበሩ በአንድነትና በተናጠል ተጠያቂ ይሆናል፡፡ ማህበሩ ጉዳት የደረሰበት አካል ጉዳት አድራሹ ሥልጣን ያልተሠጠው መሆኑን ያስረዳ እንደሆነ ከኃላፊነት ነፃ ይወጣል፡፡ ማህበሩ ይህን መሠል ዕዳዎች ለመሸፈን የመድን ሽፋን እንዲኖረው በህግ ይገደዳል፡፡
3.3 አባል ከማህበሩ ስለሚወጣበት መንገድ እና ስለማህበሩ መፍረስ
አንድ አባል ከማህበሩ ሊወጣ የሚችለው የሶስት ወር ቅድመ ማስጠንቀቂያ በመስጠት (ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ) ፣ ሲሞት ወይም ህጋዊ ሰውነት ሲያጣ ፣ ድርሻው በገንዘብ ጠያቂዎች ሲወሰድ ፣ የሞያ ፈቃዱ ሲሰረዝ ወይም ለረጅም ጊዜ ሲታገድ፣ በሕመም ወይም አካል ጉድለት ወይም ሌሎች ምክንያቶች ግዴታውን ለመወጣት የማያስችለው ሲሆን ወይም ፍርድ ቤት በበቂ ምክንያት ከማህበሩ እንዲወጣ ሲወስን ነው፡፡ አንድ ሸሪክ ከማህበሩ ከመውጣቱ በፊት ለሶስተኛ ወገኖች የነበረበት ዕዳ ኃላፊነት ከማህበሩ በመውጣቱ ቀሪ አይሆንም ፡፡
አንድ ሽሪክ ድርሻውን በሌሎች ማህበርተኞች ተቀባይነት ላገኘ ሌላ ማህበርተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሳያስተላልፍ የወጣ እንደሆነ ህጋዊ መብት ያለው ወራሽ ወይም ባለመብት ድርሻው ተሰልቶ እንዲሰጠው ከመጠየቅ ውጪ አባል ለመሆን የሚያቀርበው ጥያቄ ተቀባይነት የለውም፡፡
በንግድ ሕግ ቁጥር 181 ንግድ ማህበራት ከሚፈርሱበት ሁኔታ በተጨማሪ የማህበሩ አባላት ቁጥር ወደ አንድ ዝቅ ያለ እንደሆነ እና በስድስት ወራት አሊያም ዘጠኝ ወራት ውስጥ ወደ ሁለት ከፍ ካላለ ማህበሩ ሊፈርስ ይገባል።
Abeje Kassahun Adamu
3. ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር (Limited Liability Partnership)፣
3.1 ስለ ማህበሩ ባህሪያት እና አመሠራረት
ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር ማለት ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች የሙያና ለሙያው ደጋፊ የሆነ አገልግሎት (professional and complementary service) ለመስጠት የሚያቋቁሙት የማህበርተኞች ኃላፊነት በመዋጮዋቸው የተወሰነ የንግድ ማህበር ነው፡፡ ይህን ማህበር ሊያቋቁሙ የሚችሉት ሥልጣን ባለው መስሪያ ቤት የሙያ ፈቃድ ወይም ለሙያ ደጋፊ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት የሚችሉ ለምሳሌ እንደ ህግ ባለሙያ፣ ጤና ባለሙያ ፣ የሂሣብ ባለሙያ አይነት የተፈጥሮ ሰዎች አሊያም ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበራት ናቸው፡፡
ይህ ማህበር ከአባላቱ የተለየ የህግ ሰውነት ያለው ፤ እንደ መክሰስ መከሰስእና በራሱ ስም ውል መዋዋል የመሳሰሉ ህጋዊ ድርጊቶች በራሱ ስም መፈፀም የሚችል ሲሆን የሽሪኮቹ መሞት ፣ መክሰር፣ ከማህበሩ መውጣት ወይም በሽርኮቹ ላይ የሚደረግ ማንኛውም ለውጥ በማህበሩ ሕልውና፣ መብት ወይም ግዴታ ላይ ተፅዕኖ አይኖረውም፡፡ ማህበሩ ስም ለማውጣት የተቀመጡት ማለትም ለሞራል ተቃራኒ አለመሆን ፣ የሌሎች ነጋዴዎችን መብት አለመጋፋት ወዘተ… የመሳሰሉ የህግ መስፈርቶች እንደተጠበቁ ሆነው የመረጠውን ሥም (Assumed Name) መጠቀም የሚችል ሲሆን ከስሙ በስተመጨረሻ ግን "ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበር" የሚል ሐረግ መጨመር አለበት፡፡
በአዲሱ የንግድ ሕግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበርን ጨምሮ ከባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ውጪ ያሉት ማህበራት በሙሉ የሚቋቋሙት በመመስረቻ ፅሁፍ ብቻ ነው፡፡ ከዚህ በፊት በቀድሞ ሕግ የነበረው መተዳደሪያ ደንብ በአዲሱ ሕግ ቀሪ ተደርጓል፡፡ የዚህን ዓይነት ማህበር መመስረት የሚችሉት የሙያ ፈቃድ ያላቸው የተፈጥሮ ሰዎች ወይም ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበራት ናቸው፡፡
3.2 ሥለ ማህበሩ ሥራ አመራር እና ኃላፊነት ወሰን
ማህበሩ ምንም እንኳን ከተፈጥሮ ሰው በተጨማሪ ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበርን በአባልነት መያዝ የሚችል ቢሆንም ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ መሾም የሚችለው የተፈጥሮ ሰው የሆነ እና ማህበሩ አገልግሎት በሚሰጥበት ሞያ ፈቃድ ያለው ሸሪክ ብቻ ነው፡፡ የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ የማህበሩን ዓላማ ለማሳካት በማህበሩ ስም ማንኛውንም ሕጋዊ ተግባር ለማከናወን የሚችል ሲሆን ይህን ሥልጣን የሚገድቡ ስምምነቶች ሶስተኛ ወገኖችን መቃወሚያ የሚሆኑት በንግድ መዝገብ የተመዘገቡ ወይም ሦስተኛ ወገኖች የሥራ ኃላፊነቱን የሚያውቁ መሆናቸው የተረጋገጠ እንደሆነ ነው፡፡
የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ ሥልጣንና ተግባር የሚደነግገው የማህበሩ መመስረቻ ፅሁፍ ሲሆን ይህም መመስረቻ ፅሁፍ ተቃራኒ ስምምነተ ከሌለ በአባላት ሁለት ሶስተኛ (2/3) ድምፅ በሚሰጥ ውሳኔ ሊሻሻል ይችላል፡፡ ሌላ ማንኛውም ውሳኔ በአብዛኛዎቹ አባላት የድምፅ ድጋፍ ማለትም (50+1) ሊፀድቅ ይችላል፡፡ የማህበሩ ዜግነት ወይም የሥራ መስክ ለመለወጥ የሚሰጥ ውሳኔ የሚፀናው በ3/4ኛ (ሶስት አራተኛ) ድጋፍ ድምፅ ነው፡፡
የማህበሩ እና የአባላት ኃላፊነት ሌላኛው ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ነጥብ ነው ፡፡ በመሠረቱ ህጋዊ ሰውነት እና የማህበሩ ኃላፊነት ውስንነት የማይነጣጠኑ ሀሳቦች ናቸው (corporate existence and limited liability are inseparable):: ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማህበርን የሚለው ስም በቁሙ ስንመለከተው ኃላፊነቱ የተወሰነው የሚመስለው የማህበሩ ነው ነገር ግን ዝርዝሩን ስንመለከት ኃላፊነቱ የተወሰነው የሽሪኮች ነው ምክንያቱም የሽሪኮች ኃላፊነት በመዋጮዋቸው የተወሰነ ነው፡፡ በእርግጥ የማህበሩ ኃላፊነትም ቢሆን በግልፅ አልተጠቀሰም እንጂ የኃላፊነቱ መጠን በማህበሩ ሀብት (Asset) ልክ ነው፡፡
ሥራ አስኪያጅ ወይም ሸሪክ ከመዋጮ ባለፈ ኃላፊ ሊሆን የሚችልበት አግባብ አለ፡፡ እንዲህ አይነት ሁኔታዎች የኩባንያውን ጭምብል መግለጥ ወይም (Pericing the corporate Veil) ይባላል፡፡ ሥራ አስኪያጁ ከሥልጣኑ በላይ ለሚሠራው ሥራ ሁሉ ኃላፊነቱ የማህበሩ ሳይሆን የሥራ አስኪያጁ ብቻ ነው፡፡ ሸሪኩ ወይም ሠራተኛው የማህበሩን ሥራ በሚያከናውንበት ወቅት ሆን ብሎ ወይም የማታለል ተግባር በመፈፀም ወይም በቸልተኝነት ለሚፈፅመው ጥፋት ወይም ለሚያደርሰው ጉዳት ጥፋቱን ካደረሰው ሸሪክ ወይም ሠራተኛ ጋር ማህበሩ በአንድነትና በተናጠል ተጠያቂ ይሆናል፡፡ ማህበሩ ጉዳት የደረሰበት አካል ጉዳት አድራሹ ሥልጣን ያልተሠጠው መሆኑን ያስረዳ እንደሆነ ከኃላፊነት ነፃ ይወጣል፡፡ ማህበሩ ይህን መሠል ዕዳዎች ለመሸፈን የመድን ሽፋን እንዲኖረው በህግ ይገደዳል፡፡
3.3 አባል ከማህበሩ ስለሚወጣበት መንገድ እና ስለማህበሩ መፍረስ
አንድ አባል ከማህበሩ ሊወጣ የሚችለው የሶስት ወር ቅድመ ማስጠንቀቂያ በመስጠት (ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ) ፣ ሲሞት ወይም ህጋዊ ሰውነት ሲያጣ ፣ ድርሻው በገንዘብ ጠያቂዎች ሲወሰድ ፣ የሞያ ፈቃዱ ሲሰረዝ ወይም ለረጅም ጊዜ ሲታገድ፣ በሕመም ወይም አካል ጉድለት ወይም ሌሎች ምክንያቶች ግዴታውን ለመወጣት የማያስችለው ሲሆን ወይም ፍርድ ቤት በበቂ ምክንያት ከማህበሩ እንዲወጣ ሲወስን ነው፡፡ አንድ ሸሪክ ከማህበሩ ከመውጣቱ በፊት ለሶስተኛ ወገኖች የነበረበት ዕዳ ኃላፊነት ከማህበሩ በመውጣቱ ቀሪ አይሆንም ፡፡
አንድ ሽሪክ ድርሻውን በሌሎች ማህበርተኞች ተቀባይነት ላገኘ ሌላ ማህበርተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሳያስተላልፍ የወጣ እንደሆነ ህጋዊ መብት ያለው ወራሽ ወይም ባለመብት ድርሻው ተሰልቶ እንዲሰጠው ከመጠየቅ ውጪ አባል ለመሆን የሚያቀርበው ጥያቄ ተቀባይነት የለውም፡፡
በንግድ ሕግ ቁጥር 181 ንግድ ማህበራት ከሚፈርሱበት ሁኔታ በተጨማሪ የማህበሩ አባላት ቁጥር ወደ አንድ ዝቅ ያለ እንደሆነ እና በስድስት ወራት አሊያም ዘጠኝ ወራት ውስጥ ወደ ሁለት ከፍ ካላለ ማህበሩ ሊፈርስ ይገባል።
Abeje Kassahun Adamu
በይርጋ የማይታገዱ የፍትሀብሄር ጉዳዬች
🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑♨️♨️♨️
የይርጋ መሰረታዊ ዓላማ ማንኛውም በህግ በግልፅ የተደነገገ መብትና ግዴታ በህጉ በተወሰነው ወይም በተገደበው ጊዜ ውስጥ ስልጣን ላለው አካል እንዲቀርቡ ግዴታን በማስቀመጥ መብቴ ተጣሰብኝ የሚል ወገን ዳተኛ ሳይሆን በትጋት መብቱን እንዲጠይቅ ለማስቻል መሆኑ ይታወቃል።
ነገር ግን አንዳንድ ጉዳዬች ከንብረቶቹ ልዩ ባህሪና የመንግስት ፖሊሲ አንፃር ህግ አውጪው በይርጋ እንዳይታገዱ አድርጎ ያስቀመጣቸው የፍትሀብሄር ጉዳዬች አሉ። ከእነዚህ መካከል፦
#የመፋለም ክስ ( petitory action)
♨️♨️♨️🛑🛑🛑🛑♨️
ለባለሀብቱ የባለቤትነት መብት ከሚሰጣቸው መብቶች መካከል ንብረቱ ያለ እርሱ ፈቃድ ከህግ ውጪ በሌላ ሰው ወይም ሀይል ከተወሰደ ንብረቱን ካለበት ድረስ በመከታተል የማስመለስ ወይም የመፋለም መብት አንዱ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 ድንጋጌ ያስረዳል፡፡
ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን” በሚል ርዕስ ስር በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1192 የተመለከተው በሚንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት በአስር ዓመት የጊዜ ወሰን /ይርጋ/ ቀሪ የሚሆንበትን አግባብ ያመላከተ ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን ግን አያሳይም፡፡
ድንጋጌው የሚንቀሳቀስ ንብረትን የባለሀብትነት ጥያቄ የጊዜ ገደብ ካስቀመጠ በኋላ ስለማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት ቀሪ መሆን በዝምታ ያለፈው ለጉዳዩ ቀጥተኛ ተፈፃሚነት በሌለው በፍ/ብ/ህግ አንቀፅ 1845 ስር የተመለከተው ተመሳሳይ የ10 ዓመት የይርጋ ጊዜ ተፈፃሚ እንደሆን ተፈልጎ ካለመሆኑ በላይ የማይንቀሳቀስ ንብረት ከሚንቀሳቀስ ንብረት በተለየ ሁኔታ የዘላቂነት ባህሪ ያለው እና ከትውልው ወደ ትውልድ የሚተላለፍ በመሆኑ የባለሀብትነቱ መብት ቀሪ የሚሆነው በይርጋ ሳይሆን በሌሎች ሁኔታዎች( አንቀፅ 1168....) ይሆን ዘንድ ተፈልጎ የተቀመጠ ድንጋጌ መሆኑን እንገነዘባለን።
በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረት የመፋለም ክስ (petitory action) በይርጋ ቀሪ አይሆንም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰ/መዝ/ቁ 43600)
N.B= ይህ ሲባል ግን ከውርስ፣ ከሽያጭ፣ ከስጦታና ከሌሎች ውሎች በመነጨ በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የሚደረግ ክርክር ይርጋ የለውም ማለት የሚቻል ሳይሆን ለጉዳዩ አግባብነት ባላቸው ህጎች በተቀመጡ የይርጋ ጊዜዎች የሚስተናገዱ ይሆናል።
#ህገ ወጥ ውል (unlawful contrat)
♨️🛑🛑🛑🛑♨️♨️♨️🛑
እንድ ውል የፀና ውል ለመሆን መሟላት ከሚገባው አንዱ ነጥብ ውሉ ህጋዊ በሆነ ጉዳይ ላይ የተመሰረተ መሆን የሚገባው እንደሆነ የፍ/ብ/ህግ 1678 ይደነግጋል። አንድ ውል ህገ ወጥ ውል ነው የሚባለው ደግሞ ተዋዋዬቹ የተዋዋሉበት መሰረታዊ ጉዳይ ዓላማ በመሰረታዊና ሞራላዊ ይዘቱ ተዋዋይ ወገኖች ስምምነት በማድረግ መብትና ግዴታ እንዲፈጥሩበት በህግ ያልተፈቀደ ወይም በህግ ክልከላ የተደረገበት ሆኖ ሲገኝ ነው።
አንድ ውል የተመሰረተበት መሰረታዊ ጉዳይ (object of contract) በህግ ክልከላ የተደረረበት በሆነ ጊዜ ውሉ በህግ ፊት እንደሌለና ምንም አይነት ህጋዊ ውጤት የማያስከትል (null and void contrat) እንዲሁም ችግሩን በማስተካከል ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው ማድረግ የማይቻል ነው። ለምሳሌ፦ የመሬት ሽያጭ ውል፣ በሰው ለመነገድ የተደረግ ውል፣ ወንጀል ለመፈፀም የተደረገ ውል......
ህገ ወጥ የሆነውን ውል ውድቅ ለማድረግ ደግሞ በህጉ የተደነገገው የይርጋ ጊዜ ገደብ መቃወሚያ ሊቀርብ የማይችልና ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ በይርጋ የሚታገዱ አይደሉም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት/ሰ/መዝ/ቁ 43226)
N.B= ይህ ሲባል ግን የህጉን መስፈርት ያላሟሉ ውሎች (illegal contract) ከህገ ወጥ ውል በተለየ ሁኔታ ታይተው የይርጋ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ የሚሆንባቸው መሆኑን መረዳት ይገባል።
#የመንግስትን መሬት የማስመለስ ክስ
♨️♨️🛑🛑🛑♨️♨️🛑
ግለሰቦች በፌደራሉ እና በክልሉ መንግስት በወጡ የገጠር መሬት አጠቃቀም እና አስተዳደር አዋጅ በሚደነግጉት መሰረት በህጋዊ መንገድ ሳይሰጣቸው ከህግ ውጪ የወል ወይም የመንግስትን መሬት ይዘው መቆየታቸው እና የመሬቱ ባለይዞታ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ማግኘታቸው የመሬቱ ህጋዊ ባለይዞታ ሊያደርጋቸው አይችልም። በወረራ የተያዘ የመንግስት መሬትም ይርጋ የሌለው መሆኑን የአብክመ የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 በግልፅ ያስቀምጣል።
በመሆኑም ከህግ ውጭ በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ መሬቶችን መኖራቸውን ሲረዳ መሬት አስተዳደርም ሆነ የመንግስት ወኪል የሆነ አካል መሬቶቹን ለማስመለስ የሚያቀርበው ክስ በይርጋ የሚታገድ አይደለም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት/ሰ/መዝ/ቁ 93013 እና 96203 ያልታተሙ)
#በህገ ወጥ መንገድ የተያዘ የግለሰብ ይዞ መሬት
🛑🛑🛑🛑🛑🛑♨️♨️
ከላይ እንደተመለከትነው ህገ ወጥ ውልን መሰረት አድርጎ የግለሰብን መሬት በያዘ ሰው ላይ የሚቀርብ ክስ ይርጋ የሌለው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በአብክመ የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 መሰረት ህጉ በማይፈቅድበት መንገድ በሀይልም ሆነ በህገ ወጥ አግባብ የገጠር መሬትን ይዞ የተገኘ ግለሰብ ላይ የሚቀርብ ክስ ይርጋ የለውም።
N.B= በህገ ወጥ መንገድ የሚለው ሀሳብ በህግ ተቀባይነት በሌለው አኳኋን የያዘን በሚመለከት እንጂ የህጉን መስፈርት ባላሟላ ውል ወይም ተግባር (illegal contrat) አማካኝነት የተያዘን መሬት የሚመለከት አይደለም። ምክንያቱም መሬቱን የያዘው በህጉ በተፈቀደ የውል ተግባር ሆኖ የሚፈለገውን ፎርማሊቲ ወይም መስፈርት አለማለቱ ብቻ አያያዙ ህገ ወጥ ነው የሚያስብል ስላልሆነ ነው።
#የአደራ ውል
🛑🛑🛑🛑♨️♨️
አደራ ተቀባይ በአደራ የሚጠብቀውን ዕቃ የሚመልስበት የጊዜ ገደብ በውል ተመልክቶ ከሆነ ይህ ጊዜ ሲያበቃ ዕቃውን መመለስ ያለበት ስለመሆኑ በፍ/ብ/ህ/ቁ 2781(1) የተመለከተ ሲሆን በውል ላይ የተቀመጠ የጊዜ ገደብ ከሌለ ግን አደራ ሰጪው እንደጠየቀ ወዲያውኑ እንደሚመለስ በፍ/ብ/ህ/ቁ 2989(1) ስር ተመላክቷል።
ከእነዚህ ድንጋጌዎች ለመረዳት የሚቻለው አደራ ተቀባይ ዕቃውን የሚመልስበት የጊዜ ገደብ ከሌለ በቀር አደራ ሰጪው በአደራ እንዲቀመጥ የሰጠው ዕቃ ያለምንም የጊዜ ገደብ በማንኛውም ጊዜ እንዲመለስለት መጠየቅ የሚችል መሆኑን ነው።
#የውርስ ሀብት ክፍፍል
🛑♨️♨️♨️♨️🛑
ወራሾች ተለይተው እና የውርስ ሀብቱ ድርሻ ታውቆ ነገር ግን ክፍፍል ሳይደረግ የቆየን የውርስ ሀብት በማናቸውም ጊዜ መጠየቅ እንደሚችልና በይርጋ የሚታገድ እንዳልሆነ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1060 እና ተከታዬቹ ድንጋጌዎች መረዳት ይቻላል።
እንዲሁም ከውርስ ሀብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የውርስ ሀብቱን በእጁ አድርጎ በመገልገል ላይ ያለ ተከራካሪ የሆነ ወራሽ ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን የውርስ ንብረት በጋራ ይዞ ከቆየ ሰው ላይ የውርስ ድርሻዬን ልወቅ ወይም ይለይልኝ ጥያቄ በይርጋ ይታገዳል የሚባልበት አግባብ የለም።
#ሄኖክ ታየ
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑♨️♨️♨️
የይርጋ መሰረታዊ ዓላማ ማንኛውም በህግ በግልፅ የተደነገገ መብትና ግዴታ በህጉ በተወሰነው ወይም በተገደበው ጊዜ ውስጥ ስልጣን ላለው አካል እንዲቀርቡ ግዴታን በማስቀመጥ መብቴ ተጣሰብኝ የሚል ወገን ዳተኛ ሳይሆን በትጋት መብቱን እንዲጠይቅ ለማስቻል መሆኑ ይታወቃል።
ነገር ግን አንዳንድ ጉዳዬች ከንብረቶቹ ልዩ ባህሪና የመንግስት ፖሊሲ አንፃር ህግ አውጪው በይርጋ እንዳይታገዱ አድርጎ ያስቀመጣቸው የፍትሀብሄር ጉዳዬች አሉ። ከእነዚህ መካከል፦
#የመፋለም ክስ ( petitory action)
♨️♨️♨️🛑🛑🛑🛑♨️
ለባለሀብቱ የባለቤትነት መብት ከሚሰጣቸው መብቶች መካከል ንብረቱ ያለ እርሱ ፈቃድ ከህግ ውጪ በሌላ ሰው ወይም ሀይል ከተወሰደ ንብረቱን ካለበት ድረስ በመከታተል የማስመለስ ወይም የመፋለም መብት አንዱ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 ድንጋጌ ያስረዳል፡፡
ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን” በሚል ርዕስ ስር በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1192 የተመለከተው በሚንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት በአስር ዓመት የጊዜ ወሰን /ይርጋ/ ቀሪ የሚሆንበትን አግባብ ያመላከተ ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን ግን አያሳይም፡፡
ድንጋጌው የሚንቀሳቀስ ንብረትን የባለሀብትነት ጥያቄ የጊዜ ገደብ ካስቀመጠ በኋላ ስለማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት ቀሪ መሆን በዝምታ ያለፈው ለጉዳዩ ቀጥተኛ ተፈፃሚነት በሌለው በፍ/ብ/ህግ አንቀፅ 1845 ስር የተመለከተው ተመሳሳይ የ10 ዓመት የይርጋ ጊዜ ተፈፃሚ እንደሆን ተፈልጎ ካለመሆኑ በላይ የማይንቀሳቀስ ንብረት ከሚንቀሳቀስ ንብረት በተለየ ሁኔታ የዘላቂነት ባህሪ ያለው እና ከትውልው ወደ ትውልድ የሚተላለፍ በመሆኑ የባለሀብትነቱ መብት ቀሪ የሚሆነው በይርጋ ሳይሆን በሌሎች ሁኔታዎች( አንቀፅ 1168....) ይሆን ዘንድ ተፈልጎ የተቀመጠ ድንጋጌ መሆኑን እንገነዘባለን።
በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረት የመፋለም ክስ (petitory action) በይርጋ ቀሪ አይሆንም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰ/መዝ/ቁ 43600)
N.B= ይህ ሲባል ግን ከውርስ፣ ከሽያጭ፣ ከስጦታና ከሌሎች ውሎች በመነጨ በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የሚደረግ ክርክር ይርጋ የለውም ማለት የሚቻል ሳይሆን ለጉዳዩ አግባብነት ባላቸው ህጎች በተቀመጡ የይርጋ ጊዜዎች የሚስተናገዱ ይሆናል።
#ህገ ወጥ ውል (unlawful contrat)
♨️🛑🛑🛑🛑♨️♨️♨️🛑
እንድ ውል የፀና ውል ለመሆን መሟላት ከሚገባው አንዱ ነጥብ ውሉ ህጋዊ በሆነ ጉዳይ ላይ የተመሰረተ መሆን የሚገባው እንደሆነ የፍ/ብ/ህግ 1678 ይደነግጋል። አንድ ውል ህገ ወጥ ውል ነው የሚባለው ደግሞ ተዋዋዬቹ የተዋዋሉበት መሰረታዊ ጉዳይ ዓላማ በመሰረታዊና ሞራላዊ ይዘቱ ተዋዋይ ወገኖች ስምምነት በማድረግ መብትና ግዴታ እንዲፈጥሩበት በህግ ያልተፈቀደ ወይም በህግ ክልከላ የተደረገበት ሆኖ ሲገኝ ነው።
አንድ ውል የተመሰረተበት መሰረታዊ ጉዳይ (object of contract) በህግ ክልከላ የተደረረበት በሆነ ጊዜ ውሉ በህግ ፊት እንደሌለና ምንም አይነት ህጋዊ ውጤት የማያስከትል (null and void contrat) እንዲሁም ችግሩን በማስተካከል ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው ማድረግ የማይቻል ነው። ለምሳሌ፦ የመሬት ሽያጭ ውል፣ በሰው ለመነገድ የተደረግ ውል፣ ወንጀል ለመፈፀም የተደረገ ውል......
ህገ ወጥ የሆነውን ውል ውድቅ ለማድረግ ደግሞ በህጉ የተደነገገው የይርጋ ጊዜ ገደብ መቃወሚያ ሊቀርብ የማይችልና ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ በይርጋ የሚታገዱ አይደሉም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት/ሰ/መዝ/ቁ 43226)
N.B= ይህ ሲባል ግን የህጉን መስፈርት ያላሟሉ ውሎች (illegal contract) ከህገ ወጥ ውል በተለየ ሁኔታ ታይተው የይርጋ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ የሚሆንባቸው መሆኑን መረዳት ይገባል።
#የመንግስትን መሬት የማስመለስ ክስ
♨️♨️🛑🛑🛑♨️♨️🛑
ግለሰቦች በፌደራሉ እና በክልሉ መንግስት በወጡ የገጠር መሬት አጠቃቀም እና አስተዳደር አዋጅ በሚደነግጉት መሰረት በህጋዊ መንገድ ሳይሰጣቸው ከህግ ውጪ የወል ወይም የመንግስትን መሬት ይዘው መቆየታቸው እና የመሬቱ ባለይዞታ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ማግኘታቸው የመሬቱ ህጋዊ ባለይዞታ ሊያደርጋቸው አይችልም። በወረራ የተያዘ የመንግስት መሬትም ይርጋ የሌለው መሆኑን የአብክመ የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 በግልፅ ያስቀምጣል።
በመሆኑም ከህግ ውጭ በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ መሬቶችን መኖራቸውን ሲረዳ መሬት አስተዳደርም ሆነ የመንግስት ወኪል የሆነ አካል መሬቶቹን ለማስመለስ የሚያቀርበው ክስ በይርጋ የሚታገድ አይደለም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት/ሰ/መዝ/ቁ 93013 እና 96203 ያልታተሙ)
#በህገ ወጥ መንገድ የተያዘ የግለሰብ ይዞ መሬት
🛑🛑🛑🛑🛑🛑♨️♨️
ከላይ እንደተመለከትነው ህገ ወጥ ውልን መሰረት አድርጎ የግለሰብን መሬት በያዘ ሰው ላይ የሚቀርብ ክስ ይርጋ የሌለው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በአብክመ የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 መሰረት ህጉ በማይፈቅድበት መንገድ በሀይልም ሆነ በህገ ወጥ አግባብ የገጠር መሬትን ይዞ የተገኘ ግለሰብ ላይ የሚቀርብ ክስ ይርጋ የለውም።
N.B= በህገ ወጥ መንገድ የሚለው ሀሳብ በህግ ተቀባይነት በሌለው አኳኋን የያዘን በሚመለከት እንጂ የህጉን መስፈርት ባላሟላ ውል ወይም ተግባር (illegal contrat) አማካኝነት የተያዘን መሬት የሚመለከት አይደለም። ምክንያቱም መሬቱን የያዘው በህጉ በተፈቀደ የውል ተግባር ሆኖ የሚፈለገውን ፎርማሊቲ ወይም መስፈርት አለማለቱ ብቻ አያያዙ ህገ ወጥ ነው የሚያስብል ስላልሆነ ነው።
#የአደራ ውል
🛑🛑🛑🛑♨️♨️
አደራ ተቀባይ በአደራ የሚጠብቀውን ዕቃ የሚመልስበት የጊዜ ገደብ በውል ተመልክቶ ከሆነ ይህ ጊዜ ሲያበቃ ዕቃውን መመለስ ያለበት ስለመሆኑ በፍ/ብ/ህ/ቁ 2781(1) የተመለከተ ሲሆን በውል ላይ የተቀመጠ የጊዜ ገደብ ከሌለ ግን አደራ ሰጪው እንደጠየቀ ወዲያውኑ እንደሚመለስ በፍ/ብ/ህ/ቁ 2989(1) ስር ተመላክቷል።
ከእነዚህ ድንጋጌዎች ለመረዳት የሚቻለው አደራ ተቀባይ ዕቃውን የሚመልስበት የጊዜ ገደብ ከሌለ በቀር አደራ ሰጪው በአደራ እንዲቀመጥ የሰጠው ዕቃ ያለምንም የጊዜ ገደብ በማንኛውም ጊዜ እንዲመለስለት መጠየቅ የሚችል መሆኑን ነው።
#የውርስ ሀብት ክፍፍል
🛑♨️♨️♨️♨️🛑
ወራሾች ተለይተው እና የውርስ ሀብቱ ድርሻ ታውቆ ነገር ግን ክፍፍል ሳይደረግ የቆየን የውርስ ሀብት በማናቸውም ጊዜ መጠየቅ እንደሚችልና በይርጋ የሚታገድ እንዳልሆነ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1060 እና ተከታዬቹ ድንጋጌዎች መረዳት ይቻላል።
እንዲሁም ከውርስ ሀብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የውርስ ሀብቱን በእጁ አድርጎ በመገልገል ላይ ያለ ተከራካሪ የሆነ ወራሽ ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን የውርስ ንብረት በጋራ ይዞ ከቆየ ሰው ላይ የውርስ ድርሻዬን ልወቅ ወይም ይለይልኝ ጥያቄ በይርጋ ይታገዳል የሚባልበት አግባብ የለም።
#ሄኖክ ታየ
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
cassation decision 189201.pdf
4.3 MB
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ጉዲፈቻን አስመልክቶ የህግ ትርጉም ሰጠ
የፌዴራል ጠቅላይፍረድ ቤት 1ኛ ሰበር ችሎት መጋቢት 02 ቀን 2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት የውጭ ሃገር ጉዲፈቻን በተመለከተ የቀድሞ የቤተሰብ ህግ ደንጋጌን ያሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1070/2012 ላይ በመዝገብ ቁጥር 189201 አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡ ለዝርዝሩ ከዚህ መልዕክት ጋር የተያያዘውን የችሎት ውሳኔ ግልባጭ ያንብቡ፡፡
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የፌዴራል ጠቅላይፍረድ ቤት 1ኛ ሰበር ችሎት መጋቢት 02 ቀን 2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት የውጭ ሃገር ጉዲፈቻን በተመለከተ የቀድሞ የቤተሰብ ህግ ደንጋጌን ያሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1070/2012 ላይ በመዝገብ ቁጥር 189201 አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡ ለዝርዝሩ ከዚህ መልዕክት ጋር የተያያዘውን የችሎት ውሳኔ ግልባጭ ያንብቡ፡፡
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
ሰ-መ-ቁ 173079 ውሳኔ ግልባጭ.pdf
9.9 MB
እግድ እና የመያዣ ወይም የቅድሚያ መብት
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 173079 ከፍርድ በፊት የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረትን አስመልክቶ የሚሰጥ የእግድ ወይም ንብረት የማስከበር ትዕዛዝ የመያዣ መብትን የማያቋቁም በመሆኑ የቅድሚያ መብትን ሊፈጥር እንደማይችል አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
ይህ የህግ ትርጉም የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሰበር ሰሚ ችሎት ከዚህ በፊት በሰ/መ/ቁጥር 97206 እና በሰ/መ/ቁጥር 29269 በዚሁ ጉዳይ ላይ ሰጥቶት የነበረውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም አሻሽሏል ወይም ለውጧል፡፡
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 173079 ከፍርድ በፊት የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረትን አስመልክቶ የሚሰጥ የእግድ ወይም ንብረት የማስከበር ትዕዛዝ የመያዣ መብትን የማያቋቁም በመሆኑ የቅድሚያ መብትን ሊፈጥር እንደማይችል አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
ይህ የህግ ትርጉም የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሰበር ሰሚ ችሎት ከዚህ በፊት በሰ/መ/ቁጥር 97206 እና በሰ/መ/ቁጥር 29269 በዚሁ ጉዳይ ላይ ሰጥቶት የነበረውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም አሻሽሏል ወይም ለውጧል፡፡
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Legal Service Provider
Jhpiego
Ethiopia
Full–time
Terms of Reference Legal Service Provider Background Jhpiego, an affiliate of Johns Hopkins University, works to improve the health of women and families in limited-resource settings worldwide through strengthening the capacities of local institutions, systems, and facilitate in the health sector. Jhpiego is registered as International Non-Governmental Organization (iNGO) to operate in Ethiopia since 2003. Jhpiego Ethiopia is currently looking for a professional law firm or a lawyer able to provide legal services based on the contents of this Terms of Reference (TOR). Scope of Work The “Legal Advisor” or “Legal Firm” is expected to support Jhpiego Ethiopia on a broad range of issues, including but not limited to day-to-day legal responsibilities and providing legal advice that includes all aspects of the analysis, investigation and drafting processes. He/She is responsible for providing support in discrete legal issues by advising the organization, drafting undertakings, and structuring remedies for the relevant issues. This professional/firm may also be engaged in helping to analyze and collect evidence and schedule staff hearings. Some of the responsibilities will include, but are not limited to the following: • Renew the necessary certificate of registration and license for the Jhpiego Ethiopia Office. This will include notifying all relevant and applicable parties and taking all the necessary steps to finalize registration renewal, to follow-up and execute with all the relevant and applicable governmental and non-governmental bodies in Ethiopia,
• Renew certificate of registration and license, to submit reports and handle all matters that relate to the Societies and Charities Agency (ChSA),
• Handle the issuance and renewal of work and residence permits for expatriate staff,
• Handle the issuance of Tax Identification Number (TIN) and national staff and expatriate taxation compliance matters,
• Handle the duty-free importation of Jhpiego Corporation materials and equipment,
• Conduct legal analysis and research on various legal matters,
• Provide advice on different legal issues and assist in drafting legal opinions, memoranda and other documents,
• Be actively involved in preparing different acts and legal submissions and draft the authoritative legal opinions as well,
• Conduct legal research by utilizing various resources and selecting the relevant material to analyze the legal information,
• Assist in reviewing the legal material and any other relevant documents and to identify the most important issues that need to be sorted out on a priority basis, • Draw up formalities regarding the settlement of disputes and monitor the implementation of the legal clauses,
• Where and when duly authorized by Jhpiego, represent Jhpiego in legal matters including hearings,
• Render legal services to Jhpiego in the form of verbal or written legal opinions, briefs or advice,
• Handle other legal matters related to Jhpiego Corporation in Ethiopia upon written request from Jhpiego Corporation Country Director for Ethiopia.
• Review and provide any necessary recommendations regarding Jhpiego Employee Handbook, employment agreements payroll and contract termination to ensure compliance with local labor laws
• Regular legal advice to Jhpiego as needed
Job Requirements Qualifications
• At least MA degree in Law or equivalent field.
• Extensive 20 years’ experience working in the field.
• Experience working with similar INGOs. Work Schedule and payment mode Option 1
• Upon demand – Based on the standard hourly rates and the time necessary to complete the assignment required in a professional and timely manner. Option 2
• On retainer basis (monthly) Deliverables
• Written legal advice or recommendations,
• Report on legal advisory services provided,
• Update status of court appointments, hearing, ruling and related information in writing.
How to Apply
Jhpiego
Ethiopia
Full–time
Terms of Reference Legal Service Provider Background Jhpiego, an affiliate of Johns Hopkins University, works to improve the health of women and families in limited-resource settings worldwide through strengthening the capacities of local institutions, systems, and facilitate in the health sector. Jhpiego is registered as International Non-Governmental Organization (iNGO) to operate in Ethiopia since 2003. Jhpiego Ethiopia is currently looking for a professional law firm or a lawyer able to provide legal services based on the contents of this Terms of Reference (TOR). Scope of Work The “Legal Advisor” or “Legal Firm” is expected to support Jhpiego Ethiopia on a broad range of issues, including but not limited to day-to-day legal responsibilities and providing legal advice that includes all aspects of the analysis, investigation and drafting processes. He/She is responsible for providing support in discrete legal issues by advising the organization, drafting undertakings, and structuring remedies for the relevant issues. This professional/firm may also be engaged in helping to analyze and collect evidence and schedule staff hearings. Some of the responsibilities will include, but are not limited to the following: • Renew the necessary certificate of registration and license for the Jhpiego Ethiopia Office. This will include notifying all relevant and applicable parties and taking all the necessary steps to finalize registration renewal, to follow-up and execute with all the relevant and applicable governmental and non-governmental bodies in Ethiopia,
• Renew certificate of registration and license, to submit reports and handle all matters that relate to the Societies and Charities Agency (ChSA),
• Handle the issuance and renewal of work and residence permits for expatriate staff,
• Handle the issuance of Tax Identification Number (TIN) and national staff and expatriate taxation compliance matters,
• Handle the duty-free importation of Jhpiego Corporation materials and equipment,
• Conduct legal analysis and research on various legal matters,
• Provide advice on different legal issues and assist in drafting legal opinions, memoranda and other documents,
• Be actively involved in preparing different acts and legal submissions and draft the authoritative legal opinions as well,
• Conduct legal research by utilizing various resources and selecting the relevant material to analyze the legal information,
• Assist in reviewing the legal material and any other relevant documents and to identify the most important issues that need to be sorted out on a priority basis, • Draw up formalities regarding the settlement of disputes and monitor the implementation of the legal clauses,
• Where and when duly authorized by Jhpiego, represent Jhpiego in legal matters including hearings,
• Render legal services to Jhpiego in the form of verbal or written legal opinions, briefs or advice,
• Handle other legal matters related to Jhpiego Corporation in Ethiopia upon written request from Jhpiego Corporation Country Director for Ethiopia.
• Review and provide any necessary recommendations regarding Jhpiego Employee Handbook, employment agreements payroll and contract termination to ensure compliance with local labor laws
• Regular legal advice to Jhpiego as needed
Job Requirements Qualifications
• At least MA degree in Law or equivalent field.
• Extensive 20 years’ experience working in the field.
• Experience working with similar INGOs. Work Schedule and payment mode Option 1
• Upon demand – Based on the standard hourly rates and the time necessary to complete the assignment required in a professional and timely manner. Option 2
• On retainer basis (monthly) Deliverables
• Written legal advice or recommendations,
• Report on legal advisory services provided,
• Update status of court appointments, hearing, ruling and related information in writing.
How to Apply
While applying for this service provision, the individual/firm is required to submit a full technical and financial proposal separately through ET-Procurement@jhpiego.org . The Technical proposal should include CV with previous experience/qualification, including examples of previous similar experience and references. The financial proposal should include cost separately for both option 1 and 2. All government tax and related requirements will apply. The deadline for applications is October 24, 2021. Note: Please contact Kelemwork Messay at 0944109494 if you have any question.
Forwarded from Transparency International Ethiopia (TIE)
Corruption❌❌❌❌❌❌
dishonest or illegal behavior especially by powerful people (such as government officials or police officers)
: the act of corrupting someone or something
: something that has been changed from its original form
a : impairment of integrity, virtue, or moral principle : depravity
b : decay, decomposition
c : inducement to wrong by improper or unlawful means (as bribery)
d : a departure from the original or from what is pure or correct
From Merriam Webster
https://telegram.me/TransparencyEthiopia
dishonest or illegal behavior especially by powerful people (such as government officials or police officers)
: the act of corrupting someone or something
: something that has been changed from its original form
a : impairment of integrity, virtue, or moral principle : depravity
b : decay, decomposition
c : inducement to wrong by improper or unlawful means (as bribery)
d : a departure from the original or from what is pure or correct
From Merriam Webster
https://telegram.me/TransparencyEthiopia
Telegram
Transparency International Ethiopia (TIE)
Ethical and corruption free society that upholds integrity and accountability
Contact Us via
@Transparency_Ethiopia_Bot
and
ethiopiatransparency@gmail.com
Contact Us via
@Transparency_Ethiopia_Bot
and
ethiopiatransparency@gmail.com
Safaricom Telecom Ethiopia Vacancy Fresh Graduates - EffoySira
https://effoysira.com/2021/10/16/safaricom-telecom-ethiopia-vacancy-fresh-graduates/
https://effoysira.com/2021/10/16/safaricom-telecom-ethiopia-vacancy-fresh-graduates/
🚩 #ሞባይል_ዳታ ስናበራ የስልካችን እስክሪን አናት ላይ የምንመለከታቸው የ G ፣ E ፣ 3G ፣ H ፣ H+ ፣ 4G እና የ4G LTE ምልክቶች ትርጉም ምንድን ነው ?
እንደሚታወቀው ኢንተርኔት ለመጠቀም የሞባይል ስልካችንን ዳታ ስናበራ ከኔት-ወርክ ምልክት አጠገብ ሁልጊዜ ተጨማሪ ምልክቶች ይመጣሉ። ታዲያ እነዚህ ምልክቶች በምርጫችን የምንጠቀማቸውን የተለያዩ የዳታ አይነቶችን እና የኢንተርኔት ፍጥነት የሚያሳዩን ናቸው።
ምልክቶቹ እና መለኪያዎቹ እንደሚከተለው ነው።
~~~~~2G~~~~~~~~~
✅ የ2G ቤተሰብ(2G, G, E) 3ስቱ የሁለተኛው ትውልድ ወይም 2G(Generation) ይባላሉ።
~~~~Standard~~~~~~~~
1, 2G=GSM (Global Systems for Mobile Communication)
2, G=GPRS(General Packet Radio Service)
3, E=EDGE(Enhanced Data rates for GSM Evolution)
🔰 Maximum Download Speed ከፍተኛው የማውረድ አቅም
1, 2G=14.4kbps(Kilo Bite per second) ነው
2, G=53.6kbps(Kilo Bite per second) ነው
3, E=236.8kbps(Kilo Bite per second) ነው
🔰 Maximum Upload speed ከፍተኛው የመጫን አቅም
1, 2G=14.4kbps(Kilo Bite per second) ነው።
2, G=26.8kbps(Kilo Bite per second) ነው።
3, E=59.2kbps(Kilo Bite per second) ነው።
~~~~~3G~~~~~~~~~
✅ የ3G ቤተሰብ(3G, H, H+) 3ስቱ የሶስተኛው ትውልድ ወይም 3G(Generation) ይባላሉ።
~~~~Standard~~~~~~~~
1, 3G=UMTS(Universal Mobile Telecommunications Service)
2, H=HSPA(High Speed Packet Access)
3, H+=HPSA+(Evolved High Speed Packet Access)
🔰 Maximum Download Speed ከፍተኛው የማውረድ አቅም
1, 3G=384kbps(Kilo Bite per second) ነው
2, H=14.5mbps(Mega Bite per second) ነው
3, H+=168mbps(Mega Bite per second) ነው
🔰 Maximum Upload speed ከፍተኛው የመጫን አቅም
1, 3G=384kbps(Kilo Bite per second) ነው
2, H=5.76nbps(Mega Bite per second) ነው
3, H+=22mbps(Mega Bite per second) ነው
~~~~~4G~~~~~~~~~
✅ የ4=G ቤተሰብ(4G, 4G) 2ቱ የአራተኛው ትውልድ ወይም 4G(Generation) ይባላሉ።
~~~~Standard~~~~~~~~
1, 4G=LTE(Long-Term Evolution)
2, 4G=LTE-A(LTE-Advanced)
🔰 Maximum Download Speed ከፍተኛው የማውረድ አቅም
1, LTE=100mbps(Mega Bite per second) ነው
2, LTE-A=1gbps(Giga Bite per second) ነው
🔰 Maximum Upload speed ከፍተኛው የመጫን አቅም
1, LTE=50mbps(Mega Bite per second) ነው
2, LTE-A=500mbps(Mega Bite per second) ነው
እንዲሁም ከዚህ በፊት የለቀቅኳቸውን ቪዲዮዎችን ብትከታተሉ ምርጥ እውቀትን ልታገኙ ትችላላችሁ
አሁንም የቴሌግራምና የYouTube ቻናሌን Subscribe በማድረግ ድጋፋችሁን አሳዩኝ።
✅✅✅#ያወቁትን ማሳወቅ ብልህነት ነው!✅✅✅
via Muhammed Computer Technology
እንደሚታወቀው ኢንተርኔት ለመጠቀም የሞባይል ስልካችንን ዳታ ስናበራ ከኔት-ወርክ ምልክት አጠገብ ሁልጊዜ ተጨማሪ ምልክቶች ይመጣሉ። ታዲያ እነዚህ ምልክቶች በምርጫችን የምንጠቀማቸውን የተለያዩ የዳታ አይነቶችን እና የኢንተርኔት ፍጥነት የሚያሳዩን ናቸው።
ምልክቶቹ እና መለኪያዎቹ እንደሚከተለው ነው።
✅ የ2G ቤተሰብ(2G, G, E) 3ስቱ የሁለተኛው ትውልድ ወይም 2G(Generation) ይባላሉ።
1, 2G=GSM (Global Systems for Mobile Communication)
2, G=GPRS(General Packet Radio Service)
3, E=EDGE(Enhanced Data rates for GSM Evolution)
🔰 Maximum Download Speed ከፍተኛው የማውረድ አቅም
1, 2G=14.4kbps(Kilo Bite per second) ነው
2, G=53.6kbps(Kilo Bite per second) ነው
3, E=236.8kbps(Kilo Bite per second) ነው
🔰 Maximum Upload speed ከፍተኛው የመጫን አቅም
1, 2G=14.4kbps(Kilo Bite per second) ነው።
2, G=26.8kbps(Kilo Bite per second) ነው።
3, E=59.2kbps(Kilo Bite per second) ነው።
✅ የ3G ቤተሰብ(3G, H, H+) 3ስቱ የሶስተኛው ትውልድ ወይም 3G(Generation) ይባላሉ።
1, 3G=UMTS(Universal Mobile Telecommunications Service)
2, H=HSPA(High Speed Packet Access)
3, H+=HPSA+(Evolved High Speed Packet Access)
🔰 Maximum Download Speed ከፍተኛው የማውረድ አቅም
1, 3G=384kbps(Kilo Bite per second) ነው
2, H=14.5mbps(Mega Bite per second) ነው
3, H+=168mbps(Mega Bite per second) ነው
🔰 Maximum Upload speed ከፍተኛው የመጫን አቅም
1, 3G=384kbps(Kilo Bite per second) ነው
2, H=5.76nbps(Mega Bite per second) ነው
3, H+=22mbps(Mega Bite per second) ነው
✅ የ4=G ቤተሰብ(4G, 4G) 2ቱ የአራተኛው ትውልድ ወይም 4G(Generation) ይባላሉ።
1, 4G=LTE(Long-Term Evolution)
2, 4G=LTE-A(LTE-Advanced)
🔰 Maximum Download Speed ከፍተኛው የማውረድ አቅም
1, LTE=100mbps(Mega Bite per second) ነው
2, LTE-A=1gbps(Giga Bite per second) ነው
🔰 Maximum Upload speed ከፍተኛው የመጫን አቅም
1, LTE=50mbps(Mega Bite per second) ነው
2, LTE-A=500mbps(Mega Bite per second) ነው
እንዲሁም ከዚህ በፊት የለቀቅኳቸውን ቪዲዮዎችን ብትከታተሉ ምርጥ እውቀትን ልታገኙ ትችላላችሁ
አሁንም የቴሌግራምና የYouTube ቻናሌን Subscribe በማድረግ ድጋፋችሁን አሳዩኝ።
✅✅✅#ያወቁትን ማሳወቅ ብልህነት ነው!✅✅✅
via Muhammed Computer Technology