አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Live stream started
Live stream finished (22 minutes)
ይግባኝ ማስፈቀጃ/በህጉ የተቀመጠው የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ካለፈ በኋላ ይግባኝ ለማቅረብ እንዲፈቀድ የሚቀርብ አቤቱታ/
====================
አንድ ፍ/ቤት ይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜው ያለፈበት ምክንያት በቂ መሆኑን ሲረዳ ይግባኙ እንዲቅርብ ሊፈቅድ እንደሚገባ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 326/1/ ስር ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም ፍ/ቤቱ የቀረበለት ምክንያት በቂ መሆን አለመሆኑን በአግባቡ ሊመረምረው ይገባል፡፡ በእርግጥ በቂ ምክንያት የሚባሉት ነገሮች ሕጉ ዘርዝሮ ያላስቀመጣቸው በመሆኑ ለመወሰን አስቸጋሪ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በመሆኑም የምክንያቱ በቂ መሆን አለመሆን በእያንዳንዱ ጉዳይ ከሚቀርቡ ፍሬ ነገሮች ጋር ተገናዝበው ሊመዘኑ ይገባል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 38145 ቅጽ 8፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 326/1/
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 324/1/ መሠረት ለአንድ ፍርድ ቤት መዝገብ ሹም የተሰጠው ሥልጣን ይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ማለፍ አለማለፉን በመመልከት ይግባኝ መዝገቡ እንዲከፈት ማድረግ ሲሆን ይግባኙ ጊዜውን ጠብቆ ያልቀረበ ከሆነ ማመልከቻውን መመለስ፣ ማመልከቻው የተመለሰበት ወገን የይግባኝ ጊዜው ያለፈበት ሕጋዊ ምክንያት ካለው ማስፈቀጃ አቤቱታውን በማቅረብ ይኸው ጊዜው ያለፈበት ይግባኝ ለማቅረብ እንዲፈቀድለት ራሱን የቻለ አቤቱታ አቅርቦና ይህ መዝገብ ተከፍቶ ጉዳዩ ለችሎት ቀርቦ ችሎቱ የይግባኝ ማስፈቀጃውን በመመርመር በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 325 እና 326 መሠረት ተገቢ ነው ያለውን ትእዛዝ የሚሰጥበት ነው፡፡
የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 324/1/ ከፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 325 እና 326 ድንጋጌዎች ጋር አንድ ላይ ሲነበቡ የመዝገብ ቤት ሹም ጊዜው ያለፈበት ይግባኝ ለችሎት እንዲቀርብ የመፍቀድ ስልጣን የሌለው መሆኑን የሚያሳዩ ሲሆን ፋይሉ ተከፍቶ ቀርቦ ከሆነም ችሎቱ ጉዳዩን መርምሮ ይግባኙ የቀረበው ጊዜው ከአለፈ በኋላ ነው በማለት መዝገቡን ከመዝጋት የሚከለክለው አይደለም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 61843 ቅጽ 11፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 324-326
🔵Urgent reminding notice♨️♨️
🔴 Dear Ethiopians........⁉️⁉️⁉️
You came naked,
You will go naked.
You arrived weak,
You will leave weak.
You came without money and things,
You will leave forever without money and things.
Your first bath, Someone washed you,
Your last bath, Someone will wash you.

🩸This is life‼️‼️‼️‼️‼️

So why so much malice, so much envy, so much hate, so much resentment, so much selfishness and so much pride⁉️ why, when we have to go empty handed⁉️

BE KIND…........We have limited time on Earth don’t waste it in uselessness.🩸🩸🩸🩸🩸🩸
share share
#share #Share
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Attorney
#abay_insurance_s_c
#legal_services
#law
#attorney
Addis Ababa
LLB degree in Law or related fields of studies with relevant work experience
Competence:-
- Special training; Competence in MS Office
- Very high customer Orientation
- Excellent interpersonal communication skill,
- High coordination skill & proactive personality
- Detail orientation & analytical skill
- Excellent English language skill
Minimum Years Of Experience: #1_years
Deadline: July 27, 2021
How To Apply: Send your CV & relevant documents via: geneta@abayinsurancesharecompany.com or in person at Abay Insurance S.C Office, located from Urael Church on the way to Bole Atlas area, near to Atlas traffic light, to the Head office 4th floor, room no. 405 For further information contact Tel. 0116663332
Forwarded from ሕግ ቤት
charge case.docx
11.4 KB
የወንጀል ክስ ፎርም በEnglish version Hypothetical case.
@EthiopianLawStudentsUnion
via about law
attorny general regulatin.doc
433 KB
የደቡብ ክልል አቃቢያን መተዳደሪያ ደንብ
ማስታወቂያ ለ5ኛ አመት የ Exit Exam ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ‼️
ፈተናው ይራዘም እያሉ ከዚህም ከዚያም መረጃወችን የሚያንሸራሽራሩ እና ተፈታኞ ተረጋግተው ለፈተና እራሳቸውን እንዳያዘጋጁ ከንቱ ተስፋ ሰንቀው የቴሌግራም ግሩፕ ከፍተው ተፈታኞችን የሚያደናግሩ እንዳሉ እየገለፅን።
ምንም አዲስ ነገር የሌለ በመሆኑ ተረጋግታችሁ ተዘጋጁ፤
ማንኛውም ጥያቄ እና ብዥታ ቢኖር ትክክለኛ የሚመለከተውን ሰው በመጠየቅ እና የዚሁ ቻናል አካል በሆነው @ALE_lawsocieties ላይ በመጠየቅ ትክክለኛ የሚመለከታቸውን ሰዎች ማግኘት ትችላላችሁ።
ተዋክበው ለሚያዋክቡ እራሳችሁን አታጋልጡ።
ሁሌም በእየ አመቱ እንዲህ አይነት ወከባ በመፍጠር የግል ቴሌግራም ግሩፕ አድማቂ ከማድረግ የዘለለ ምንም መፍጠር እና መቀየር የማይችሉ እና ምንም አይነት ውክልና ሳይኖራቸው በግላቸው ተነሳሽነት የግላቸው አጀንዳ ለመፈፀም petition እናሰባስብ 5th year እንዲሁ ቅሬታ Appeal እና መሰል ማሰሚያ በሚል ይቀሳቀሳሉ።
በጣም የግል ቴሌግራም ግሩፕ አባላት (አድማቂ) እንዲበዙላቸው ከመጓጓታቸው የተነሳ ያልተፈጠረ ያልተለወጠ፤ ያልተወሰነን ምንም በሌለበት አዲስ መረጃ አገኘን እንደገና አሳሳቢ ጉዳይ ምናምን እያሉ የብዙሀኑ ጥያቄ እና ፍላጎት በማስመሰል መረጃ በማሰራጨት
ተማሪዎችን ያዘናጋሉ።
የሚመለከተው የመንግስት ክፍል ለሁሉም አራቱም አቅጣጫ ለሚገኙ የሀገሪቱ ተማሪዎች አስፈላጊውን ጠቃሚ የሚለውን ሁኔታ ከህግ ት/ት ቤቱ ሄዶች እና ዲኖች መረጃ በመሰብሰብ እና በጋራ በመወያያት ማለትም በመጨረሻ ከሁሉም የኒቨርሲቲ ከህግ ት/ት የተውጣጡ ሄዶች እና ዲኖች በኮንሰርቲዬም ስብሰባ የሚወሰን ሲሆን እንድታውቁ እንላለን።
🔴ቅሬታ ጥያቄ ካለ ለህግ ት/ትቤታችሁ ሄድ ወይም ዲን ማቅረብ ነው ስርዓቱ።
🔵አዲስ ነገር ከህግ ት/ትቤታችሁ ሄድ ወይም ዲን መጠየቅ ነው ትክክለኛው።
በተረፈ በዚህ ቻናል የሚለቁቁ መረጃዎችን ተከታተሉ።
ተረጋግታችሁ ተዘጋጁ‼️
via Eta.B. Addis Ababa
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Babu:
Gys let me tell you one thing there are some student, who don't want to exit, to be extended ena they are confusing us, pleas brothers and sisters don't be confused. We are not sure, exit may extended or may not so please study hard and wait for us.

ስታጠኑ exit እንደማይራዘም አድርጋችሁ አጥኑ or ይራዘማል የሚለው ከአእምሮቹህ አውጡት እና አጥኑ። እኛ የተቻለንን ነው የምናደርገው። Study hard💪💪
ስለአዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013፡- አንዳንድ ምልከታዎች
1. የአዋጁ መልካም ጎኖች፡-
1.1. የተለያዩ አዋጆችን አንድ ላይ አጠቃልሎ/consolidated/ ለአጠቃቀም ምቹ ማድረጉ፣
1.2. በፍርድ ሊወሰኑ በሚችሉ ጉዳዮችና በሕገ መንግስታዊ መብቶች ላይ ፍርድ ቤቶች ስልጣን ያላቸው መሆኑን ግልጽ ለማድረግ ጥረት ማድረጉ፣
1.3. ስለመሰረታዊ የሕግ ስህተት አመላካች ሊባሉ የሚችሉ መስፈርቶችን ማስቀመጡ፣
1.4. የክልል ጉዳዮች ወደ ሰበር ችሎቱ ሊመጡ የሚችሉበትን አግባብ/መንገድ/ ለማጥበብ መሞከሩ፣
1.5. የሰበር ችሎት ውሳኔ አስገዳጅነት የሚጀምርበትን ጊዜ ማሳየቱ (ባይታተምም)፣
1.6. የሰበር ችሎት ውሳኔ የሚቀየርበትን ስርዓት የሕግ ማዕቀፍ እንዲኖረው ማድረጉ፣
1.7. የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትና የከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶችን የስረ ነገር ስልጣን መጨመሩ፣
1.8. የአለም አቀፍ ድርጅቶች በፍትሃ ብሔር ሊከሰሱ የሚችሉበት አግባብ ካለ ክስ ሊቀርብባቸው እንደሚችል የሚያሳይ ድንጋጌ መያዙ፣
1.9. ፍርድ ቤቶቹ በበጀትና በድጋፍ ሰራተኞች አስተዳደር ረገድ ነጻነት እንዲኖራቸው ማስቻሉ፣
1.10. ከዳኝነት አገልግሎት አስጣጥ ጋር በተያያዘ አጋዥ መመሪያዎች ሊወጡ የሚሉበትን አግባብ መደንገጉና እንደ አስማሚ መርና የጉዳዮች ፍስት አስተዳደር ያሉትን አዳዲስ ሀሳቦችን ማካተቱ፣
1.11. ከዳኞች ከችሎት የመነሳትና ከውሳኔዎች/ትዕዛዛት አፈጻጸም ጋር ተያይዞ አስተማሪ ቅጣቶች ሊጣሉ የሚችሉበትን አግባብ የሚያሳዩ ድንጋጌዎችን መያዙ……ወዘተ ተጠቃሽ ናቸው፡፡

2. የአዋጁ ውስን ድክመቶች
2.1. መግቢያው ላይ ስለአዋጁ ዓላማዎች ሲዘረዝር የፌዴራል ጉዳዮችን ለመለየት ብሎ ያለመጥቀሱ፣(አዋጅ ቁጥር 25/88 ግን ይህንኑ በመግቢያው ላይ ይገለጽና አዲሱ አዋጅ የያዛቸውን ሌሎች ነጥቦችን አይጠቅስም ነበር (ቁንፅል መግቢያ ይዞ ነበር)፣
2.2. የአርትኦት ስራ ግድፈት መኖሩ- የአማርኛም ሆነ የእንግሊዝኛ ፊደላት እና ስርዓተ ነጥብ አጠቃቀም ችግሮች መኖራቸው
ለምሳሌ፡-
o የአማርኛ ስርዓተ ነጥብ የሆነው ነጠላ ሰርዝ በብዙ ቦታዎች ከቃላት እንዲርቅ መደረጉ፣ ባንዳንድ ቦታዎች ደግሞ በነጠላ ሰረዙና በቀጣዩ ቃል ወይም ሐረግ መካከል ክፍተት/ስፔስ/ ሳይኖረው መቅረቱ፣ በቃላት ወይም በሐረጎች መካከልም ስፔስ መኖር ሲገባው መታለፉ፣
o ፌዴራል የሚለው ቃል በብዙ ቦታዎች(ምሳሌ በአንቀጽ 3(1) ፣ አንቀጽ 4 የመጀመሪያው ፓራግራፍ፣ በዚሁ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 16 ”ዴ“ ከተባለ በኋላ በሌሎች በርካታ ድንጋጌዎች ስር በፊደል ”ደ“ መተካቱ፣ በብዙ አዋጆች የነጋሪት ጋዜጣ ስያሜም ሆነ ተቋማት ስም ሲገለጽ ፌዴራል የሚል እንጂ ፌደራል የሚል ሁኖ አይታይም፣
o አንቀጽ 3 (2) ስር ድንጋጌዎች መባል ሲገባው ደንጋጌወች ተብሎ መታለፉ፣
o በአዋጁ አንቀጽ 5(1(ደ)) ስር ወሳኝ ኩነት የሚለውን ሐረግ ወደ እንግሊዝኛ ሲተርጉም Critical Event ( ስለወሳኝ ኩነቶች የሚደነግገውን አዋጅ ቁጥር 760/2004 እንኳን ባለማገናዘብ (Vital Events)) ብሎ ማስቀመጡ፣
o በአንዳንድ ድንጋጌዎች ስር ፍርድ ቤቶች የሚለውን ቃል በፍ/ቤቶች መተካቱ (አዋጅ ላይ አሳጥሮ መፃፍ ተገቢነት የሌለው ከመሆኑም በላይ ወጥነት ያለመኖር)፣ ለምሳሌ በአዋጁ አንቀጽ 17(1(ተ))፣ በአንቀጽ 37(1)(2)(4)
o በአዋጁ አንቀጽ 5(1(ደ)) እቁብ የሚለውን ቃል association በሚል መተርጎሙ(እቁብ በፈረንጅ አገር የሚታወቅ አይመስለኝም፣ አገር በቀል ማህበራዊ ተቋም ስለሆነ እንዳለ ቃሉን Equb ብሎ በአዋጁ ማስቀመጥ የማይቻልበት አግባብ አለ ብዬ ስላላስብኩ)፣
o በጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር ስለሚኖሩ ችሎቶች ሲደነግግ(አንቀጽ 25) የፍትሃ ብሔርና የወንጀል የመጀመሪያ ደረጃ ችሎቶች እንዲሚኖሩት መግለጹ በአዋጁ አንቀጽ 8 ስር ከተደነገገው ጋር የማይጣጣም መሆኑ(ፍርድ ቤቱ በመጀመሪያ ደረጃ ያለው ብቸኛው ስልጣን ከስልጣን ይለይልኝ ጋር የተያያዘ ነው)፡፡ በዚህ ረገድ የሚቀርቡ ጥያቄዎች ደግሞ በጣም ውስን( እንዲያውም የማይቀርቡበት የበጀት አመትም ነበር) ስለሆነ ለእነዚህ ጉዳዮች ብሎ የመጀመሪያ ደረጃ ስልጣን ያለውን ችሎት ማደራጀት የሰው ሃይልን ብክነት ያስከትላል፣(ምናልባት ይህ አባባል በአዋጁ እንዲስፍር የተደረገው ከዚህ በፊት የነበረውን አዋጅ በመቅዳት ሂደት በተፈጸመ ስህተት ወይም ስልጣን ይለይልኝ የሚለው ጉዳይ ስላለ ከዚሁ ጋር ተያይዞ ሊከሰት የሚችለውን ብዥታ ለማስወገድ ሊሆን ይችላል)፣
o በአዋጁ አንቀጽ 23 (1(ሐ)) ስር መጨረሻ ላይ ….13241… የሚለው ቁጥር ያለምክንያት ገብቶ መታተሙ፣
o በአዋጁ አንቀጽ 4(16) ስር በአማርኛው ቅጅ የማስረጃ ሕግ የሚለው ሐረግ በእንግሊዝኛው ቅጅ Procedure Code በሚል የተተረጎመ ሁኖ መታየቱ፣ በዚሁ ድንጋጌ ስር በእንግሊዝኛው ትርጉም ውስጥ የመጀመሪያው ዐርፍተ ነገር ከአለቀ በኃላ አዲስ በሚጀምረው ዐረፍተ ነገር ውስጥ other የሚለው ቃል በ“ካፒታል” O መጀመር ሲገባው በ”ስሞል“ o መጀመሩ፣ እንዲሁም In addition to የሚለው ቃል አርፍተ ነገሩ ባላለቀበት ሁኔታ I በካፒታል ሌተር መጻፏ፣
o በአንዳንድ አንቀጾች ስር ፊደሉ ”ስ ” መሆን ሲገባው ”ሰ“ ተብሎ መጻፉ(ለምሳሌ በአንቀጽ 19(1( ረ)) ስር ….ሰለተፈጻሚነቱም… በሚለው ቃል ስር ያለው፣ በአንቀጽ 36(2) ስር ….ማሰገባት…. የሚለው ቃል፣በአንቀጽ 47(4) …እሰከ…. ፣ በአንቀጽ 55(2) ስር …ለማሰፈጸም… የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
o በአዋጁ አንቀጽ 53 ስር በአማርኛው ቅጅ …ባለሙያዎች… መባል ሲገባው ….ባለሙያወች… መባሉ፣
o በአዋጁ አንቀጽ 50 ስር ቴክኖሎጂ መባል ሲገባው ቴክኖሎጅ መባሉ፣
o በአዋጁ አንቀጽ 26(3) ስር የክልል የሚለው የአማርኛ ቅጅ በእንግሊዝኛው reginal በሚል መተርጎሙ፣
o በአዋጁ አንቀጽ 25(3) ስር በብዙ ቁጥር አገላለጽ በሚገኙ እያለ ማንኛውም ችሎት ብሎ በነጣለ ማስቀመጡ፣
o በአዋጁ አንቀጽ 27(2) ስር የአማርኛው ቅጅ የስር ፍርድ ቤት መዝገብን ሰበር ችሎቱ ማስቀረብ እንደሚችል ሲገልጽ መዝገቡን የሚያስቀርበው በራሱ በኩል መሆኑን በሚያስገነዝብ መልኩ ደንግጎ እያለ በእንግሊዝኛው ቅጂ ግን ችሎቱ መዝቡን የሚያስቀርበው በተከራካሪ ወገኖች በኩልም ሊሆን እንሚችል መደንገጉ፣
o በአንዳንድ አንቀጾች የፍርድ ቤቶቹን ስያሜ በእንግሊዝኛ ሲጠቅስ የመጀመሪያ ፊደላትን ካፒታላይዝ ለምሳሌ በትልቅ ፊደላት/capital letters/ Federal High Court ይልና ትንሽ ቆይቶ ደግሞ በትንሽ ፊደላት(Small) federal high court ብሎ ማስቀመጡ(ምንም እንኳን መሰረታዊ ባይሆንም ወጥነት የሌለው የስም አገላለጽ በመሆኑ ተገቢነት የለውም..)፣
o በአዋጁ አንቀጽ 34(5) ስር የአማርኛው ቅጅ ቀናት ማለት ሲገባው ቀን ብሎ ጠቅሶ ካለፈ በኋላ የእንግሊዝኛው ቅጅ days ብሎ መተርጎሙ፣
o በአንዳንድ ድንጋጌዎች ስር የአማርኛ ቅጂው ላይ ቁጥር ሲኖር ቁጥሩ በኢትዮጵያ(በግዕዝ) አኃዝ እየተቀመጠ ከሄደ በኋላ በአንዳንድ ድንጋጌዎች ደግሞ በፊደል ብቻ የተቀመጠ ሁኖ መገኘት(ለምሳሌ አንቀጽ 52)፣
o በአዋጁ አንቀጽ 53(3) የአማርኛው እና የእንግሊዝኛው ቅጅ የማይጣጣሙ መመስል፣ የአማርኛው ቅጅ እያንዳንዱ የአማካሪ ምክር ቤቱ አባል በግል ደረጃ ኃላፊነቱን ሲወጣ ስለሚኖረው ግዴታ የሚያውጅ የሚመስል ሲሆን የእንግሊዝኛው ቅጅ ግን አማካሪ ምክር ቤቱ እንደተቋም ያለበትን ግዴታ የሚያሳስብ ይመስላል፣
o በአንቀጽ 35(2) ስር የቅጣቱን መጠን ከ፩ሺህ እስከ፫ሺህ ብሎ አስቀምጦ እያለ እና ይህ አገላለጽ መነሻውንና ጣሪያውን የሚያሳይ ሁኖ እያለ በድጋሚ በአርፍተ ነገር ከአንድ ሺህ ብር ያላነሰ ከሶስት ሺህ ብር ያልበለጠ ማለቱ እንዲሁም ከ፫ሺህ እስከ ፯ሺህ የሚለውንም ከሶስት ሺህ ብር ያላነሰ ከሰባት ሺህ ያልበለጠ ብሎ አላስፈላጊ በሆነ አገላለጽ መጠቀሙ፣ በዚሁ ድንጋጌ ስር በቁጥር የተቀመጠውን መነሻ እና ጣሪያውን በአረፍተ ነገር ሲያስቀምጥም ቅንፍ ከፍቶ የዘጋበት ቃል ትክክለኛ ያለመሆኑ(ቅንፉ ሲዘጋ ያልበለጠ በሚለው ቃል መጨረሻ ላይ ያለመቀመጡ፣
o በአዋጁ አንቀጽ 26(4) ስር ባለሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት የራሱን ውሳኔ ሊያሻሽል እንደሚችል የሚገልጽ ድንጋጌ እያስቀመጠ በድንጋጌው የመጨረሻ አረፍተ ነገር ፊደል… ያ… ቀሪ ተደርጋ ሊሻሻል ይችላል ተብሎ መቀመጡ፣(ሊያሻሽል……. መባል የነበረበት ይመስለኛል).
2.3 አዋጁ ስለሰበር የሕግ ትርጉም አስገዳጅነት የሚገልጽበት አግባብ ለመደበኛ ፍርድ ቤቶች ብቻ እንደሆነ የሚያስመስል መልዕክት የሚያስተላልፍ መሆኑ
 በአዋጁ አንቀጽ 10(2) ስር የሰበር ችሎቱ የሚሰጠው የሕግ ትርጉም አስገዳጅነቱ በየትኛውም ደረጃ በሚገኝ የፌዴራልም ሆነ የክልል ፍርድ ቤት እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን በአዋጁ አንቀጽ 2(5) ደግሞ የመጨረሻ ውሳኔ የሚባለው በፍርድ ቤት የተሰጠ ብቻ ያለመሆኑን የሚያስገነዝብ ድንጋጌ ይዟል፡፡ ስለሆነም ሁለቱ ድንጋጌዎች እንዲሁም አንቀጽ 2(4(ሰ)) ድንጋጌ መጣጣም ይገባቸው የነበረ ከመሆኑም በላይ የህግ ትርጉም አስገዳጅ እንዲሆን ከፈለገበት ዓላማና ችሎቱ ሲከተለው ከነበረው፣ አሁንም እየተከተለ ካለው አሰራር አንጻር የሕግ ትርጉሙ ለፍርድ ቤት፣ በሕግ የመዳኘት ስልጣን በተሰጣቸው አካላት፣ ተቋማትና አማራጭ የክርክር መፍቻ ሰጪ አካላት ጭምር አስገዳጅነት እንዲኖረው ግልጽ መደረግ ነበረበት፡፡ ለግልፅነት ብዬ ያነሳሁት እንጂ እነዚህ ተቋማት የሰበር ችሎቱን የህግ ትርጉም ተቀብለው ተግባራዊ ማድረግ አንችልም ማለት ይችላሉ ለማለት አለመሆኑ ይታወቅልኝ፡፡
2.4 መካተት የነበረባቸውን ጉዳዮች የተወ መሆኑ
 የፍሬ ነገር እና የማስረጃ ምዘና ስህተት የሚባለው ምን እንደሆነ ትርጉም ማስቀመጥ ወይም አመላካች ነጥቦችን ጠቅሶ ያለማለፉ፣ በዚህ ረገድ የኦሮሚያ ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር ተጠቃሽ ነው፡፡
 በሰበር ችሎቱ የተሰጠ የህግ ትርጉም ለአንድ ጉዳይ አስገዳጅ ነው የሚባለው በመሰረታዊ ሕግና በፍሬ ነገሮች መካከል መመሳሰል ሲኖረው መሆን ያለመሆኑን ጠቅሶ ያለማለፉ፣
 የሰበር ችሎቱ ዳኞች በህግ ትርጉሙ የሚገደዱ መሆን ያለመሆናቸው፣(ምንም እንኳን ዳኞቹ ከሌሎች የጠቅላይ ፍርድ ቤት ችሎቶች የተለዬ ስልጣን የሌላቸው መሆኑ ቢታወቅም ለክርክር በር ይከፈት የነበረ ጉዳይ መሆኑ ይታወቅ ስለነበር መፍትሔ ተበጅቶ ቢታለፍ መልካም ነበር)፣
 የሰበር ችሎቱ ውሳኔ ለመቀየር የሚቻልባቸው ምክንያቶች አመላካች በሆነ መንገድ(ለምሳሌ ተቃራኒ ውሳኔ መኖር፣ ሶሺዮ ኢኮኖሚክ ፋክተርስ…) ተጠቅሰው ያለማለፍ፣
 ውሳኔውን ለመቀየር ሲያስፈልግ አቋሙ መያዝ ያለበት ከአምስቱ ዳኞች በስንቱ ዳኞች እንደሆነ ተለይቶ መቀመጥ ነበረበት፣ እንዲሁም ተጨማሪ ሁለት ዳኞች ወደ ችሎቱ የሚገቡበት ከሌሎች የሰበር ችሎቶች ውስጥ ነው ወይስ ከይግባኝ ችሎቶች ጭምር የሚለውም(ምንም እንኳን ሁሉም የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ የሚሾመው በተመሳሳይ መመዘኛ ስለሆነና ዳኞችን መመደብ የፍርድ ቤቱ የአስተዳደር ኃላፊነት ቢሆንም ከችሎቱ ልዩ ስልጣን አንጻር ለግልጽኝነት ሲባል ቢቀመጥ መልካም መስሎ ይታያል)፣
 በሰበር ችሎቱ የሚደረገውን የጽሑፍ ክርክር ሬ/ጽ/ቤት ማከናወን የሚችል መሆኑ(በአሰራር ያለ ቢሆንም እንዲሁም ወደፊት በጋይድላይን ሊወጣ የሚችል ቢሆንም)
 አዋጅ ቁጥር 322/95 አዲስ ክልል ሲፈጠር ስለሚኖረው ህጋዊ ውጤት
o ለምሳሌ በዚህ አዋጅ መሰረት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከተቋቋመባቸው ክልሎች አንዱ የደ/ብ/ብ/ሕ/ብ/ክልላዊ መንግስት አንዱ ሲሆን ከዚህ ክልል ውስጥ የሲዳማ ክልል ተፈጥራል፡፡ ስለሆነም የሲዳማ ክልል የደቡብ ክልል አካል ስለነበር በአዋጅ ቁጥር 322/95 መሰረት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተቋቁሞበታል ሊባል ይችላልን የሚለው ጥያቄ በቀላሉ የሚመለስ ነው ብሎ ማሰብ አይቻልም፡፡
 እንዲሁም የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተቋቋመባቸው ክልሎች ውስጥ የፌዴራሉን መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ስልጣንን በውክልና የሚያዩት የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች በሚሰጡት ውሳኔ ይግባኙ መቅረብ ያለበት ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት መሆን ያለመሆኑም በዚህ አዲስ አዋጅ ምላሽ ማግኘት ይገባው ነበር፡፡ ይህ እንዳይሆን የሚከለክል የሰበር ችሎቱ አስገዳጅ ውሳኔ ስላለ፡፡
2.5 ሕገ መንግስታዊ ጥያቄ የሚያስነሱ ጉዳዮች ያሉበት መሆኑ
አዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ለአዲስ አበባና ለድሬዳዋ ከተማ ፍርድ ቤቶች በወንጀልም ሆነ በፍትሃ ብሔር ጉዳዮች ስልጣን ሰጥቷል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤቶች በኢ.ፌ.ዲ.ሪፐብሊክ ሕግ መንግስት የተቋቋሙ መሆን ያለመሆኑ አከራካሪ ጥያቄ ከመሆኑም በላይ እነዚህ ፍርድ ቤቶች ከፌዴራል ስርዓት ጽንሰ ሀሳብ አንጻርም ፍርድ ቤቶቹ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር የተያያዙ ጉደዳዮችን ብቻ ለማየት ስልጣን ከሚኖራቸው በስተቀር የፌዴራል ጉዳዮችን እንዲዳኙ የሚደረግበት የሕግ አግባብ ያለ አይመስለኝም፡፡ እንዲሁም ህገ መንግስቱ የሰበር ሰበር እንደሚኖር የሚያሳይ ድንጋጌ ይዞ እያለና ይህ ደግሞ ሕገ መንግስቱ ሲረቀቅ በነበረው ውይይትም በግልጽ ተነስቶ አረቃቂው አቋም ይዞበት ያለፈው ሁኖ እያለ በአዲሱ አዋጅ የክልል ጉዳዮች በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሚታዩበት መንገድ እጅግ ጠባብ እንዲሆን መደረጉ ሕገ መንግስታዊ ጥያቄ የሚያስነሳ መስሎ ይታያኛል፡፡ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች በርካታ የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን ጉዳዮች እንዲመለከቱ እንዲሁም የሰበር ሰበር ስርዓት እድል እጅግ ጠባብ እንዲሆን የተደረገበት አቢይ ምክንያት ግልጽ የሆነ ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ ስላለ ሳይሆን በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ያጋጠመው የመዝገብ ክምችት ይመስለኛል፡፡ የመዝገብ ክምችት ማጋጠም ወደ ፍርድ ቤት የሚመጡትን ጉዳዮች ለመከልከል/ ለመገደብ ወይም የፍርድ ቤቱን ስልጣን ለሌላ አሳልፎ ለመስጠት ህጋዊ ምክንያት ሊሆን አይችልም፡፡
3. ማጠቃለያ
ጠንካራ ፍርድ ቤት ለአንድ አገር ብልፅግና ወሳኝ ሚና አለው፡፡ ጠንካራ ፍርድ ቤት የሚኖረው ደግሞ የፍርድ ቤቱን ነፃነትና ገለልተኝነት የሚያረጋግጥ ጠንካራ የሕግ ማዕቀፍ ሲኖርና የወጣው ህግም በትክክል ሲተገበር መሆኑ ይታመናል፡፡ በእኛ አገር ነጻና ገለልተኛ ፍርድ ቤቶች እንደሚኖሩ በሕገ መንግስቱ ጭምር የተደነገገ ቢሆንም በህገ መንግስቱ አግባብ የተቋቋሙ ፍርድ ቤቶች ለበርካታ ጊዚያት የተለያዩ አዋጆች ሲወጡላቸው የነበሩ ከመሆኑ ውጪ ነጻና ገለልተኛ ነበሩ ለማለት አያስደፍርም፡፡ ለዚህ ትልቁ ማሳያ ደግሞ ፍርድ ቤቶቹ የራሳቸውን በጀት ማስመደብና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን የማስተዳደር ስልጣን ያልነበራቸው መሆኑ ነው፡፡ አሁን የወጣው ሕግ ግን እነዚህን ችግሮች አስወግዷል፡፡ ይህም ትልቅ እምርታ ነው፡፡ በዚህም ለፍርድ ቤቶቻችን ነጻነታቸውና ገለልተኝነታቸው ማሳኪያ የሚሆን ትልቁ ሐዲድ ተገንብቶላቸዋል ማለት ይቻላል፡፡ በሐዲዱ መጓዝ እና ወደ መዳረሻው መድረስ ደግሞ የፍርድ ቤቶቹ አመራሮች፣ ዳኞችና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ኃላፊነት ይሆናል፡፡ ከላይ የተጠቀሱት የአዲሱ አዋጅ ችግሮች መሰረታዊ ሊባሉ የማይችሉ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አንድ ህግ በአንድ ተቋም መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት ታስቦ ሲወጣ ትልልቅ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ማድረግ፣ በአሰራር ሂደት ያጋጠሙትን ችግሮች መቅረፍ እና ረዥም አመታት ሊያሰራ የሚችል/ ዘመን ተሻጋሪ ሁኖ መቀረፅ ያለበት መሆኑ የሚታመን ከመሆኑም በላይ ሕጉን የማርቀቅ ስራም/Drafting Task/ የዘርፉን ጥበብ ባሟላ መልኩ ከአርትኦት፣ ከቋንቋ ትርጉም ግጭትና ከይዘት መጣጣም እና ከሌሎች ተያያዥ ችግሮች የጸዳ እንዲሆን ተገቢው ጥንቃቄ ይጠይቃል፡፡
Via alamaw wele
ሰላም እንዴት ናችሁ!!!!
==============
በቅድሚያ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮችና ኢ/ያዊያን እንኳን ለኢደል አልአድሃ አረፋ በአል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!!!!!
.
.
ከላይ የተቀመጡ ፅሁፎችን አይቻለሁ፡፡2ቱም መልካም የሚባሉ ናቸው፡፡ነገር ግን የሚያመጡት ውጤት ደካማ ነው፡፡ባቡፈው ጊዜ ማለትም ገና የኮንሰርቲየሙ ስብሰባ ከመካሄዱ አንድ ሳምንም ቀደም ብዬ በዚሁ ገፅ የመውጫ ፈተናን አስመልክቶ የተማሪውን ዝግጅት በተመለከተ ከሁሉም ዩንቨርስቲዎች መረጃ እንድሰጠንና ለሚመለከተው አካል እንድደርሰው ለማድረግ ሰፊ እድል ተሰጥቶ ነበር፡፡አሁን ፈተናው እንድራዘም እየጠየቃችሁ ያላችቱ አካላትም፡ጭምር በጊዜው ለምን ዝምታን መረጣችሁ??? ደግሞስ ምን የቱዬ ነገር ተፈጠረ ዛሬ ላይ ??? ያኔ ግን ከአስር በላይ ዩንቨርስቲዎች ያሉበትን አቋምና ዝግጅት አሳውቀውን እኛም ለኮንሰርቲየሙ አድረሰን እርሱም በጉዳዩ አምኖበት ለተወሰነ ቀናት እንዲራዘም ወስኖ ነገር ግን ለፈተናዎች ኤጂንሲ አቅርቦት ኤጄንሲውም አሳማኝ ያለውን ም/ት አቅርቦ ባለበት እንደሰጥ ወስኗል፡፡እኛም መረጃውን አድሰናል ተማሪውም በተቻለ መጠን ሙሉ ጊዜውን ተጠቅሞ ለፈተናው ራሱን እንዲያዘጋጅ ጥሪ አድርገናል፡፡
.
.
በሌላ መልኩ ግን በዝግጅት የተሻልን ዩንቨርስቲዎች የሌሎችንም አቅምና ዝግጅት ወርደን እኛን በነሱ ቦታ አስቀምጦ ማየቱ ተገቢ ነው ባይ ነኝ፡፡በግሌ እንዲራዘም አልፈልግም በዝግጅት በኩልም ከሌላው ዩንቨርስቲ በተሻለ መልኩ አርባምንጭ ጥሩ ላይ ነን ብዬ አምናለሁ ተማሪውም መራዘሙን አይፈልግም ብዬ አምናለሁ፡፡ይሁን እንጅ እንደ አገር አቀፍ ፈተና መለመድ የሌለበት የጊዜ አወሳሰን ወጥ የሆነ ስኬጁልና ካሪኩለም በሌለበት፣የህግ ት/ቤቶችና ተማሪው በተለያዬ አቋም ባለበት ተወዳዳሪና ወጥ የሆነ አመዛዘን ማምጣት ከባድ ነው፡፡ጥቂት ዩንቨርስቲዎች ተማሪው ምንም ዝግጅት የለውም እንደውም በሪሰርችና በአፓረንትሺፕ ውጥረት ላይ ነው ት/ቤቶቹ ግን ዝግጁ ነን ይላሉ ይሄ ደግሞ ትልቅ ውድቀትን ያመጣል፡፡
.
.
በመሆኑም እንዲራዘም የሚጠይቁትን አካላት እንደ ጠፋተኛ ማየቱ አግባብ ነው ብዬ አላምንም በነሱ ውደቀት ውስጥ በነሱ የልፋትን ማጣት ውስጥ በነሱ ተስፋ መጨለም ውስጥ በነሱ የ17አመት ድካም ውስጥ ሆነን መለካት አለብን፡፡የነሱ ውድቀትም ይሁን ማለፍ ለሌሎቻችን ተራ ሆኖ ሊታየን አይገባም ይሄ እጣ በኛ ላይ ቢደርስ ምን አይነት ሙድ ውስጥ ልንሆን እንደምንችል መመዘኑ የበለጠ ምክንያታዊ እንዲንሆን ያደርገናል፣እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል አይነት አካሄድም ባንከተል ጥሩ ነው፣ውድድሩም ይሁን ፈተናው ከራስጋ ነው በሌላኛው መውደቅ ለመደሰት የሚመስል አይነት አቋም ሊኖረን አይገባም፣ብንችልኮ የራሳችን እህትና ወንድሞች ትግራይ ክልል በሚገኙ ዩንቨርስቲዎች የነበሩ አሁን ላይ ተስፋ ቆርጠው የሚሆኑት የሚናገሩት የሚወቅሱት አጥተው ያን ሁሉ አመት ደክመው በዝምታ ውስጥ ናቸው፣ይልቅ ማሰብ ከቻልን የነሱም ጉዳይ ስለምን በቸልታ ታዬ፣የሚመለከተው አካል ለምን በቶሎ መፍትሄ አይፈልግም ብለን መጮህና የመፈትሄው አካል በሆናቸው ነበር፡፡እነሱም እንደኛ እኩል ለፍተዋል ጥረዋል ታግለዋል፣እኛ አሁን በጉጉት የምንጠብቀውን ነገም እነሱም መጠበቅና ህይወታቸውን ማስተካኩል ይፈልጋሉ ፡፡ነገር ግን ማን ይናገርላቸው ማንስ ይስማቸው??? ይሄን ትተን ደግሞ ሰላም አካባቢ ያለን ደግሞ በሌላ ውጥረት አልተዘጋጀንም አግዙን ጊዜ ይሰጠንና እንዘጋጅ ሲሉ ስለምን መረዳት እንዳቃተን ግን አልገባኝም፡፡
.
.
እኛ ቢራዘም አንድም የሞራል ውድቀት ነው ሁለትም እንደ አድስ ተመልሰን እምደክማለን፣ሳይራዘም ቢቀርና አህትና ወንድሞቻችን ቢወድቁ ደግሞ ውደቀቱ የሞራል ሳይሆን የአመታት ልፋት ነው የህይወታቸው መስመር ብልሽት ነው፣ንፅፅሩን ለናንተው ትቼው እኛ ብንታገስና የሚመለከተው አካል ተረድቷቸው እኩል ሚዛን ላይ ሆነን ብንፈተን መልካም ነው ባይ ነኝ፡፡መረሳት የሌለበት ግን በዝግጅት በኩል ከየትኛውም በላይ እኛ ዝግጁ ነን፡፡ራስ ወዳድ ላለመሆንና ምክንያታዊነትን በመላበስ ነው ሲቀጥል ባለፈው መራዘሙን የከለከለው ፈተናዎች ኤጄንሲ እንጂ ሁሉም ዩንቨርስቲ ተስማምቶበት የነበረ ጉዳይ ነው፡፡
.
.
ስንፅፍ የማንንም ሞራል ባንነካ ነፃና ገለልተኛ ሃሳባችንን በምክንያት እየረስደገፍን ብንናገር፣የውድድርና የእልክ የመሸናነፍ መድረክ ባናደርገው እላለሁ፡፡
.
.
በመጨረሻ ግን ሁላችንም ከዝግጅት መዘናጋት የለብንም ፈፅሞ ስለመራዘሙ ረስተን ባለንበት አቋም ልናጠና ይገባል፡፡ይህ ውሳኔ የሚወሰነው በማንኛችንም የግል ጩኸት ሳይሆን በሚዛን ነው፣በተረፈ በያላችሁበት ዩንቨርስቲ ዲኖችጋ በቅርበት መረጃ ተለዋወጡ፡፡
.
.
መልካም ጊዜ በያላችሁበት!!!!
አህመድ.M(ከአ/ምንጭ)
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
አለሕግAleHig ️
ስለአዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013፡- አንዳንድ ምልከታዎች 1. የአዋጁ መልካም ጎኖች፡- 1.1. የተለያዩ አዋጆችን አንድ ላይ አጠቃልሎ/consolidated/ ለአጠቃቀም ምቹ ማድረጉ፣ 1.2. በፍርድ ሊወሰኑ በሚችሉ ጉዳዮችና በሕገ መንግስታዊ መብቶች ላይ ፍርድ ቤቶች ስልጣን ያላቸው መሆኑን ግልጽ ለማድረግ ጥረት ማድረጉ፣ 1.3. ስለመሰረታዊ የሕግ ስህተት አመላካች ሊባሉ የሚችሉ…
ትክክለኛ እይታና እውነተኛ ሃሳብ ነው፣ የግሌ ትዝብትም ነበር። ከአዋጁ ውስንነት አንፃር እኔ ታዚቢያቸው በፀሐፊው ካልተዳሰሱት ነጥብች መካካል የተወሰኑትን ለማሳየት፦
1. በአዋጁ የትርጓሜ ድንጋጌ ስር አንቀፅ 2(11) ላይ የፃታ አገላለጽ መደንገጉ፣
2. በሌሎች ሕጎች የተጠቀሱ ጉዳዮች የሚል ድንጋጌ በብዙ አንቀፆች ስር አሰልቺ በሆነ መልኩ ተደጋግሞ መደንገጉ፣
3. በአንቀፆች መካከል በአንዳንድ በታዎች የክፍተት (space) አሰጣጡ ወጥነት የጎደለው ድንጋጌዎች የተበታተኑ መሆን፣
4. የፌዴራል ከፍተኛ እና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶች ስልጣንና ተግባር ተደጋግሞ በአንቀፅ 19(6) እና 20 ላይ መፃፉ። ተመሳሳይ ሃሳብና ድንጋጌ ተደጋግሞ መፃፉ ከredundancy ውጭ የተለየ ፈይዳ የላቸውም
5. የአንቀፅ 26 አርዕስት የአማርኛ ቅጂው ከእንግሊዝኛው ጋር የማይጣጣም መሆኑ፦ አማርኛው ከሰባት ያላነሱ ዳኞች ሲል እንግሊዝኛው with not less than five judges የሚል መሆኑ
በመልካሙ ጌታሁን‼️
#join #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Legal Manager at BGI Ethiopia

Company: BGI Ethiopia

Location: Ethiopia

State: Addis Ababa Jobs

Job type: Full-Time

Job category: Legal Jobs in Ethiopia

Job Description

Purpose of the job

The Legal Manager is responsible for overseeing the legal matters of BGI Ethiopia and subsidiaries in Ethiopia.

Main duties & responsibilities

Provide updates on all changes to laws and regulations within the Country

To support in the drafting, reviewing, negotiation, and finalization of legal documents

Ensure that the company carries its commercial activities in full compliance with internal (Group) policies, codes, and guidelines,

Ensure that the Company and its subsidiaries comply with the Corporate regulations in the Country.

Giving legal advice on all matters requested by the company’s management.

 Overseeing the contract drafting and review process.

Ensure that regulatory policies and procedures have been documented, implemented, and communicated;

Prepare and lodge reports with relevant regulatory and compliance authorities;

 Liase with external regulators

Collaborate with public authorities for the proper introduction of regulatory standards and facilitate discussions;

Periodically review risks to ensure identification of legal and regulatory risks to all commercial teams and design plans to avoid these;

Undertake such other legal tasks as assigned by the Company.

The role is largely office-based, but frequent travel to sites will be necessary.

Job Requirements

In depth knowledge of the laws regulating the brewery sector

 Expert knowledge of professional compliance and investigation standards; and ability to apply policy and legal concepts to issues.

Commitment to the highest ethical and professional standards.

Excellent written and oral communication skills.

Ability to work independently and within a team environment.

Ability to share information and build consensus across stakeholders.

Ability to supervise support and professional analyses functions for compliance and ethics programs.

Ability to establish trust and credibility with stakeholders and senior management.

Knowledge of the Group’s ethics and compliance policies, procedures, and programs.

Ability to develop and deliver presentations.

Demonstrated ability to successfully manage a large corporate or centralized institutional legal office.

Knowledge of legal documentation procedures and requirements.

Ability to develop and implement legal strategies and solutions.

Expected Education and Experience

Learned Law Bachelor

6 years of experience of work preferably in a law office.


Method of Application

Submit your CV and Application to yibelu.workineh@Castel-Afrique.com
Use the title of the position as the subject of the email
Closing Date : 23 July. 2021
#join #join #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties