አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የፌዴራልና የክልል ፍ/ቤቶች በመተባበር መንፈስ መስራታቸውን ይቀጥላሉ!

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከክልል ፍርድ ቤቶች ጋር በጋራ ሊሰሩ የሚችሉበት ምህዳር እና የሚያገናኛቸው ሰንሰለት መነሻው ህግመንግስታዊ የዳኝነት ውክልና ስልጣናቸውና አስተዳደራዊ ግንኙነታቸውን ለመወሰን የወጡ ህጎች ናቸው፡፡

የኢፌዲሪ ህገመንግስት ስለፍርድ ቤቶች አወቃቀርና ስልጣን ግልጽ ድንጋጌዎችን ባስቀመጠበት ምዕራፍ ዘጠኝ የፌዴራል ከፍተኛና መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች ባልተደራጁባቸው ክልሎች የክልል ፍርድ ቤቶች የፌዴራል መጀመሪያና ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ስልጣን በውክልና የተሰጣቸው መሆኑን ይደነግጋል፡፡ ከዚህ በመነሳት የክልል ፍርድ ቤቶች የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የሚመለከቷቸውን ጉዳዮች ከክልሉ የዳኝነት ጉዳዮች ጋር ደርበው ይሰራሉ፡፡ ለዚህም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለክልል ፍርድ ቤቶች የበጀት ማካካሻ እንደሚሰጥ ተጠቅሷል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የተሰጡ የመጨረሻ ውሳኔዎችን የማየት ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ ይህም ፍርድ ቤቱ የፌዴራል ጉዳዮች ላይ በክልል ጠቅላይ ፍ/ቤቶች የተሰጡ ውሳኔዎችን በይግባኝ፤ የክልል ጉዳዮችን የተመለከቱ ውሳኔዎችን ደግሞ በሰበር ችሎት እንዲያይና ውሳኔውን እንዲያሻሽል ወይም እንዲያጸና ወይም እንዲሽር ያስችለዋል፡፡

በተመሳሳይ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን አደረጃጀትና ዝርዝር የስልጣን ወሰን ለማስቀመጥ የወጣው የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁ.25/1988 የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ጋር በጋራ ስለሚያገናኟቸው ዳኝነታዊና አስተዳደራዊ ሁኔታዎች ያመላክታል፡፡ ከነዚህም መካከል የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የመዝገብ አያያዝና ጠቅላላ አሰራር ከክልል ፍርድ ቤቶች ጋር በመመካከር የሚሻሻልበትን ሁኔታ ያመቻቻል፡፡ የክልል ፍርድ ቤቶች የፌዴራል ጉዳዮችን አስመለክቶ ስላከናወኑት ተግባራት በስታትስቲክስ የተደገፈ ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባል፡፡

ከዚህም ባሻገር ዓዋጁ በሃገር አቀፍ ደረጃ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት፣ ምክትል ፕሬዝደንትና ዳኞች፤ የፌዴራል ከፍተኛና መጀመሪያ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝደንቶች፤ እና የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንቶች አባል የሚሆኑበት እንዲሁም ሌሎች የፍትህ አካላት የሚሳተፉበት አንድ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ጉባዔ እንደሚኖር ይፈቅዳል፡፡ ይህ ጉባዔም በዳኝነት ስራ አስተዳደር ረገድ ባጋጠሙ ችግሮች ላይ ተወያይቶ መፍትሔ ይሰጣል፡፡ የፍርድ ቤቶችን አስራር ለማሻሻል የሚረዱ መመሪያዎችና ውሳኔዎችን ያሳልፋል፡፡ እንዲሁም አዳዲስ ህጎች እንዲወጡ ወይም ነባር ህጎች እንዲሻሻሉ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሃሳብ ያቀርባል፡፡

ሌላው የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በህገመንግስቱና ይህንኑ መሰረት በማድረግ በወጡ ዓዋጆች በተሰጣቸው የዳኝነት ስልጣን በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የሚሰጧቸው ውሳኔዎችና ትዕዛዞች በክልል ፍርድ ቤቶች እንዲፈጸሙ የፌዴራሉ ፍርድ ቤቶች ማዘዝ እንደሚችሉም በግልጽ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

ከላይ የተጠቀሱት መሰረታዊ የህግ ሃሳቦች የፌዴራልና የክልል ፍርድ ቤቶች የተሳሰሩ መሆናቸውንና የሚያገናኟቸው በርካታ ጉዳዮች እንዳሉ የሚያመላክቱ ናቸው፡፡ ህገመንግስቱ ስራ ላይ ከዋለበት ጊዜ ጀምሮ የክልልና የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በህግ አግባብ የዳኝነት እየሰጡ ቆይተዋል፡፡ በሃገራችን የተዘረጋው ህገመንግስታዊና ፌደራላዊ ስርዓት ተጠናክሮ፤ የክልልና የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኝነታዊ ነጻነታቸውን ጠብቀው ፍትህ የመስጠት ሃላፊነታቸውን እየተወጡም ናቸው፡፡ ነጻና ግልጽ፤ ህጋዊና ፍትሃዊ፣ ተደራሽና የህዝብ አመኔታ ያለው ዳኝነት ለመስጠት በየጊዜውና በየሁኔታው የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች ቢኖሩም ለጋራ ግብና ስኬታማነት የስልጣን ሚዛናቸውን ጠብቀው የየራሳቸውን ጥራት እያደረጉም ይገኛሉ፡፡

የፌዴራልና የክልል ፍርድ ቤቶች በውክልና እና በይግባኝ ስልጣናቸው የጋራ ባለጉዳዮች ሊኖሯቸው እንደሚችል የታመነ ነው፡፡ የዳኝነት ውክልና ስልጣን ባልተሰጣቸው ክልሎች እንኳን የፌደራል ፍርድ ቤቶች በተዘዋዋሪ ችሎቶች ዳኝነት ይሰጣሉ፡፡ በቪዲዮ ኮንፈረንስ እና በኢ ፋይሊንግ (የርቀት ችሎት ማእከሎች) በመታገዝም ባለጉዳዮች ባሉበት ከልል ሆነዉ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችሉ አሰራሮችም ተዘርግተዋል፡፡ ይህም በክልል የሚገኙ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ባይ ባለጉዳዮችን ከአላስፈላጊ ወጪ እና እንግልት ለመታደግ ተችሏል፡፡

አስተዳደራዊ ጉዳዮችንም በተመለከተ በትብብር መንፈስ በጋራ ጉባዔ በመምከር፤ በመልካም ተሞክሮ እና በመረጃ ልውውጥ በመታገዝ በመካከላቸው መልካም የግንኙነት ባህል አዳብረዋል፡፡ በዳኝት አገልግሎት አሰጣጥና አስተዳደር ጉዳዮች ላይ በየጊዜው ምክክር ይደረጋል፡፡ የእርስ በእርስ የልምድ ልውውጥ ይካሄዳል፡፡ በሃገራችን ቀልጣፋ፤ ተደራሽ እና የሚሻሻል የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት የጋራ አቋም የተያዘባቸው የመረጃ ልውውጥ ስራዎችም ይከናወናሉ፡፡

በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወደ ክልሎች እንዲሁም ከክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ወደ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሚላኩ ደብዳቤዎችና ማስታወሻዎች የመረጃ ልውውጥን ለማቀላጠፍ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ከማድረግ በዘለለ የሚደረጉት የመረጃ ለውውጦች ተቋማዊና ክልላዊ አደረጃጀት ላይ ጣልቃ በመግባት አሉታዎ ተጽእኖ ለማሳረፍ ታስበው የሚደረጉ አይደሉም፡፡

በተለይም በሃገራችን የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ስርጭት ለመግታትና ለመከላከል የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ባለበት ጊዜ ፍርድ ቤቶች የወረርሽኑ ማሰራጫ ማዕከል እንዳይሆኑ በመደበኛ አገልግሎት አሰጣጣቸው ላይ ለውጥ አድርገዋል፡፡ አስቸኳይነት ያላቸውን ጉዳዮች ብቻ እንዲያዩ በከፊል ዝግ ሆነው እንዲቆዩ በአመራሮቹ ውሳኔ ተላልፏል፡፡ በዚህ ውሳኔ ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች የወረዱ የስራ አቅጣጫዎችን በደብዳቤ /በማስታወሻ / የክልል ፍርድ ቤቶችና ባለጉዳዮች እንዲያውቋቸው ማድረግ አስፈላጊነቱ አጠያያቂ አይሆንም፡፡ የክልል ባለጉዳዮች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት እንግልት እንዳይደርስባቸውና ለወረርሽኙ ተጋላጭ እንዳይሆኑ ያግዛል፡፡ የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶችም በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ተረድተውና ተገንዘብው በፍርድ ቤቶቻቸው የአሰራር ለውጥና ማሻሻያ እንዲሁም አስተዳደራዊ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ይረዳቸዋል፡፡ ይህም የመረጃ ልውውጥ የክልልም ሆነ የፌዴራል ፍርድ ቤቶቹ የጋራ የዳኝነት ተልዕኳቸውን በተጣጣመና በተናበበ መልኩ እንዲወጡ መልካም እድል ይፈጥርላቸዋል፡፡

በአጠቃላይ በፌደራልና በክልል መንግስታት ህግ የመተርጎምና ዳኝነት የመስጠት ተልዕኮ የተሰጣቸው ፍርድ ቤቶች በህገመንግስቱ እና ህገመንግስቱን መሰረት አድርገው በወጡ አዋጆች ዜጎች ህጋዊና ፍትሃዊ ዳኝነት የማግኘት መብቶቻቸው እንዲከበሩባቸው በመተባበር መንፈስ መስራታቸውን ይቀጥላሉ፡፡

አካላዊ ርቀታችንን በመጠበቅ፤ አፍና አፍንጫችንን በጭምብል በመሸፈን፤ እጃችንን በሳሙናና በውሃ በተደጋጋሚ በመታጠብ፤ (በተቻለ መጠን) በቤት በመቀመጥ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን በጋራ እንከላከል!

ፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ቸልተኝነትን እና መዘናጋትን በማስወገድ ከመቼውም ግዜ በላይ በጥንቃቄና በእውቀት የኮሮና ቫይረስን እንቆጣጠረው!
________________

“ብልህ ከሆንክ በሰው ከደረሰው ትማራለህ…” የኮሮና ቫይረስ በሀገራችን ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ ወረርሽኙ ከፍተኛ ጉዳት በህዝባችን ላይ ከማድረሱ በፊት በርካታ የበሽታው መተላለፊያ መንገዶች እና የጥንቃቄ መመሪያዎች ላይ የግንዛቤ እና የቅድመ መከላከል ስራ ቢሰራም ቸልተኝነትና መዘናጋት በወለደው ችግር የወረርሽኙ ስርጭት የህይወት ዋጋ እያስከፈለን ይገኛል፡፡

በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በዓለም ከ8 ሚሊዮን ሰዎች በላይ በቫይረሱ ተጠቅተዋል፤ 436 ሺህ ሰዎች በላይ ሕይወታቸውን አጥተዋል፡፡አሜሪካ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር በመያዝ ቀዳሚ ስትሆን፥ ካላየው አላምንም ያለችውን ብራዚልን በሁለተኛ ደረጃ፤ ሩሲያን ደግሞ በሦስተኛ ደረጃ አጥቅቷል፡፡

በአገራችን የመጀመሪያው ሰው በኮሮና መያዙ ከተረጋገጠ ከመጋቢት ወር ጀምሮ ባሉት 3 ወራት ውስጥ በቫይረሱ የተያዙ፣ ህይወታቸውን የሚያጡ፣ በጽኑ ሕክምና ክፍል እየታከሙ ያሉ ሰዎች ቁጥርም እየጨመረ መምጣቱ እጅጉን እያሳሰበ መጥቷል፡፡

መታዘዝ ከመስማት ይበልጣል እና በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተከለከሉ ተግባራትን በማክበርና በማስከበር የነገ ተስፋችንን፣ ቤተሰባችንን እንዲሁም የአገራችን ህልውና ብሎም ደህንነት መጠበቅ የሁላችን እዳ እና ግዴታ መሆን አለበት፡፡

ከሁሉም በፊት ዛሬ ጤናችን በእጃችን ሳለ ከቁጥር ጎድለን እንዳንጎድል ቸልተኝነትን በማስወገድ ከመቼውም ግዜ በላይ በእውቀትና በማስተዋል ኮሮናን ልንቆጣጠረው ይገባል፡፡
Selam ye ale betesoch endet nachu..ye serategna wel(form of employment contract in ameharic) kalachu lakulegn pls?
BlueNileMyRiver
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ ቤቶች የኮቪድ-19ን በመከላከል መደበኛ አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸው መመሪያ ለማውጣት ረቂቅ መመሪያ እያዘጋጀ መሆኑን ገለጸ፡፡
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በሃገራችንም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቅርብ ጊዜ መፍትሔ እንደማይኖረው ከግምት ውስጥ በማስገባት የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ወርሽኙን በመከላከል መደበኛ አገልግሎታቸውን መስጠት የሚችሉበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየሰራ ይገኛል፡፡
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በሃገራችን የኮቪድ 19 ወርሽኝን ስርጭት ለመግታትና ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ፍርድ ቤቶች ከመጋቢት 10 ቀን 2012 ዓ.ም በከፊል ዝግ ሆነው አስቸኳይነት ያላቸው ጉዳዮች ብቻ በተረኛ ችሎት እንዲያስተናግዱ እስከ ሐምሌ 10 ቀን 2012 ዓ.ም መወሰኑ ይታወቃል፡፡
ነገር ግን ፍርድ ቤቶች ዜጎች በህግ አግባብ ፍትህ የሚያገኙበት ተቋማት እንደመሆናቸው ለረጅም ጊዜ በከፊል ዝግ ሆነው መቆየት እንደሌለባቸው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በጽኑ ይገነዘባል፡፡
በመሆኑም ጠቅላይ ፍ/ቤቱ በኮቪድ 19 ዘመን ወረርሽኙን በመከላከል ዜጎች ፍትህ በሚጠይቁባቸው ጉዳዮች ላይ ፍርድ ቤቶች መደበኛ አገልግሎ መስጠት የሚያስችላቸውን ወጥ አሰራር ለመዘርጋት የሚመሩበት ረቂቅ መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ የረቂቅ መመሪያው ዝግጅት ሲጠናቀቅም የህግ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ግብአት እንዲሰጡበት ከተደረገ በኋላ ስራ ላይ እንዲውል ይደረጋል ብሏል፡፡
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ከሐምሌ 10 ቀን 2020 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን “በኮሮና ቫይረስ (COVID 19) ምክንያት የተከሰተውን ሀገራዊ ሁኔታ አስመልክቶ ፍርድ ቤቶች ሊመሩበት የሚገባ አጠቃላይ መመሪያ (Comprehensive Guideline)” አውጥቷል እየተባለ የሚሰራጨው መረጃም ትክክል አለመሆኑን ገልጿል፡፡
የ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
በህጻናትና ሴቶች ላይ የሚፈጸመዉ ጥቃት አሰመልክቶ ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተሰጠ መግለጫ
****************************************
በህጻናትና ሴቶች ላይ የሚፈጸመዉ ጥቃት ይብቃ የምንልበት ጊዜው አሁን ነዉ ፡፡
****************************************
ዛሬ ዓለማችን ብሎም ሀገራችንን የኮሮና ቫይረስ ተግዳሮት እየተፈታተነን ባለበት ወቅት በህጻናትና በሴቶች ላይ የሚደረሰው ጥቃት አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱ የገሀድ ነዉ፡፡ ይህን ችግር ለመቅረፍ የሁላችንም ኃላፊነት መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የህግና የፍትህ አካላት የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ጥረታቸውን ይቀጥላሉ ፡፡

-ለአብነት ባለፉት 3 ወራት ዉስጥ በአስገደዶ መድፈር በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ክስ ከተመሰረተባቸው 40 መዝገቦች፣ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ተግዳሮት ውስጥ ሆነንም ቢሆን እስከ አሁን ድረስ 8 መዝገቦች ላይ ዉሳኔ ተሰጥቶባቸዋል። ከእነዚህ ዉስጥ በዐቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተባቸው የ64 ዓመቱ ተከሳሽ በአዲስ አበባ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዕድሜያቸው ስምንት እና ዘጠኝ አመት የሆኑ ሁለት ሴት ህፃናቶችን በተለያዩ ቀናቶች ተከራይቶ ከሚኖርበት ቤት ውስጥ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈጽሞባቸዋል፡፡ፈጽሞባቸዋል፡፡

-በዚህም ተከሳሹ የኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 627(1) ተላልፎ በመገኘቱ አራት ክሶችን ተመስርቶበታል፡፡ ጉዳዩ በፍጥነት ወሳኔ እንዲያገኝ በተደረገው እንቅስቃሴ ተከሳሽ የተከሰሰበትን ክስ ሊያስተባብል ባለመቻሉ ፍርድ ቤቱ ተከሳሽን በአራቱም ክሶች ጥፋተኛ ነህ ብሎታል፡፡ በዚህም ሰኔ 16 ቀን 2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት የተከሰሰበት ድንጋጌ ጣሪያው 25 ዓመት በመሆኑ በ 25 አመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡

-በተመሳሳይ ሁኔታ በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን አካባቢ ከህፃንነቷ ጀምሮ ያሳደጋትን የ15 ዓመት የእንጀራ ልጁን የደፈረው ግለሰብ በ11 ዓመት ከ9 ወር ጽኑ እስራትየተቀጡ ሲሆን ቅጣታቸዉም በቂ አይደለምተብሎ በታመነበት ላይ የይግባኝ ክርክራችን ቀጥላል። ይህ ለአብነት ተገለጸ እንጂ በሌሎች የጥቃት ፈጻሚዎች ላይ ተገቢ የህግ ቅጣት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ ከምንጊዜም በላይ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

-ሰለሆነም በሴቶችና ህፃናት ላይ በሚፈፀሙ ወንጀሎች ህብረተሰቡ ተጋላጭ እንዲሆን ጥንቃቄእንዲያደርግና ድርጊቱ ተፈፅሞ ሲያገኝም ከመቼውም በበለጥ ከፍትህ አካላት ጎን በመሆንና ይህን አሳፋሪና አሰነዋሪ ወንጀል በማጋለጥ እና ድርጊቱን ባለመተባበር እንዲሁም ለተጎጂዎቹ ምስክር በመሆን የህግ የበላይነት እና ፍትህ እንዲሰፍን የበኩላችን እንድንወጣ በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናቀረባለን።

ኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ

ሰኔ 19 ቀን 2012 ዓ.ም

አዲስአበባ
ምክር ቤቱ በወንጀል ጉዳዮች የጋራ የፍትሕ ትብብር እና በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ መስጠት ስምምነት ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጸደቀ
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስትና በጅቡቲ ሪፐብሊክ መንግስት መካከል የተደረገውን በወንጀል ጉዳዮች የጋራ የፍትሕ ትብብር እና በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ መስጠት ስምምነት ረቂቅ አዋጅን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል ፡፡

ስምምነቱ በአለም አቀፍ ደረጃ እየጨመረ የመጣውን ድንበር ዘለል ወንጀል ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና በሃገራቱ መካከል የሚኖረውን የሰላምና የደሕንነት እንቅስቃሴዎች ለማጠናከርእንደሚያግዝ የገለጹት አምባሳደር መስፍን ቸርነት በወንጀል የሚፈለጉ ግለሰቦችን አሳልፎ መስጠት በሁለቱ ሃገሮች መካከል ሰላም፣ ጸጥታንና መረጋጋትን ለማረጋገጥም ሚናው የጎላ እንደሆነም አስገንዝበዋል፡፡

በእንደዚህ አይነት ጉዳዮች ከተለያዩ ሃገራት ጋር ስምምነቶች ተደርገዋል፣ እስካሁን ምን ውጤት ተገኝቷል? የሚሉ ጥያቄዎች ከምክር ቤት አባላት የተነሱ ሲሆን በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን ለመያዝ ከተለያዩ ሃገራት ጋር ወንጀለኞችን የመለየት ስራ እንደተሰራና ሃገራቱ አሳልፈው እንዲሰጡ መጠየቁን የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ሕግ ምክትል አቃቢ ሕግ አቶ ገለታ ስዩምአስረድተዋል፡፡

ምክር ቤቱ አክሎም በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስትና በሩዋንዳሪፐብሊክ መንግስት መካከልየተደረገውን በወንጀል ጉዳዮች በጋራ የጋራ የፍትሕ ትብብርና በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ መስጠት ስምምነት ለማጽደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል ፡፡

ስምምነቱ በኢትዮጵያና ሩዋንዳ መካከል ካለው ትስስርና ድንበር ዘለል ወንጀሎች ተጋላጭነት አንጻር በተቀናጀ የዘመናዊ ምርመራ ዘዴ፣ መረጃና ማስረጃዎች ሳይጠፉ ምርመራ በማከናዎን ወንጀለኞች ተጠያቂ እንዲሆኑ የሚያስችልና ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ስምምነት እንደሆነ አምባሳደር መስፍን አብራርተዋል ፡፡ ወንጀለኞች ኢትዮጵያ ከሩዋንዳ ጋር ያላትንና እያደገ የመጣውን የንግድ እና ኢንቨስትመንት ግንኙነት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከሕግ ለማምለጥ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩን የገለጹት አምባሳደር መስፍን፣የስምምነቱ መጽደቅ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ጉልሕ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል ፡፡

ምክር ቤቱ የተባበሩት መንግስታት አለም አቀፍ የዕቃዎች ሽያጭ ውሎች ስምምነት ረቂቅ አዋጅንም በሙሉ ድምጽ አጽድቋል ፡፡ ስምምነቱ ለአለም አቀፍ ንግድ ማደግ እና መስፋፋት እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮችን በማስወገድ የዕቃዎችን አለም አቀፍ ሽያጭ እንደሚያሳልጥ የጠቀሱት አምባሳደር መስፍን ወጪን በመቀነስና ድንበር ዘለል ንግድን በማበረታታት በአለም አቀፍ ደረጃ አስተማማኝ የንግድ ልውውጥ እንደኖር እንደሚያደርግም ነው የገለጹት

ምንጭ፡- ፓርላማ ሰኔ 18 ቀን 2012 ዓ.ም.
via ኢ.ጠ.ዐ. ሕግ
Forwarded from Deleted Account
ዘነበ ደጀን ከ ሀረር ነኝ እና 0967037846 የሚባል ስልክ ቁጥር ከሻሸመኔ ፋና fm ነን እና የ65000ሺህ ብር ሽልማቱን በባንክ እናስገባልሀለን እና ባለ 100 birr card lak blo yaschegerun new ena tetenkeku belulin hibretesebun!!!
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ ቤቶች የኮቪድ-19ን በመከላከል መደበኛ አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸው መመሪያ ለማውጣት ረቂቅ መመሪያ እያዘጋጀ መሆኑን ገለጸ፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በሃገራችንም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቅርብ ጊዜ መፍትሔ እንደማይኖረው ከግምት ውስጥ በማስገባት የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ወርሽኙን በመከላከል መደበኛ አገልግሎታቸውን መስጠት የሚችሉበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየሰራ ይገኛል፡፡

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በሃገራችን የኮቪድ 19 ወርሽኝን ስርጭት ለመግታትና ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ፍርድ ቤቶች ከመጋቢት 10 ቀን 2012 ዓ.ም በከፊል ዝግ ሆነው አስቸኳይነት ያላቸው ጉዳዮች ብቻ በተረኛ ችሎት እንዲያስተናግዱ እስከ ሐምሌ 10 ቀን 2012 ዓ.ም መወሰኑ ይታወቃል፡፡

ነገር ግን ፍርድ ቤቶች ዜጎች በህግ አግባብ ፍትህ የሚያገኙበት ተቋማት እንደመሆናቸው ለረጅም ጊዜ በከፊል ዝግ ሆነው መቆየት እንደሌለባቸው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በጽኑ ይገነዘባል፡፡

በመሆኑም ጠቅላይ ፍ/ቤቱ በኮቪድ 19 ዘመን ወረርሽኙን በመከላከል ዜጎች ፍትህ በሚጠይቁባቸው ጉዳዮች ላይ ፍርድ ቤቶች መደበኛ አገልግሎ መስጠት የሚያስችላቸውን ወጥ አሰራር ለመዘርጋት የሚመሩበት ረቂቅ መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ የረቂቅ መመሪያው ዝግጅት ሲጠናቀቅም የህግ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ግብአት እንዲሰጡበት ከተደረገ በኋላ ስራ ላይ እንዲውል ይደረጋል ብሏል፡፡

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ከሐምሌ 10 ቀን 2020 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን “በኮሮና ቫይረስ (COVID 19) ምክንያት የተከሰተውን ሀገራዊ ሁኔታ አስመልክቶ ፍርድ ቤቶች ሊመሩበት የሚገባ አጠቃላይ መመሪያ (Comprehensive Guideline)” አውጥቷል እየተባለ የሚሰራጨው መረጃም ትክክል አለመሆኑን ገልጿል፡፡

የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ (Alemwaza)
የተከበራችሁ ቅኝ መገዛትን የምታወግዙ❗️
ባርነትን የምትጠሉ! የግብፅ ኢፍትሃዊነት የሚያንገበግባችሁ ❗️

⚡️ግብፅ በኢትዮጵያ መንጭቶ ሃገሯ በደረሰው አባይ 100 በመቶ በመብራት ደምቃ የኢትዮጵያዊያን በጨለማ መኖር እንደ ዉጋት እረፍት የማይሰጣችሁ ኢትዮጵያዊያን ይህችን ፊርማ በመፈረም በድጋሜ ለቅኝ ግዛት እምቢ እንድትሉ እንጋብዛለን!! ፊርማው ተሰባስቦ ለተመድ ጄኔቫ የሚገባ ነው!!

•የተከበራችሁ ኢትዮጲያዊያንና የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ ጠል የኢትዮጲያ ወዳጆች!

⚡️ይህ በታላቁ የኢትዮጲያ ህዳሴ ግድባችን እና በአጠቃላይ አባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይ ግብፅና ደጋፊዎቿ እያደረጉ ያሉትን ኢፍትሃዊና የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ ላይ የተመሰረተ ጫና ላይ አለም አቀፍ የተቃዉሞና ትብብር ማሳያ ፊርማ (Petition) ነዉ፤ ፊርማዉ ሲጠናቀቅ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ይገባል፡፡ በመሆኑም እየገባችሁ እንድትፈርሙ ትጠየቃላችሁ!

⚡️Dear Distinguished Ethiopians and supporters of Anti-Neo-Colonialism!
This petition is prepared to oppose the unfair and colonial thoughts on the usage of Nile water.

⚡️Egypt and its imperialist supporters propagate such unjust actions. The petition is thus to call for international solidarity with Ethiopia’s quest for fair water usage on the Nile water. You are expected to sign. Once the petition is signed, it will be submitted to the UN.

https://secure.avaaz.org/en/community_petitions/the_world_a_call_for_petition_for_anti_colonial_water_agreements/details

©ወንድአጥር መኮንን

• መልካም ምሽት • #SHARE
ምክር ቤቱ በወንጀል ጉዳዮች የጋራ የፍትሕ ትብብር እና በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ መስጠት ስምምነት ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጸደቀ

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስትና በጅቡቲ ሪፐብሊክ መንግስት መካከል የተደረገውን በወንጀል ጉዳዮች የጋራ የፍትሕ ትብብር እና በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ መስጠት ስምምነት ረቂቅ አዋጅን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል ፡፡

ስምምነቱ በአለም አቀፍ ደረጃ እየጨመረ የመጣውን ድንበር ዘለል ወንጀል ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና በሃገራቱ መካከል የሚኖረውን የሰላምና የደሕንነት እንቅስቃሴዎች ለማጠናከር እንደሚያግዝ የገለጹት አምባሳደር መስፍን ቸርነት በወንጀል የሚፈለጉ ግለሰቦችን አሳልፎ መስጠት በሁለቱ ሃገሮች መካከል ሰላም፣ ጸጥታንና መረጋጋትን ለማረጋገጥም ሚናው የጎላ እንደሆነም አስገንዝበዋል፡፡

በእንደዚህ አይነት ጉዳዮች ከተለያዩ ሃገራት ጋር ስምምነቶች ተደርገዋል፣ እስካሁን ምን ውጤት ተገኝቷል? የሚሉ ጥያቄዎች ከምክር ቤት አባላት የተነሱ ሲሆን በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን ለመያዝ ከተለያዩ ሃገራት ጋር ወንጀለኞችን የመለየት ስራ እንደተሰራና ሃገራቱ አሳልፈው እንዲሰጡ መጠየቁን የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ሕግ ምክትል አቃቢ ሕግ አቶ ገለታ ስዩም አስረድተዋል፡፡ ምክር ቤቱ አክሎም በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስትና በሩዋንዳ ሪፐብሊክ መንግስት መካከል የተደረገውን በወንጀል ጉዳዮች በጋራ የጋራ የፍትሕ ትብብርና በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ መስጠት ስምምነት ለማጽደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል ፡፡

ስምምነቱ በኢትዮጵያና ሩዋንዳ መካከል ካለው ትስስርና ድንበር ዘለል ወንጀሎች ተጋላጭነት አንጻር በተቀናጀ የዘመናዊ ምርመራ ዘዴ፣ መረጃና ማስረጃዎች ሳይጠፉ ምርመራ በማከናዎን ወንጀለኞች ተጠያቂ እንዲሆኑ የሚያስችልና ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ስምምነት እንደሆነ አምባሳደር መስፍን አብራርተዋል ፡፡ ወንጀለኞች ኢትዮጵያ ከሩዋንዳ ጋር ያላትንና እያደገ የመጣውን የንግድ እና ኢንቨስትመንት ግንኙነት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከሕግ ለማምለጥ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩን የገለጹት አምባሳደር መስፍን፣ የስምምነቱ መጽደቅ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ጉልሕ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል ፡፡

ምክር ቤቱ የተባበሩት መንግስታት አለም አቀፍ የዕቃዎች ሽያጭ ውሎች ስምምነት ረቂቅ አዋጅንም በሙሉ ድምጽ አጽድቋል ፡፡ ስምምነቱ ለአለም አቀፍ ንግድ ማደግ እና መስፋፋት እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮችን በማስወገድ የዕቃዎችን አለም አቀፍ ሽያጭ እንደሚያሳልጥ የጠቀሱት አምባሳደር መስፍን ወጪን በመቀነስና ድንበር ዘለል ንግድን በማበረታታት በአለም አቀፍ ደረጃ አስተማማኝ የንግድ ልውውጥ እንደኖር እንደሚያደርግም ነው የገለጹት
ምንጭ፡- ፓርላማ ሰኔ 18 ቀን 2012 ዓ.ም.
ale sile exit exam adis neger share adrigun ebakachihu?
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና!

የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የዘንድሮውን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ (የ12ኛ ክፍል) ፈተና በኢንተርኔት በመታገዝ በኦንላይ ለመስጠት ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ታውቋል።

ለዚህ የኦንላይ ፈተና እንዲረዳ ለተማሪዎች 'ታብሌቶችን' ለማቅረብ እንደሚሰራ እንዲሁም በፈተና ጣቢያዎችም 'ፈጣን የሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት' እንዲኖር ለማድረግ ስራዎች እየተጠናቀቁ እንደሆነ ተሰምቷል።

የዘንድሮው ፈተና ተማሪዎች በኦንላይ እንዲፈተኑ ከማድረግ በተጨማሪ ውጤታቸውን በቀናት ውስጥ እንዲያውቁት ለማድረግም ዝግጅቶች እየተጠናቁቁ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

የዘንድሮ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ (የ12ኛ ክፍል) ፈተና መቼ እንደሚሰጥ እስካሁን ቀን አልተቆረጠለትም። በሌላ በኩል የ8ኛ ክፍል ፈተና በወረቀት ይሰጣል፤ የተማሪዎች ውጤትም በጊዜ ይደርሳል ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪም ባሳለፍነው ሳምንት በተሰጠ መግለጫ መሰረት ከ8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተፈታኞች በስተቀር ሁሉም የመጀመሪያ ደረጃና ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ ያለምንም ፈተና እንዲዘዋወሩ ውሳኔ ተላልፎ ነበር።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Hello, I'm sorry to bother you. I found your account from a channel. I was wondering if you could help me. I was searching for a international trade law teaching material or any good slides and i cant seem to find any. Soo.. can you help me with that?
ለሚዲያ ተቋማት በሙሉ
አዲስ አበባ

ዜና መግለጫ
በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከሀምሌ 13/2012 ዓ.ም ጀምሮ ስለሚሰጡ ተጨማሪ የዳኝነት አገልግሎቶች የተሰጠ መግለጫ
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የኮሮና ቫይረስ (Covid-19) ወረርሽኝ በሀገራችን መኖሩ ከታወቀበት ጊዜ ጀምሮ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የተለያዩ የጥንቃቄ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡ ከመጋቢት 10 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ በከፊል ዝግ በመሆን እና የከፊል ዝግ ውሳኔውን በማራዘም እስከ ሐምሌ 10/2012 ዓ.ም ድረስ በፍ/ቤቱ አመራር በተለዩ ጉዳዮች ላይ ብቻ አገልግሎት እየሰጡ ቆይተዋል፡፡
ይሁን እንጂ ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ባህሪና ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር ወረርሽኙ በአጭር ጊዜ በቁጥጥር ውስጥ ልናስገባውና ስርጭቱን ሙሉ በሙሉ ልንገታው የማንችል መሆኑን እንዲሁም አብሮን በተግዳሮትነት የሚቀጥል እንደሆነ ማስረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቶችን በከፊል በመዝጋት የዜጎች ፍትህ የማግኘት መብትን በውል ላልታወቀና ለተራዘመ ጊዜ ማቆየት የማይቻል መሆኑን ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ይረዳል፡፡ በተጨማሪም ከኮቪድ በኋላ ፍርድ ቤቶች መደበኛ ስራቸውን ይጀምሩ በሚባልበት ጊዜ ወደ ፍ/ቤት ሊመጣ የሚችለው ከፍተኛ የመዛግብት ፍሰት ፍርድ ቤቶች ስራቸውን መስራት የማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሊያስገባቸው እንደሚችል በፍርድ ቤቱ የተከናወነው የመላምት ትንታኔ ያሳያል፡፡ ለእነዚህ ሁለት አበይት ችግሮች መፍትሄ መስጠት ያስችል ዘንድ ወረርሽኙን በከፍተኛ የመካላከልና የጥንቃቄ እርምጃዎችን በመውሰድ የተቋረጡትን አገልግሎቶች ደረጃ በደረጃ ማስጀመር አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
ስለሆነም ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ ሆነው እንዲቆዩ ከተደረጉበት ከሃምሌ 13 ቀን 2012 ዓ.ም በኋላ ደረጃ በደረጃ መደበኛ አገልግሎት መስጠት ስለሚጀምሩበት ሁኔታ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀፅ 16 (1) እና በዚሁ አዋጅ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 454/97 አንቀፅ 4 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ መመሪያ አውጥቷል፡፡
በመመሪያው መሰረት በየደረጃው ባሉ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከሃምሌ 13 2012 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጡ አገልግሎቶች እና የሚወሰዱ አስገዳጅ እርምጃዎች የሚከተሉት ይሆናሉ፡፡
1. ከሐምሌ 13 - 30 /2012 ዓ.ም የሚሰጡ አገልግሎቶች
 በሁሉም ደረጃ ባሉት ፍ/ቤቶች መልስ፣የመልስ መልስ፣ አስተያየቶች ፣የትዕዛዝ ውጤቶች ለመቀበል የተቀጠሩ፣ እልባት ለመስጠት ጥቂት ሂደት ብቻ የሚቀራቸው ጉዳዮች እንዲሁም እስረኛ ያላቸው መዛግብት በየቀጠሮ ቀናቸው የማስተናገድ፤
 ማስረጃ ለመስማት' ክስ ለመስማት የተቀጠሩ መዝገቦች በጣም አስቸኳይነታቸዉ በዳኛው፣ በየፍርድ ቤቱ በየደረጃው በሚገኝ አመራር እስካልታመነ ድረስ ለቀጣይ የ2013 በጀት ዓመት የሚቀጠር ይሆናል ሆኖም ግን ከዚህ በፊት በተሰጡት መመሪያዎች መሰረት ሲከናወኑ የነበሩ ተረኛ ችሎቶችን በማደራጀት በአመራሩ የተለዩ ወሳኝ እና አንገብጋቢ ጉዳዮች በተለይም ከዜጐች የሰብዓዊ መብት ጋር የተቆራኙ ጉዳዮችን፣ ከቤት ውስጥ ጥቃት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን፣ እግድ፣ በስምምነት ፍች፣ ጥፋት ውስጥ ገብተው የተገኙ ወጣቶች (ወጣት ጥፋተኞች)፣ የልጆች አስተዳደግ እና ቀለብን የመሠሉ የቤተሰብ ጉዳዮች፣ አፋጣኝ የወንጀል ጉዳዮች (RTD) ከአስቸኳይ ግዜ አዋጅ አፈፃፀም ጋር የተያያዘ የወንጀል ጉዳዮችን፣ በስምምነት ክስን ማቋረጥ፣ ከትላልቅ ሜጋ ኘሮጀክቶች ጋር የተያያዙ የንግድ ኢንቨስትመንት ጉዳዮች፣ ከሀገር ፀጥታ እና ሠላም ጋር የተያያዙ የወንጀል ጉዳዮች እንዲሁም ብዙ ተካራካሪ የሌላቸው መዛግብትን የሚስተናገዱ ሲሆን በመደበኛ ችሎት ሲስተናገዱ የነበሩ የስራ ክርክር፣ የሴቶች እና ህፃናት ችሎቶች፣ የሁከት እና ሌሎች የአስተዳደር ጉዳዮች በመደበኛ ችሎት ዳኞች በየቀጠሯቸው የሚስተናገዱ ይሆናል፡፡
 በየደረጃው ያሉ የፍርድ አፈጻጸም ችሎቶች በአጭርና በቀላሉ የሚፈፀሙ የአፈፃፀም ጉዳዮችን ማስተናገድ የሚጀምሩ ይሆናል፡፡ ከዚህ በተያያዘም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ አፈጻጸም ዳይሬክቶሬት ከሐምሌ 13/2012ዓ.ም ጀምሮ መደበኛ ስራውን የሚጀምር ሲሆን በፍርድ አፈፃፀም ምክንያት ከመኖሪያ ቤት ማስለቀቅ፣ የመኖሪያ ቤት ሽያጭ ማጫረት ማካሄድ ውስብስብነት ያላቸውና የሰዎች መሰባሰብ የሚጠይቁ የአፈፃፀም ጉዳዮች ተለዋጭ የስራ አቅጣጫ እስከሚሰጥ ድረስ ባሉበት ደረጃ እንዲቆዩ ይደረጋል፡፡
 የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በአዲስ አበባ ከሚገኙ ባለጉዳዮች የሚቀርቡ የሰበር አቤቱታዎችን የሚያሥተናግድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ከአዲስ አበባ ውጪ የሚገኙ ባለጉዳዮችን በዚህ ወቅት ማስተናገድ ለኮቪድ 19 ወረርሽኝ ያላቸውን ተጋላጭነት የሚጨምር መሆኑን ታሳቢ በማድረግ የወረርሽኙ ስርጭት አስጊነት በቀነሰና ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ የስራ አቅጣጫ በሚሰጥበት ጊዜ የሚስተናገዱ ይሆናል፡፡
 በሁሉም ፍርድ ቤቶች የምርመራ መዛግብት የማጥራት ተግባር በተጨማሪነት የሚከናወን ይሆናል፡፡
2. በነሀሴ ወር 2012 ዓ.ም የሚሰጡ አገልግሎቶች
 በሁሉም ደረጃ ባሉት ፍ/ቤቶች አዲስ መዝገቦችን ማለትም ቀጥታ ክስ፣ ይግባኝ እና አፈፃፀም መዝገቦችን የመክፈት አገልግሎት ይጀመራል፡፡
 ዳኞች በየዓመቱ በነሐሴ ወር እረፍት የሚወስዱ የነበረ ቢሆንም ወደፊት በዳኝነት ስራ ላይ የሚፈጠረውን የስራ ጫና ለማቃለል እንዲረዳ ዳኞች በስራ ገበታቸው በመገኘት አዲስ የሚከፈቱ መዝገቦችን በመመርመር በጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መርህ መሰረት ቀጠሮ ወይም ተገቢውን ትእዛዝ የሚሰጡ ይሆናል፡፡
 አስቸኳይነት ያላቸው ጉዳዮች ማለትም ቀደም ሲል በተረኛ ችሎት ሲስተናገዱ የነበሩ ጉዳዮች በተረኛ ችሎት መስተናገዳቸውን ይቀጥላሉ፡፡
 የምርመራ መዛግብት የማጥራት ስራ በተጨማሪነት የሚከናወን ይሆናል፡፡
3. በመስከረም ወር 2013 ዓ.ም የሚሰጡ አገልግሎቶች
 የመስከረም ወር 2013ዓ.ም የዳኞች የእረፍት ጊዜ ይሆናል፡፡
 አስቸኳይ ጉዳዮች ማለትም በተረኛ ችሎት ሲስተናገዱ የነበሩ ጉዳዮች እስከ መስከረም 30/2013ዓ.ም በተረኛ ችሎት የሚስተናገዱ ይሆናል፡፡
ፍርድ ቤቶች አብዛኛውን አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ተከትሎ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል በሁሉም ፍርድ ቤቶች በአስገዳጅነት ሊተገበሩ የሚገባቸዉ የጥንቃቄ እርምጃዎች
1. በቀጣይ የሚሰጡ አገልግሎቶች ቢያንስ ሁለት ሜትር ርቀትን በጠበቀ ሁኔታ እንዲከናወን ማድረግ፤
2. ሰራተኞችም ይሁኑ ተገልጋዮች የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ እንዲጠቀሙ ማድረግ፤
3. ለፍ/ቤቱ ማህበረሰብና ለተገልጋይ የሚያገለግሉ የንፅህና መጠበቂያ ግብአቶችን እንደ የእጅ ንፅህና መጠበቂያ ውሃ፣ ሳሙና፣ አልኮል እና ሳኒታይዘር የመሳሰሉትን ማሟላትና እንዲጠቀም ማድረግ፡፡
4. ተገልጋይም ሆነ የፍ/ቤቱ ማህበረሰብ ወደ ግቢ ከመግባቱ በፊት የሙቀት መጠን እንዲለካ ማድረግና የሙቀት መጠኑ ከ38 ዲግሪ በላይ ከሆነ ተለይቶ ማቆየት እና በአቅራቢያው ለሚገኙ ጤና ጣቢያዎች ማሳወቅ፡፡
5. በየእለቱ ቀጠሮ ካላቸዉ ተከራካሪ ወገኖች እና የፍ/ቤቱን ሌሎች አገልግሎት ፈልገው የሚመጡ ባለጉዳዮች ብቻ ወደ ፍ/ቤቱ ግቢ እንዲገቡ ማድረግ፡፡
6. በየደረጃው ባሉ ፍ/ቤቶች በሚወሰን ግዜ በመደበኛነት የኮቪድ 19 ተጋላጭነት ለመከላከል የፀረ-ተሀዋሲያን ርጭት ማከናወን፡፡
7. የፍ/ቤቱ አመራር የሚያወጣቸውን ተጨማሪ የጥንቃቄ እርምጃዎች በጥብቅ መተግበር ይሆናል፡፡
የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመከላከል በጤና ባለሙያዎች የሚሰጡ ምክሮችን በጥብቅ በመተግበር ከወረርሽኙ ራሳችንን፤ ቤተሰቦቻችንንና ሃገራችን ከችግር እንታደግ!!
----------------------- // ----------------------------
የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ግልባጭ፡-
 ለክብርት ፕሬዝደንት ጽ/ቤት
ፌ/ጠ/ፍ/ቤት
news release.pdf
1.7 MB
በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከሀምሌ 13/2012 ዓ.ም ጀምሮ ስለሚሰጡ ተጨማሪ የዳኝነት አገልግሎቶች የተሰጠ መግለጫ
ከፍተኛ ጥንቃቄ!

#SHARE #ሼር

በኢትዮጵያ የምትኖሩ የቲክቫህ አባላት፣ ይህን መልዕክት የኢንተርኔት አገልግሎት አግኝታችሁ ማንበብ የቻላችሁ በሙሉ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በከፍተኛ ደረጃ በሀገሪቱ እየተሰራጨ በመሆኑ ጥንቃቄ አድርጉ።

ኢትዮጵያ የመመርመር አቅሟን እያሣደገች መጥቱን ተከትሎ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል።

በሀገሪቱ በሁለት ቀናት #ብቻ (ሀምሌ 9/2012 እና ሀምሌ 10/2012) 672 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በምርመራ ተረጋግጧል።

በኢትዮጵያ የሟቾች ቁጥርም እየጨመረ መጥቷል በትላንት እንዲሁም በዛሬ ሪፖርት መሰረት 15 ሰዎች ከቫይረሱ ጋር በተገናኘ ህይወታቸውን አጥተዋል።

ይህንን መልዕክት በስልካችሁ ያገኛቹ ወገኖቻችን እራሳችሁ እና ቤተሰባችሁን በሙሉ ከዚህ አስፈሪ ወረርሽኝ ሳትዘናጉ እንድትጠብቁ ጥሪ እናቀርባለን ፤ ኢንተርኔት ማግኘት ላልቻሉ ወዳጆቻችሁ በSMSና በመደወል አሳሳቢውን ሁኔታ አሳውቋቸው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የፌደራል ፍርድ ቤቶች ሙሉ አገልግሎት ሊሰጡ ነው!

የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከሐምሌ 13/2012 ዓ/ም እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ኮቪድ-19ን እየተከላከሉ ሙሉ አገልግሎት ሊሰጡ መሆኑ ኢቢሲ ዘግቧል።

ከመጪው ሰኞ ሐምሌ 13 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ዳኞች በመደበኛ የስራ ሰዓት ቢሮ ገብተው አንገብጋቢ የሆኑ ጉዳዮችን በመለየት ክስ መስማት ፤ ምርመራቸው በተገባደደ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ መስጠት እና የመሳሰሉ ስራዎችን ያከናውናሉ ተብሏል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia