" የተርሚናል አገልግሎት ክፍያው የሚፈጸመው ማህበራቱ በስኬት ባንክ በከፈቷቸው አካውንቶች በቴሌብር አማካኝነት ነው " - ማህበራቱ
ነባር ተራ እስከባሪዎችን በመተካት የተርሚናል አስተዳደር እና ቁጥጥር ስልጠና የወሰዱ ከ 80 በላይ በሚሆኑ ማህበራት(ኢንተርፕራይዝ) የተደራጁ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ዛሬ ከሰአት ስራ ጀምረዋል።
ዛሬ ጠዋት የአዲስ አበባ ከተማ ስራ እና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ፣የአዲስ አበባ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እና የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ያብባል አዲስ በተገኙበት የተመረቁት 996 የታክሲ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ከሰአት በኋላ ስራ መጀመራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።
ነባሮቹን ተራ አስከባሪ ወጣቶች በመተካት ከዛሬ ጀምሮ ወደ ስራ የገቡት ወጣቶች በየወረዳው የተደራጁ ሲሆን በከተማዋ በሚገኙ 87 ተርሚናሎች ወደ ስራ ገብተዋል።
የተርሚናል አገልግሎት ክፍያው የሚፈጸመው ማህበራቱ በስኬት ባንክ በከፈቷቸው አካውንቶች በቴሌብር አማካኝነት መሆኑን ቲክቫህ ያነጋገራቸው የማህበራቱ አባላት ገልጸዋል።
ለትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ በሚል ከትላንት ጀምሮ የተበተነው እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው በራሪ ወረቀት የተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በየትኛውም መነሻ እና መድረሻ ላይ 10 ብር መሆኑን በመግለጽ ክፍያውንም በዲጂታል መንገድ ብቻ እንዲፈጸም ይጠይቃል።
በተጨማሪም ከተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በላይ የከፈለ አሽከርካሪም ሆነ ረዳት 4000 ብር እንደሚቀጡ ይገልጻል።
ነባር ተራ አስከባሪዎች በመረጡት የስራ ዘርፍ እንዲሰማሩ አስፈላጊው ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ነባር ተራ እስከባሪዎችን በመተካት የተርሚናል አስተዳደር እና ቁጥጥር ስልጠና የወሰዱ ከ 80 በላይ በሚሆኑ ማህበራት(ኢንተርፕራይዝ) የተደራጁ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ዛሬ ከሰአት ስራ ጀምረዋል።
ዛሬ ጠዋት የአዲስ አበባ ከተማ ስራ እና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ፣የአዲስ አበባ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እና የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ያብባል አዲስ በተገኙበት የተመረቁት 996 የታክሲ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ከሰአት በኋላ ስራ መጀመራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።
ነባሮቹን ተራ አስከባሪ ወጣቶች በመተካት ከዛሬ ጀምሮ ወደ ስራ የገቡት ወጣቶች በየወረዳው የተደራጁ ሲሆን በከተማዋ በሚገኙ 87 ተርሚናሎች ወደ ስራ ገብተዋል።
የተርሚናል አገልግሎት ክፍያው የሚፈጸመው ማህበራቱ በስኬት ባንክ በከፈቷቸው አካውንቶች በቴሌብር አማካኝነት መሆኑን ቲክቫህ ያነጋገራቸው የማህበራቱ አባላት ገልጸዋል።
ለትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ በሚል ከትላንት ጀምሮ የተበተነው እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው በራሪ ወረቀት የተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በየትኛውም መነሻ እና መድረሻ ላይ 10 ብር መሆኑን በመግለጽ ክፍያውንም በዲጂታል መንገድ ብቻ እንዲፈጸም ይጠይቃል።
በተጨማሪም ከተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በላይ የከፈለ አሽከርካሪም ሆነ ረዳት 4000 ብር እንደሚቀጡ ይገልጻል።
ነባር ተራ አስከባሪዎች በመረጡት የስራ ዘርፍ እንዲሰማሩ አስፈላጊው ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia