ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎቹ ስለ አፍሌክስ በተደረገላቸው ገለጻ አመስግነው ከአፍሌክስ ጋር አብረው ለመስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ሀሳብ ሰጥተዋል።
የ UNDP, UNIDO, UNESCO, እና UN ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ካነሷቸው ጥያቄና አስተያየቶች መካከል አካዳሚው አፍሪካዊ ቅርጽ እና ይዘት እንዲኖረው በሚደረገው ሪፎርም፤ ማስፋት እና ሽግግር ዙሪያ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ኤምባሲዎች እና ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ጋር አብሮ ለመስራት ስላቀደው ዕቅድ፤ የማስተርስ ዲግሪዎቹን በተመለከተ ስላለው ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ዕውቅና፤ የአመራር ልማት ፕሮግራሙን ወደ ስራ ለመቀየር ያለው ዝግጅት ምን እንደሚመስል፤ እና ከሌሎች አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በምን መልኩ ለመስራት እንደታቀደ የጠየቁ ሲሆን አቶ ዛዲግ አብርሃ ማብራሪያ ሰጥተዋቸዋል።
ከ UNDP, UNIDO, UNESCO, እና UN ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ከአፍሌክስ ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን እና ዝርዝር ጥናት በማድረግ ዽጋፍ በተጠየቁባቸው መስኮች አብረው ለመስራት ተስማምተዋል። የአካዳሚውን ፋሲሊቲም ጎብኝተዋል።
የ UNDP, UNIDO, UNESCO, እና UN ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ካነሷቸው ጥያቄና አስተያየቶች መካከል አካዳሚው አፍሪካዊ ቅርጽ እና ይዘት እንዲኖረው በሚደረገው ሪፎርም፤ ማስፋት እና ሽግግር ዙሪያ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ኤምባሲዎች እና ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ጋር አብሮ ለመስራት ስላቀደው ዕቅድ፤ የማስተርስ ዲግሪዎቹን በተመለከተ ስላለው ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ዕውቅና፤ የአመራር ልማት ፕሮግራሙን ወደ ስራ ለመቀየር ያለው ዝግጅት ምን እንደሚመስል፤ እና ከሌሎች አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በምን መልኩ ለመስራት እንደታቀደ የጠየቁ ሲሆን አቶ ዛዲግ አብርሃ ማብራሪያ ሰጥተዋቸዋል።
ከ UNDP, UNIDO, UNESCO, እና UN ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ከአፍሌክስ ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን እና ዝርዝር ጥናት በማድረግ ዽጋፍ በተጠየቁባቸው መስኮች አብረው ለመስራት ተስማምተዋል። የአካዳሚውን ፋሲሊቲም ጎብኝተዋል።
የኢትዮጵያ መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች በአፍሪካ አመራር ልህቀት ቅጥር ውስጥ ለሚያሰሩት የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ግንባታ የመስክ ምልከታ አደረጉ።
በክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር የተመራው ልዑክ በአፍሌክስ ውስጥ ለሚሰራው Center for Medemer and African Integration ማዕከል ግንባታ የሚሆነውን ቦታ ተመልክተዋል።
በመስክ ምልከታው ላይ ግንባታውን የሚያከናውነው ኮንትራክተርም ተገኝቶ የቦታውን የቀደመ ዲዛይን እና አሁን ያለበትን ሁኔታ ተመልክቶአል።
በክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር የተመራው ልዑክ በአፍሌክስ ውስጥ ለሚሰራው Center for Medemer and African Integration ማዕከል ግንባታ የሚሆነውን ቦታ ተመልክተዋል።
በመስክ ምልከታው ላይ ግንባታውን የሚያከናውነው ኮንትራክተርም ተገኝቶ የቦታውን የቀደመ ዲዛይን እና አሁን ያለበትን ሁኔታ ተመልክቶአል።
የራሺያ ሳይንስ እና ባህል ማዕከል ከፍተኛ አመራሮች የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን የአመራር ልማት ፕሮግራም እንደሚደግፉ ገለጹ።
ስለ አፍሌክስ የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስትራቴጂም ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል። በሱሉልታ የሚገኘውን የአመራር ልማት ማዕከልንም ጎብኝተዋል።
የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስትራቴጂ ላይ ሰፊ ገለጻ ያደረጉት የአፍሌክስ የውስጥና የውጭ ግንኙነት ቡድን መሪ አቶ ዮሐንስ ሣሀለማሪያም ሲሆኑ አካዳሚው ከራሺያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና የምርምር ማእከላት ጋር በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳለው ጠቅሰው የሳይንስ እና ባህል ማዕከሉ በራሺያ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና የስልጠና ማዕከላት ጋር ለሚኖረው ስትራቴጂያዊ ትስስር እና ትብብር የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ አቶ ዮሐንስ ጠይቀዋል።
የራሺያ ሳይንስ እና ባህል ማዕከል ዳይሬክተር አሌክሳንደር ኤቭጊየስትኔቭ በበኩላቸው አካዳሚው ሊተገብራቸው ያቀዳቸው የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስትራቴጂ እቅድ ለአገሪቱ ብቻ ሳይሆን እንደ አህጉር ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን በማመን በራሺያ ከሚገኙ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አመራሮች እና የስራ ክፍሎች ጋር በመወያየት ይህንን ራዕይ እንደሚያስገነዝቡና ለስኬቱም በቅርቡ ወደ ስራ እንደሚገቡ አስረድተዋል፡፡
ስለ አፍሌክስ የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስትራቴጂም ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል። በሱሉልታ የሚገኘውን የአመራር ልማት ማዕከልንም ጎብኝተዋል።
የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስትራቴጂ ላይ ሰፊ ገለጻ ያደረጉት የአፍሌክስ የውስጥና የውጭ ግንኙነት ቡድን መሪ አቶ ዮሐንስ ሣሀለማሪያም ሲሆኑ አካዳሚው ከራሺያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና የምርምር ማእከላት ጋር በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳለው ጠቅሰው የሳይንስ እና ባህል ማዕከሉ በራሺያ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና የስልጠና ማዕከላት ጋር ለሚኖረው ስትራቴጂያዊ ትስስር እና ትብብር የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ አቶ ዮሐንስ ጠይቀዋል።
የራሺያ ሳይንስ እና ባህል ማዕከል ዳይሬክተር አሌክሳንደር ኤቭጊየስትኔቭ በበኩላቸው አካዳሚው ሊተገብራቸው ያቀዳቸው የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስትራቴጂ እቅድ ለአገሪቱ ብቻ ሳይሆን እንደ አህጉር ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን በማመን በራሺያ ከሚገኙ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አመራሮች እና የስራ ክፍሎች ጋር በመወያየት ይህንን ራዕይ እንደሚያስገነዝቡና ለስኬቱም በቅርቡ ወደ ስራ እንደሚገቡ አስረድተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አያይዘውም አሌክሳንደር ኤቭጊየስትኔቭ ራሺያ በተለያዩ ዘርፎች የስመጥር ምሁራንና ተመራማሪዎች መፍለቂያ መሆኗን ገልጸው፤ በአገራቸው ከሚገኙ አንጋፋ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የምርምር ማዕከላት ጋር አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን እና ከአካዳሚው በሚቀርቡ ክፍተትን መሰረት ያደረጉ የስልጠና፤ የጥናትና ምርምር እንዲሁም የማማከር ፍላጎቶች አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል፡፡
በተለይም የሱሉልታ የአመራር ልማት ማዕከልን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ በተያዘው ዕቅድ ላይ ራሺያ የበኩሏን እገዛ እንደምታደርግ በመግለጽ የተለያዩ አለምአቀፍ ፎረሞችና ኮንፈረንሶችን በማዕከሉ ለማድረግ ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል፡፡
በተለይም የሱሉልታ የአመራር ልማት ማዕከልን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ በተያዘው ዕቅድ ላይ ራሺያ የበኩሏን እገዛ እንደምታደርግ በመግለጽ የተለያዩ አለምአቀፍ ፎረሞችና ኮንፈረንሶችን በማዕከሉ ለማድረግ ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል፡፡
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በአፍሌክስ የአመራር ልማት ቅጥር ውስጥ የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ለመገንባት ወሰነ።
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ክቡር ሚኒስትሩ ገብረ መስቀል ጫላ ውሳኔውን ያሳወቁት ከአፍሌክስ ጋር በምን መልኩ መስራት እንደሚቻል ጥናት እንዲያደርግ የተቋቋመው ቴክኒካል ኮሚቴ ያቀረበውን መነሻ ሀሳብ ከተመለከቱ በኋላ ሲሆን የንግዱን እና የቀጠናዊ ትስስር ስራዎችን ለማጎልበት የሚያግዝ የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል በአፍሪካ አመራር ልህቀት ቅጥር ውስጥ ለመገንባት ተቋማቸው እንደወሰነ ተናግረዋል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው በአመራር ልማት ዘርፍ የራሱን አሻራ ማሳረፍ እንደሚፈልግ የጠቆሙት ክቡር ሚኒስትሩ የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ለመደገፍ፤ በንግድ ዘርፍ እና በቀጠናዊ ትስስር የተሰማሩ ባለሀብቶችን በማስተባበር በርካታ አገልግሎትን በአንድ የያዘ ዘመናዊ የጥናት እና ምርምር ማዕከል በመገንባት፤ ሳይንሳዊ እና ችግር ፈች ሀሳቦችን ማፍለቅ እንደሚቻል ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል። የሚገነባው ማዕከልም የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራን ጨምሮ ሁሉንም መሰረታዊ አገልግሎቶች የሚሰጥ እንዲሆን እንደሚፈልጉ ክቡር ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በአፍሌክስ የሽልማት መስክም ቴክኒካል ኮሚቴው ካቀረበው መነሻ ጥናት በተጨማሪ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዲካተቱ የሚፈልጋቸው የአፍሌክስ የአመራር የሽልማት ዘርፎች እንዳሉ የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትሩ በተለይም ምርጥ ተመራማሪ፤ የንግድ ባለሙያ፤ የንግድ መሪ፤ የተቋም መሪ፤ ጅምላ ነጋዴ፤ ችርቻሮ ነጋዴዎች ተወዳድረው የሚሸለሙበት እንዲሆን ሀሳብ አቅርበዋል።
በሚኒስትር ዲኤታ የሚመራ የሀብት አፈላላጊ እና አሰባሳቢ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን የቴክኒክ ኮሚቴውም የተሰጡትን ተግባራት አጠናቆ በአስራ አምስት ቀናት ይዞ እንዲቀርብ ክቡር ሚኒስትሩ ገብረ መስቀል ጫላ ተናግረዋል።
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ክቡር ሚኒስትሩ ገብረ መስቀል ጫላ ውሳኔውን ያሳወቁት ከአፍሌክስ ጋር በምን መልኩ መስራት እንደሚቻል ጥናት እንዲያደርግ የተቋቋመው ቴክኒካል ኮሚቴ ያቀረበውን መነሻ ሀሳብ ከተመለከቱ በኋላ ሲሆን የንግዱን እና የቀጠናዊ ትስስር ስራዎችን ለማጎልበት የሚያግዝ የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል በአፍሪካ አመራር ልህቀት ቅጥር ውስጥ ለመገንባት ተቋማቸው እንደወሰነ ተናግረዋል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው በአመራር ልማት ዘርፍ የራሱን አሻራ ማሳረፍ እንደሚፈልግ የጠቆሙት ክቡር ሚኒስትሩ የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ለመደገፍ፤ በንግድ ዘርፍ እና በቀጠናዊ ትስስር የተሰማሩ ባለሀብቶችን በማስተባበር በርካታ አገልግሎትን በአንድ የያዘ ዘመናዊ የጥናት እና ምርምር ማዕከል በመገንባት፤ ሳይንሳዊ እና ችግር ፈች ሀሳቦችን ማፍለቅ እንደሚቻል ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል። የሚገነባው ማዕከልም የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራን ጨምሮ ሁሉንም መሰረታዊ አገልግሎቶች የሚሰጥ እንዲሆን እንደሚፈልጉ ክቡር ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በአፍሌክስ የሽልማት መስክም ቴክኒካል ኮሚቴው ካቀረበው መነሻ ጥናት በተጨማሪ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዲካተቱ የሚፈልጋቸው የአፍሌክስ የአመራር የሽልማት ዘርፎች እንዳሉ የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትሩ በተለይም ምርጥ ተመራማሪ፤ የንግድ ባለሙያ፤ የንግድ መሪ፤ የተቋም መሪ፤ ጅምላ ነጋዴ፤ ችርቻሮ ነጋዴዎች ተወዳድረው የሚሸለሙበት እንዲሆን ሀሳብ አቅርበዋል።
በሚኒስትር ዲኤታ የሚመራ የሀብት አፈላላጊ እና አሰባሳቢ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን የቴክኒክ ኮሚቴውም የተሰጡትን ተግባራት አጠናቆ በአስራ አምስት ቀናት ይዞ እንዲቀርብ ክቡር ሚኒስትሩ ገብረ መስቀል ጫላ ተናግረዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ በበኩላቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የአፍሪካ አመራር ልህቀትን የአመራር ልማት ፕሮግራም እና የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ለመደገፍ ያሳለፈውን ውሳኔ አድንቀው ለስራው መሳካት ከአፍሌክስ የሚጠበቀውን ሁሉ በማድረግ ትብብሩን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ እንደሚሰሩ አምባሳደሮች ተናገሩ።
ኢትዮጵያን ወክለው በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ለሚሰሩ አምባሳደሮች፤ ሚሲዮኖች እና ዲፕሎማቶች ስለ አፍሌክስ የአመራር ልማት ፕሮግራም እና የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለአምባሳደሮች፤ ለሚሲዮኖች እና ለዲፕሎማቶች ስለ አፍሌክስ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች እና የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ሰፊ ገለጻ ያቀረቡ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎችም አብራርተዋል።
አቶ ዛዲግ አፍሌክስ የጀመረውን የአመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳካት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመሆን ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ አስታውሰው፤ በተለይም ከአውሮፓ እና አሜሪካ፤ ከእስያ፤ ከመካከለኛው ምስራቅ፤ ከላቲን አሜሪካ እና ከአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራሎች ጋር በመሆን አፍሌክስን የማስተዋወቅ እና ሀብት የማፈላለጉ ተግባር ውጤት እያመጣ እንደሆነ ገልጸው፤ በስራው ላይ ትብብር ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ኢትዮጵያን በመወከል በመላው ዓለም የሚሰማሩ አምባሳደሮች፤ ሚሲዮኖች እና ዲፕሎማቶችም የአፍሌክስን ተልእኮ እና ራዕይ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በማስተዋወቅ የቴክኒክ፤ የዕውቀት እና የገንዘብ ድጋፍ የሚገኝበትን መንገድ እንዲያመቻቹ አቶ ዛዲግ አብርሃ ጥሪ አቅርበዋል።
ገለጻውን የተከታተሉ አምባሳደሮች፤ ዲፕሎማቶች እና ሚሲዮኖች በበኩላቸው አፍሌክስ ይዞ የተነሳውን ራዕይ አድንቀው፤ አዲስ የተቀረጸውን የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፍ ለመደገፍ በየተመደቡበት ሀገራት ያለውን ሁኔታ በማጥናት እና ለአፍሌክስ የሚሆኑትን በመለየት ስትራቴጂያዊ አጋርነት እና ሀብት የሚገኝበትን መንገድ እንደሚያመቻቹ ተናግረዋል።
በተለይም የፓኪስታን፤ የጀርመን፤ የዩናይትድ ኪንግደም፤ የመካከለኛው ምስራቅ እና የሞሮኮ አምባሳደሮች እንደተናገሩት አፍሌክስ ኢትዮጵያን እና አፍሪካን እንደ ድልድይ ሆኖ ለማገናኘት የጀመረውን ጥረት ለማገዝ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያን ወክለው በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ለሚሰሩ አምባሳደሮች፤ ሚሲዮኖች እና ዲፕሎማቶች ስለ አፍሌክስ የአመራር ልማት ፕሮግራም እና የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለአምባሳደሮች፤ ለሚሲዮኖች እና ለዲፕሎማቶች ስለ አፍሌክስ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች እና የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ሰፊ ገለጻ ያቀረቡ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎችም አብራርተዋል።
አቶ ዛዲግ አፍሌክስ የጀመረውን የአመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳካት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመሆን ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ አስታውሰው፤ በተለይም ከአውሮፓ እና አሜሪካ፤ ከእስያ፤ ከመካከለኛው ምስራቅ፤ ከላቲን አሜሪካ እና ከአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራሎች ጋር በመሆን አፍሌክስን የማስተዋወቅ እና ሀብት የማፈላለጉ ተግባር ውጤት እያመጣ እንደሆነ ገልጸው፤ በስራው ላይ ትብብር ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ኢትዮጵያን በመወከል በመላው ዓለም የሚሰማሩ አምባሳደሮች፤ ሚሲዮኖች እና ዲፕሎማቶችም የአፍሌክስን ተልእኮ እና ራዕይ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በማስተዋወቅ የቴክኒክ፤ የዕውቀት እና የገንዘብ ድጋፍ የሚገኝበትን መንገድ እንዲያመቻቹ አቶ ዛዲግ አብርሃ ጥሪ አቅርበዋል።
ገለጻውን የተከታተሉ አምባሳደሮች፤ ዲፕሎማቶች እና ሚሲዮኖች በበኩላቸው አፍሌክስ ይዞ የተነሳውን ራዕይ አድንቀው፤ አዲስ የተቀረጸውን የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፍ ለመደገፍ በየተመደቡበት ሀገራት ያለውን ሁኔታ በማጥናት እና ለአፍሌክስ የሚሆኑትን በመለየት ስትራቴጂያዊ አጋርነት እና ሀብት የሚገኝበትን መንገድ እንደሚያመቻቹ ተናግረዋል።
በተለይም የፓኪስታን፤ የጀርመን፤ የዩናይትድ ኪንግደም፤ የመካከለኛው ምስራቅ እና የሞሮኮ አምባሳደሮች እንደተናገሩት አፍሌክስ ኢትዮጵያን እና አፍሪካን እንደ ድልድይ ሆኖ ለማገናኘት የጀመረውን ጥረት ለማገዝ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።