African Leadership Excellence Academy
2.14K subscribers
2.38K photos
89 videos
6 files
104 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
#ኢትዮጵያ በመጪዎቹ ዓመታት #የኢኮኖሚ_እመርታ እንደምታስመዘግብ ተገለፀ።
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 11ቀን ፣2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ ኢትዮጵያ በመጪዎቹ አራት አስርተ አመታት ከፍተኛ የኢኮኖሚ እመርታ እንደምታስመዘግብ የፕላንና ልማት ሚንስትር ክብርት ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ በሚሰጠው ስልጠና ላይ ገለፁ።
የትንበያ ጥናቱ ከሀገራችን የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ባሻገር የውጭ ሀገራት ባለሙያዎችም ያረጋገጡት ነው ብለዋል።
ክብርት ዶ/ር ፍፁም ይህን የተናገሩት "እመርታ ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደ ተሟላ ብልፅግና" በሚል ርዕስ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽህፈት ቤቶች አመራሮች እየተሰጠ ባለው ሥልጠና ላይ ባቀረቡት ገለፃ ነው።
ሀገራት ባላቸው የነፍስ ወከፍ ገቢ፣ ከሚያመርቱት ምርትና ከሚጠቀሙት ቴክኖሎጂ አንፃር ከፍተኛ፣ መካከለኛ እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሀገራት ተብለው በሶስት እንደሚከፈሉ አብራርተዋል።
ክብርት ዶ/ር ፍፁም ሀገራችን አሁን ላይ በአፍሪካ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ካስመዘገቡ ሀገራት በ5ኛ ደረጃ፣ ከሰሃራ በታች ካሉት ሀገራት በ3ኛ እና ከምስራቅ አፍሪካ ደግም ቀዳሚውን ደረጃ መያዟን አስገንዝበዋል።
በአለም ባንክ በተደረጉ ጥናቶች ኢትዮጵያ በ2021 እና በ2022 ዓ.ም. በአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ዕድገት ከሚያስመዘግቡ ሀገራት 2ኛ ደረጃን እንደምትይዝ መጠቆሙን አብራርተዋል።
ክብርት ዶ/ር ፍፁም አሁን ላይ ኢትዮጵያ ካላት የተፈጥሮ ሀብት፣ የሰው ሀይል፣ ይሄንን ማስፈፀም የሚችል መንግስት አኳያ ህልሟን እውን የማታደርግበት አንዳች ምክንያት እንደማይኖርም ነው ያስረዱት።
ስልጠናው ዛሬም #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ለ5ኛ ቀን ቀጥሏል።
አሁን ላይ በዓለም በተፈጠረው ዘርፈ ብዙ የእርስ በርስ ትስስር፣ የተፈጥሮ ሀብትን በከፍተኛ ደረጃ መጠቀም እና ከፍተኛ የቴክኖሎጂ ዕድገትና ጥቅም ላይ መዋል ዓለም በፉክክርና እና በውጥረት ላይ እንድትጠመድ ማድረጉም ተመላክቷል።
በቅርቡ #በራሺያና #በዩክሬን መካከል በተፈጠረው ጦርነት ታዳጊ ሀገራት የምግብ ግብአቶችን እና ማዳበሪያን ወደ ሀገራቸው እንዳያስገቡ በማድረጉ የኢኮኖሚ ጫና መፍጠሩ ተገልጿል።
#ኢትዮጵያም በተፈጠሩ ዓለም አቀፍ ጫናዎች ውስጣዊ አቅሟን በማጠናከር በተለይ ስንዴንና ሌሎች የሀገር ውስጥ ምርቶችን በከፍተኛ ደረጃ በማምረት መቋቋም የተቻለ ቢሆንም በቀጣይም በቀጠናው በተለይ በቀይ ባህር አካባቢ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተገቢው መንገድ በመረዳት ከጊዜው ጋር የሚመጥን የራሷን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ እንደሚኖርባትም ነው #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ የተብራራው።
አሁን ላይ በኢኮኖሚው እና በውጭ ግንኙነት ረገድ የተሻለ ደረጃ ላይ የሚገኙት እንደ #ቻይና#ሕንድ#ቱርክና ሌሎች ቀደምት ሥልጣኔ ያላቸው ሀገራት መሆኑ ተጠቁሟል።
ከዚህ አኳያ #ኢትዮጵያም_ቀደምት_የስልጣኔ_ሀገር ከመሆኗም ባሻገር #በቅኝ_ያልተገዛች#በኢኮኖሚ_እያደገች የመጣችና #የብሪክስ_ሀገራት አባል መሆን የቻለች፣ #ከአፍሪካ ትልቅ ሕዝብና የመልማት አቅም ያላት፣ በቀጠናው ተቀባይነት ያላትና ተፅእኖ ፈጣሪ የሆነች እንዲሁም ከፍተኛና ጥብቅ ማህበራዊ ትስስር ያላት ሕዝብ ባለቤት እንዲሁም #በአፍሪካ_አንድነት_ጉልህ_ድርሻ ያላት በመሆኗ በዓለም ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሀገር የመሆን ዕድሏ ሰፊ መሆኑ ተብራርቷል።
ስለሆነም #ኢትዮጵያ በውስጥ ያሉባትን ትንንሽ አለመግባባቶችን በጠረጴዛ ዙሪያ በውይይት በመፍታት #ገጽታዋን_መገንባት እና #የውጭ_ግንኙነት_እመርታዋን_ማረጋገጥ እንደሚኖርባት #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ እየቀረበ ካለው ገለፃ ለመረዳት ተችሏል ።
(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)
#ኢትዮጵያ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን እምርታ በማረጋገጥ ላይ መሆኗ ተመለከተ::

#ኢትዮጵያ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን እምርታ በማምጣት ላይ መሆኗን ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ #ተመስገን_ጥሩነህ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አመላከቱ።

ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን በመገንባት ረገድ የረጅም ጊዜ ባለ ታሪክ መሆኗንም ገልፀዋል።

የዛሬው የሥልጠና ርዕሰ ጉዳይ "የፀጥታና ደህንነት እመርታ" የሚል ሲሆን በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤቶች አመራሮች የሥልጠናው ገለፃ በክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ ቀርቧል።

ክቡር ም/ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ባቀረቡት ገለፃ ሀገራችን የፀጥታና የደህንነት ተቋማትን በመገንባት ረጅም አመታትን ማስቆጠር ብቻ ሳይሆን እነዚህ ተቋማት የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ከማስጠበቅ አልፈው እንደ ኮሪያ፣ ኮንጎ እና በሌሎች ሀገራት በመሰማራት ሰላም የማስከበር ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን መወጣት የቻሉ ናቸው ብለዋል።

ተቋማቱ የየራሳቸው ጥንካሬ ቢኖራቸውም የነበረባቸው ክፍተት ሊያርም በሚችል መልኩ አሁን ላይ በክቡር ጠቅላይ ሚንስትሩ አነሳሽነት ወቅቱን በሚመጥን ደረጃ የሪፎርም ሥራ በመሠራቱ ከፍተኛ አቅም ለመፍጠር ተችሏል ሲሉ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ በሚሰጠው ስልጠና ላይ ተናግረዋል።
With just Two days to go until the Netsebrak Leadership Conference, remember our motto: 🧭Leading with Purpose, Serving with Integrity!

Get ready to:

🔹Engage
🔹Learn
🔹And connect with fellow leaders committed to making a difference.

👉Don’t miss this opportunity to elevate your leadership journey!

#ነጸብራቅ_የመሪነት_ኮንፍራንስ #ኢትዮጵያ #AFLEX #Sululta #Netsebrak2024 #Leadership_Conference
በነጸብራቅ የመሪነት ኮንፍራንስ ሲሳተፉ:

👉 ውጤታማ መሪነት ምን እንደሚመስል በመሪነት ስፍራ ላይ ከሚገኙ ተጋባዥ እንግዶች ይሰማሉ

👉 መሪዎች ስለመሪነት ጉዞአቸው ከሚናገሩባቸው ቃለ-ምልልሶች ልምድ ይወስዳሉ

👉 መሪዎችን እና ኤክስፐርቶችን ጥያቄ ለመጠየቅ እድል ያገኛሉ

👉 በመሪነት ዙሪያ ሃሳብ እያነሱ ይወያያሉ

👉 ከመላው ኢትዮጵያ ከመጡ በተለያዩ የራ መስኮች ከተሰማሩ አዳዲስ እና ልምድ ካላቸው መሪዎች ጋር ኔትወርክ ይፈጥራሉ

ለአይን የሚማርክ ተፈጥሮአዊ ውበት ባላት ሱሉልታ፣ ደረጃውን በጠበቀው የአፍሌክስ ማሰልጠኛ፣ ለሶስት ቀናት ሙሉ ወጪዎ ተሸፍኖ፣ ከመላው ኢትዮጵያ ከመጡ እንግዶች ጋር፣ ስለመሪነት የህይወት ዘመን ትምህርት ይዘው ይሄዳሉ!

ነጸብራቅ የመሪነት ኮንፍራንስ
ከህዳር 26 እስከ 28 2017
በአፍሌክስ ሱሉልታ

#ነጸብራቅ_የመሪነት_ኮንፍራንስ #ኢትዮጵያ #AFLEX #Sululta #Netsebrak2024 #Leadership_Conference
With just one day to go until the Netsebrak Leadership Conference, remember our motto: 🧭Leading with Purpose, Serving with Integrity!

Get ready to:

🔹Engage
🔹Learn
🔹And connect with fellow leaders committed to making a difference.

👉Don’t miss this opportunity to elevate your leadership journey!

#ነጸብራቅ_የመሪነት_ኮንፍራንስ #ኢትዮጵያ #AFLEX #Sululta #Netsebrak2024 #Leadership_Conference