የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ
*******************************
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከዘርፉ የክልል አመራሮች፣ ባለድርሻ እና አጋር አካላት ጋር ለሁለት ተከታታይ ቀናት #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ሲያደርገው የነበረው የምክክር መድረክ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡
*******************************
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከዘርፉ የክልል አመራሮች፣ ባለድርሻ እና አጋር አካላት ጋር ለሁለት ተከታታይ ቀናት #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ሲያደርገው የነበረው የምክክር መድረክ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡
👍3
#አሁን
#Happening_now
#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ እና #የከተማ_እና_መሰረተ_ልማት_ሚኒስቴር
በጋራ ያዘጋጁት የተተኪ ወጣቶች ስልጠና #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ እየተሰጠ ነው::
#በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የስራ አመራር ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ #ወንድዬ_ለገሰ (ዶ/ር) በስልጠናው መክፈቻ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት አካዳሚው የወጣቶችን አቅም ለመገንባት በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰው ወጣቶች የወደፊት አገር ተረካቢ መሆናቸውን ተገንዝበው የመሪነት አቅማቸውን በሚያሳድጉ ተግባራት ውስጥ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው ተናግረዋል::
ስልጠናው የአፍሪካን የወደፊት የከተማ አመራር ማብቃት (Future urban leaders for Africa) በሚል እየተሰጠ ሲሆን ተሳታፊዎቹም ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት: ከተለያዩ ሲቪል ማህበራት: መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት የተውጣጡ አንድ መቶ ወጣቶች እየተሳተፉ ነው::
በዘርፉ ልምድ ያላቸው ከፍተኛ አመራሮችና ሙሁራንና ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን ያካበቱትን ልምድና የህይወት ተሞክሮ ለውጣቶቹ አካፍለዋል::
#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚን የሪፎርም: ማስፋትና ሽግግር ፕሮግራም #በእሸቴ_አበበ (ዶ/ር) ቀርቧል::
#Happening_now
#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ እና #የከተማ_እና_መሰረተ_ልማት_ሚኒስቴር
በጋራ ያዘጋጁት የተተኪ ወጣቶች ስልጠና #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ እየተሰጠ ነው::
#በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የስራ አመራር ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ #ወንድዬ_ለገሰ (ዶ/ር) በስልጠናው መክፈቻ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት አካዳሚው የወጣቶችን አቅም ለመገንባት በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰው ወጣቶች የወደፊት አገር ተረካቢ መሆናቸውን ተገንዝበው የመሪነት አቅማቸውን በሚያሳድጉ ተግባራት ውስጥ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው ተናግረዋል::
ስልጠናው የአፍሪካን የወደፊት የከተማ አመራር ማብቃት (Future urban leaders for Africa) በሚል እየተሰጠ ሲሆን ተሳታፊዎቹም ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት: ከተለያዩ ሲቪል ማህበራት: መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት የተውጣጡ አንድ መቶ ወጣቶች እየተሳተፉ ነው::
በዘርፉ ልምድ ያላቸው ከፍተኛ አመራሮችና ሙሁራንና ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን ያካበቱትን ልምድና የህይወት ተሞክሮ ለውጣቶቹ አካፍለዋል::
#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚን የሪፎርም: ማስፋትና ሽግግር ፕሮግራም #በእሸቴ_አበበ (ዶ/ር) ቀርቧል::
የገጠር መንገድ ትስስርን ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን የምግብ ዋስትና ማረጋገጠ አለብን ሲሉ የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሄለን ደበበ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ በተደረገው መርሀ ግብር ላይ ተናገሩ፡፡
ሚኒስትር ዲኤታዋ ይህን ያሉት ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ የመንገድና ትራንሰፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሚኒስቴር መ/ቤቱ አስተባባሪነትና በአለም ባንክ ድጋፍ በ407 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገጠር ትስስርን በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን አዲሱን ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ ነው፡፡
ሚኒስትር ዲኤታዋ ይህን ያሉት ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ የመንገድና ትራንሰፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሚኒስቴር መ/ቤቱ አስተባባሪነትና በአለም ባንክ ድጋፍ በ407 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገጠር ትስስርን በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን አዲሱን ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ ነው፡፡
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለመላው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ቤተሰቦች፦
አዲሱ ዓመት የሰላም፤ የጤና እና የብልጽግና እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!
ዛዲግ አብርሃ
ፕሬዚደንት
አዲሱ ዓመት የሰላም፤ የጤና እና የብልጽግና እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!
ዛዲግ አብርሃ
ፕሬዚደንት
👍2
Forwarded from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
እንኳን ለ2017 የዘመን መለወጫ በዓል ዕንቁጣጣሽ በዓል አደረሳችሁ
ዘመን ዕድል ነው፡፡ ዘመንን መጠቀም ግን የሥራ ውጤት ነው፡፡ ዘመንን ፈጣሪ ለሁላችንም በእኩልነት ሰጥቶናል፡፡ ልዩነት የሚፈጠረው በዘመን በመሥራትና ባለመሥራት ነው፡፡ በታሪካችን ውስጥ የምንኮራባቸው ምእራፎች አሉ፡፡ በሕይወታችን ውስጥም ደስ የሚያሰኙን ጊዜያት አሉ፡፡ እነዚያ ምእራፎችና ጊዜያት ሌላ ነገር አይደሉም፡፡ የተሰጠንን የዘመን ዕድል በሚገባ ተጠቅመን የሠራንባቸው ወቅቶች ናቸው፡፡
እኛ ብንፈልግም ባንፈልግም ዘመን ይለወጣል፡፡ ጊዜ ወደፊት ብቻ የሚሄድ ማሽን ነውና፡፡ ማንም አያስቆመውም፤ አቅጣጫም አያስቀይረውም፡፡ የሚቻለው በጊዜ መጠቀም ብቻ ነው፡፡ “ክረምት ለሰነፍ ገበሬ መዓት፤ ለጎበዝ ገበሬ ምሕረት ነው” ይባላል፡፡ ምሕረትና መዓቱ ከዝናቡ የሚመጣ ሳይሆን ከገበሬዎቹ ዝግጅትና ሥራ የሚገኝ ነው፡፡ በሰነፍ ገበሬ ላይ ዘመን ይለወጥበታል፤ ብርቱው ገበሬ ግን ዘመንን ራሱን ይለውጠዋል፡፡
በ2016 ለኢትዮጵያ ምን አሳክተናል? በ2017ስ ለኢትዮጵያ ምን ተዘጋጅተናል? የእነዚህ ጥያቄዎች መልስ የዘመን መለወጥን ትርጉም ይቀይረዋል፡፡ ዘመን እየተለወጠብን ነው ወይስ ዘመኑን እየለወጥነው ነው? የሚለውን ያመለክተናል፡፡ ኢትዮጵያን ዘመን እየለወጣት ብዙ ጊዜ ኖራለች፡፡ አልፎ አልፎ ደግሞ በብርታትና በትጋት ዘመኑን ለውጣው ታውቃለች፡፡ ዘመን ሲለውጠን፣ ከተራራ እንደተፈነቀለ ድንጋይ፣ ወዳሰብነው ሳይሆን ወደ ፈለገው ነው የሚወስደን፡፡
2017 የሚለውጠን ሳይሆን የምንለውጠው ዓመት እንዲሆን ነው ምኞቴ፡፡ ዕቅዶቻችንን ተግብረን፤ ፕሮጀክቶቻችንን በጊዜና በጥራት አጠናቅቀን፤ ግጭቶቻችንን በውይይትና በድርድር ፈትተን፤ የዘመናት ስብራቶቻችንን በምክክርና በሽግግር ፍትሕ ጠግነን፤ በብዙ ነገሮች ራሳችንን ችለን፤ ሪፎርሞቻችንን በብቃት አሳክተን፣ የምንለውጠው ዘመን እንዲሆን ነው ምኞቴ፡፡
2017ን በኢትዮጵያ ታሪክ የሚጠቀስ ዘመን ለማድረግ እንዘጋጅ፡፡ የዘመናት ዕዳዎቻችን የምናወራርድበት፤ የኖሩ ቁስሎቻችን የምናክምበት፤ የዘመናት ሕልሞቻችንን ሥር መሠረት የምናስይዝበት፤ የታሪክን መኪና መሪና ማርሽ የምንቆጣጠርበት ዘመን ለማድረግ እንነሣ፡፡
ወደፊት የሚመጡት ልጆቻችን “ይሄ ታሪክ የተሠራው፣ የዛሬ ስንት ዓመት በ2017 ነው” እንዲሉን እናድርገው፡፡
በወጀብና በዐውሎ ውስጥ አስገራሚ ሥራዎችን እንድንሠራ የፈቀደ ፈጣሪ ዛሬም ከእኛ ጋር ነው፡፡ ነገም ከእኛ ጋር ነው፡፡ መሥራት የእኛ ማከናወንም የእርሱ ነው፡፡ እኛ ከተነሣን ዘመኑን እንድንለውጠው እርሱ ይረዳናል፡፡
በድጋሚ እንኳን ለ2017 የዘመን መለወጫ በዓል ዕንቁጣጣሽ አደረሳችሁ
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ጳጉሜን 5፣ 2016 ዓ.ም
//
ዘመን ዕድል ነው፡፡ ዘመንን መጠቀም ግን የሥራ ውጤት ነው፡፡ ዘመንን ፈጣሪ ለሁላችንም በእኩልነት ሰጥቶናል፡፡ ልዩነት የሚፈጠረው በዘመን በመሥራትና ባለመሥራት ነው፡፡ በታሪካችን ውስጥ የምንኮራባቸው ምእራፎች አሉ፡፡ በሕይወታችን ውስጥም ደስ የሚያሰኙን ጊዜያት አሉ፡፡ እነዚያ ምእራፎችና ጊዜያት ሌላ ነገር አይደሉም፡፡ የተሰጠንን የዘመን ዕድል በሚገባ ተጠቅመን የሠራንባቸው ወቅቶች ናቸው፡፡
እኛ ብንፈልግም ባንፈልግም ዘመን ይለወጣል፡፡ ጊዜ ወደፊት ብቻ የሚሄድ ማሽን ነውና፡፡ ማንም አያስቆመውም፤ አቅጣጫም አያስቀይረውም፡፡ የሚቻለው በጊዜ መጠቀም ብቻ ነው፡፡ “ክረምት ለሰነፍ ገበሬ መዓት፤ ለጎበዝ ገበሬ ምሕረት ነው” ይባላል፡፡ ምሕረትና መዓቱ ከዝናቡ የሚመጣ ሳይሆን ከገበሬዎቹ ዝግጅትና ሥራ የሚገኝ ነው፡፡ በሰነፍ ገበሬ ላይ ዘመን ይለወጥበታል፤ ብርቱው ገበሬ ግን ዘመንን ራሱን ይለውጠዋል፡፡
በ2016 ለኢትዮጵያ ምን አሳክተናል? በ2017ስ ለኢትዮጵያ ምን ተዘጋጅተናል? የእነዚህ ጥያቄዎች መልስ የዘመን መለወጥን ትርጉም ይቀይረዋል፡፡ ዘመን እየተለወጠብን ነው ወይስ ዘመኑን እየለወጥነው ነው? የሚለውን ያመለክተናል፡፡ ኢትዮጵያን ዘመን እየለወጣት ብዙ ጊዜ ኖራለች፡፡ አልፎ አልፎ ደግሞ በብርታትና በትጋት ዘመኑን ለውጣው ታውቃለች፡፡ ዘመን ሲለውጠን፣ ከተራራ እንደተፈነቀለ ድንጋይ፣ ወዳሰብነው ሳይሆን ወደ ፈለገው ነው የሚወስደን፡፡
2017 የሚለውጠን ሳይሆን የምንለውጠው ዓመት እንዲሆን ነው ምኞቴ፡፡ ዕቅዶቻችንን ተግብረን፤ ፕሮጀክቶቻችንን በጊዜና በጥራት አጠናቅቀን፤ ግጭቶቻችንን በውይይትና በድርድር ፈትተን፤ የዘመናት ስብራቶቻችንን በምክክርና በሽግግር ፍትሕ ጠግነን፤ በብዙ ነገሮች ራሳችንን ችለን፤ ሪፎርሞቻችንን በብቃት አሳክተን፣ የምንለውጠው ዘመን እንዲሆን ነው ምኞቴ፡፡
2017ን በኢትዮጵያ ታሪክ የሚጠቀስ ዘመን ለማድረግ እንዘጋጅ፡፡ የዘመናት ዕዳዎቻችን የምናወራርድበት፤ የኖሩ ቁስሎቻችን የምናክምበት፤ የዘመናት ሕልሞቻችንን ሥር መሠረት የምናስይዝበት፤ የታሪክን መኪና መሪና ማርሽ የምንቆጣጠርበት ዘመን ለማድረግ እንነሣ፡፡
ወደፊት የሚመጡት ልጆቻችን “ይሄ ታሪክ የተሠራው፣ የዛሬ ስንት ዓመት በ2017 ነው” እንዲሉን እናድርገው፡፡
በወጀብና በዐውሎ ውስጥ አስገራሚ ሥራዎችን እንድንሠራ የፈቀደ ፈጣሪ ዛሬም ከእኛ ጋር ነው፡፡ ነገም ከእኛ ጋር ነው፡፡ መሥራት የእኛ ማከናወንም የእርሱ ነው፡፡ እኛ ከተነሣን ዘመኑን እንድንለውጠው እርሱ ይረዳናል፡፡
በድጋሚ እንኳን ለ2017 የዘመን መለወጫ በዓል ዕንቁጣጣሽ አደረሳችሁ
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ጳጉሜን 5፣ 2016 ዓ.ም
//
👍4