ET Securities
650 subscribers
572 photos
7 videos
26 files
287 links
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
የኢትዮጲያ ሰነደመዋለንዋይ ገበያ ዲጂታል አካዳሚ መጀመሩን በይፋ አብስሯል።

የኢትዮጲያ ሰነደመዋለንዋይ ገበያ "ESX Academy" የተሰኘውን የመማሪያ ፕላትፎርም ያስተዋወቀ ሲሆን ይህም ከ FSD Ethiopia ጋር በመተባበር  የተሰራ ፕሮጀክት ነው።

መጪው ካፒታል ገበያ ሲጀመር ክፍተት ይሆናል ተብሎ የታሰበውን የፋይናንስ እውቀት ለመቅረፍ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ኢሰገ ገልጿል።

በኢትዮጲያ ካፒታል ገበያ ሰሚት ላይ አቶ ሚካኤል ሃብቴ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ አካዳሚ እንጀምራለን ማለታቸው አይዘነጋም ነበር።

ፕላትፎርሙ የተለያዩ ኮርሶችን አንድላይ የያዘ ሲሆን ከነዚህም፡

1. ካፒታል ገበያ እንዴት ነው ሚሰራው
2. ኢንቨስትመንት ስትራቴጂ
3. ሻሪያን ስላገናዘቡ ምርቶች
4. የኢትዮጲያ ሰነደመዋለንዋይ ገበያ በኢትዮጲያ ኢኮኖሚ ላይ ስላለው ሚናና ያካትታል።

ኮርሶቹን ለመወሰድ esxacademy.com ላይ ገብተው መውሰድ ይችላሉ።
| YouTube | X | TikTok
አዲሱን የባንክ ስራ አዋጅ ከማብራሪያው ጋር እነሆ!!
ገዳ ባንክ ከታክስ በፊት 101 ሚሊዮን ብር ማትረፉ ተገለፀ!!

ገዳ ባንክ የባለ አክሲዮኖች ሶስተኛ መደበኛ ጉባኤውን  ባካሄደበት ወቅት  በበጀት ዓመቱ ከታክስ በፊት 101 ሚሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታውቋል።

በ2016በጀት አመት ያገኘው ገቢ 790 ሚሊዮን ብር  ሲሆን ካለፈው አመት ጋር ሲነፃጸር የ609 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱ ተገልጿል፡፡

በ 2,88,174 ደንበኞች አጠቃላይ ተቀማጭ የገንዘብ መጠኑ 4 ቢሊዮን  መድረሱም ተጠቁሟል።

ካሉት ደንበኞች የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚ 42,930 መሆናቸውን ባንኩ አሳውቋል።

በበጀት አመቱ 2.9 ሚሊዮን ብር ብድር መስጠት መቻሉም ተገልጿል፡፡
ዓለም ባንክ፣ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለማጠናከር የሚውል የ700 ሚሊዮን ዶላር ብድር አጽድቋል

#Ethiopia  | ከብድሩ 90 በመቶው የንግድ ባንክን ሒሳብ ለማስተካከልና ባንኩን መልሶ ለማዋቀር እንደሚውል ዓለም ባንክ ገልጧል።

ከፊሉ ብድር ለብሄራዊ ባንክና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ማጠናከሪያና መዋቅራዊ ማሻሻያ እንደሚሰጥ ባንኩ ጠቅሷል።

ብድሩ በአራት ዓመታት ጊዜ ውስጥ የሚለቀቀው፣ የባንኮቹ አፈጻጸም፣ የደንቦችና የመዋቅሮች ማሻሻያ ሂደት እየታየ የሚለቀቅ ነው።

የብድሩ ዓላማ፣ የአገሪቱን የፋይናንስ ዘርፍ ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግና ተደራሽነቱን ለማስፋት ያለመ እንደኾነም ባንኩ ባሠራጨው አጭር መግለጫ አንስቷል።

https://t.me/etstocks
" የሂጅራ ባንክ አጠቅላይ ሀብት 8.1 ቢሊዮን ብር ደርሷል " - የሂጅራ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዱሰላም ከማል

ሂጅራ ባንክ አ.ማ የባለአክስዮኖች 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ታህሳስ 13 ቀን 2017 በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ በተሳካ ሁኔታ አካሂዷል፡፡

በጉባኤው ላይ የሂጅራ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዱሰላም ከማል የ2023/2024 የበጀት ዓመት ዓመታዊ ሪፖርት ለባለ አክሲዮኖች ያቀረቡ ሲሆን ባንኩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከታክስ በፊት 100 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ በማስመዝገብ ማጠናቀቁን ያበሰሩ ሲሆን፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ334.78%  ብልጫ ማሳየቱን ገልጸዋል፡፡

ባንኩ ከምን ጊዜውም በላይ የአገልግሎት ተደራሽነቱን በማስፋት በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ቅርንጫፎችን በመክፈት አጠቃላይ የቅርንጫፍ ብዛቱን ወደ 100+ ከፍ ማድረጉን ገልጸው ይህም 40% እድገት ማሳየቱን አብራርተዋል።

ባንኩ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የደንበኞች ብዛቱን በማሳደግ ከ700,000 በላይ ደንበኞችን ማፍራቱንም ገልጸዋል።

በዚሁ ረገድ ባንኩ ስኬታማ አፈፃፀም በማስመዝገብ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የባንኩ አጠቃላይ ሀብት 8.1 ቢሊዮን ብር መድረሱን ለባንኩ ባለአክሲዮኖች አብስረዋል።

ባንኩ ከፋይናንሺያል አፈፃፀም በተጨማሪ  የማህበረሳችንን እሴቶች ማእከል ያደረጉ ምርትና አገልግሎቶች በማስተዋወቅ በደንበኞቹ ዘንድ ተመራጭ እና ተወዳዳሪ ባንክ የመሆን ራዕዩን አጠናክሮ መቀጠሉን አብራርተዋል::

#HijraBank
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ መዝጋት ዕቅድ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ700 ሚሊዮን ዶላር የዓለም ባንክ የፋይናንሺያል ሴክተር ማጠናከሪያ ፕሮጀክት ቅርንጫፎችን ከመዝጋቱ በፊት የማህበራዊ ስጋት ግምገማ ያካሂዳል። መልሶ ማዋቀሩ ቅልጥፍናን ለማሳደግ እና ከተማን ያማከለ ብድርን ለመፍታት ያለመ ቢሆንም ተቺዎች የገጠር የባንክ ተደራሽነትን ሊያባብስ እንደሚችል ያስጠነቅቃሉ።

ተጽዕኖዎችን ለመቀነስ፣ ንግድ ባንክ የስንብት ፓኬጆችን፣ የሥራ ሽግግር ፕሮግራሞችን እና አማራጭ የአገልግሎት ሞዴሎችን አቅዷል። የዓለም ባንክ ዋና ዳይሬክተር ሜሪየም ሳሊም የፕሮጀክቱን የበለጠ ተቋቋሚ እና አካታች የፋይናንሺያል ስርዓት ለመገንባት ያለውን ግብ አፅንዖት ሰጥተዋል። የዘመናዊነት ተስፋ ሰጪ ቢሆንም፣ ቅነሳው ለገጠሩ ማህበረሰብ ስጋት ይፈጥራል።

Linkupbusiness
@Etstocks
ፍሊንትስቶን ኢንጂነሪንግ በአይፒኦ ወቅት 269,433 አክሲዮኖችን እያንዳንዳቸው በ750 ብር በመሸጥ የአክሲዮን ባለቤቶቹም ብዛት ከ7 ወደ 1,799 ከፍ ብሏል። በሐምሌ፣ 2016 የጀመረውይህ የመጀመሪያው የህዝብ አቅርቦት(IPO) 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለመሸጥ ያለመ ነበር።

በሪል እስቴት (80 በመቶው የፕሮጀክቶች) እና የመንግስት ኮንትራቶች (20%) ልዩ አቅም ያለው ፍሊንትስቶን እንደ የዋጋ ግሽበት እና የዋጋ ንረት ያሉ የሴክተሩን ተግዳሮቶች ተቋቁሞ በቦጎሲያን፣ አዋሬ እና ካዛንቺስ ውስጥ ፕሮጄክቶችን አጠናቆ አስረክቧል።

በ2016 በጀት አመት የ829.2 ሚሊየን ብር ገቢ፣ የተጣራ 25 ሚሊየን ብር እና አጠቃላይ የሀብት መጠን 2.1 ቢሊዮን ብርጽቭ
በማስዝገብ የ24 በመቶ እድገት አሳይቷል። 18 ፕሮጀክቶችን ተረክቦ በመካሄድ ላይ ያለው ፍሊንትስቶን በኢትዮጵያ የግንባታ እና የሪል ስቴት ዘርፎች የማይበገር ተጫዋች ሆኖ ቀጥሏል።

linkupbusiness
@Etstocks
አማራ ባንክ የኢንቨስትመንት ባንክ ሊያቋቋም መሆኑ ተሰማ!!

አማራ ባንክ የካፒታል ገበያና የኢንቨስትመንት ባንክ ፕሮጀክቶችን ለመጀመር ማቀዱን ካፒታል በዘገባው ገልጿል።

ባንኩ በፋይናንሺያል ኢንደስትሪ ውስጥ ካለው ወቅታዊ አካሄድ አንፃር የደንበኞቹን ፍላጎት ለማሟላት የተለያዩ አዳዲስ የፋይናንስ አማራጮችን ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን ተጠቁሟል።

ባንኩ አሰራሩን እየለወጠ እና አገልግሎት አሰጣጡን ለማሳደግ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ቀርፆ ወደ ስራ መግባቱን የባንኩ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሀንስ አያሌው ገልፀዋል፡፡

አክለውም ማህበራዊ ልማት ፕሮጀክቶችን እየደገፍን ግቦቻችንን ለማሳካት ቆርጠን ተነስተናል ብለዋል፡፡

የካፒታል ማርኬት እና ኢንቨስትመንት ባንኪንግን ለመጀመር ማቀዱ በኢትዮጵያ ባንክ ዘርፍ ተጨማሪ ሚና እንዲሚኖረው እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
Abay Bank’s profit margin erosion emerged when its net profit dropped 3.2pc to 1.5 billion Br, accompanied by a 22pc fall in earnings per share (EPS), down from 360 Br, though it still is higher than many private banks.

Read More

Source: addisfortune
@Etstocks
የኢንሹራንስ ምርት እና አገልግሎት ሻጭ ለመሆን  ጥቂት ቁልፍ ነገሮችን ማስታወስ ያስፈልግዎታል።

ኢንሹራንስ ለመሸጥ ምን ማድረግ እንደሚችሉ አንዳንድ ምክሮች እነሆ፡-

1. የኢንሹራንስ ኢንዱስትሪን በደንብ ይረዱ
* የተለያዩ የኢንሹራንስ አይነቶችን ይወቁ: የህይወት ኢንሹራንስ፣ የጤና ኢንሹራንስ፣ የመኪና ኢንሹራንስ፣ የንብረት ኢንሹራንስ እና ሌሎችም አይነቶች ምን እንደሚሸፍኑ እና ለምን አስፈላጊ እንደሆኑ በደንብ ይረዱ።
* የኢንሹራንስ ውሎችን ይረዱ: ፖሊሲዎች ምን እንደሚሸፍኑ፣ ምን እንደማይሸፍኑ እና ምን ዓይነት ቅናሾች እንዳሉ በደንብ ይረዱ።
* የኢንሹራንስ ደንቦችን ይወቁ: ኢንሹራንስን የሚቆጣጠሩትን ደንቦች እና ደንቦችን ማወቅ በጣም አስፈላጊ ነው።

2. ጠንካራ የደንበኛ ግንኙነት ይገንቡ
* ደንበኞችን ያዳምጡ: ደንበኞችዎ ምን እንደሚፈልጉ እና ምን እንደሚያስፈልጋቸው ለማወቅ ጊዜ ይወስዱ።
* የደንበኞችን ፍላጎት ይረዱ: ደንበኞችዎ ምን አይነት ኢንሹራንስ እንደሚያስፈልጋቸው ለመወሰን ይረዱ።
* የደንበኞችን ጥያቄዎች በትዕግስት ይመልሱ: ደንበኞችዎ ጥያቄ ሲጠይቁ በትዕግስት እና በግልፅ ይመልሱ።

3. የሽያጭ ክህሎቶችዎን ያሻሽሉ
* የሽያጭ ቴክኒኮችን ይማሩ: እንዴት ውጤታማ በሆነ መንገድ ማቅረብ እንደሚችሉ፣ እንቅፋቶችን እንዴት ማሸነፍ እንደሚችሉ እና ሽያጭን እንዴት መዝጋት እንደሚችሉ ይማሩ።
* በራስ መተማመን ይኑርዎት: በምርትዎ ላይ እምነት ይኑርዎት እና ለደንበኞችዎ እሴት እንደሚሰጡ ያሳዩ።
* የሽያጭ ግቦችን ያወጡ እና ይከታተሉ: ግልጽ የሆኑ የሽያጭ ግቦችን ያወጡ እና እድገትዎን ይከታተሉ።

4. ኔትወርኪንግ ያድርጉ
* በኢንዱስትሪው ውስጥ ያሉ ሰዎችን ያውቁ: ሌሎች የኢንሹራንስ ወኪሎች፣ ብሮከሮች እና የኢንዱስትሪ ባለሙያዎችን ያግኙ።
* የንግድ ክስተቶች ላይ ይሳተፉ: የኢንዱስትሪ ኮንፈረንሶች፣ ሴሚናሮች እና ሌሎች የኔትወርኪንግ ዝግጅቶች ላይ ይሳተፉ።
* የማህበራዊ ሚዲያን ይጠቀሙ: ሊንክዲን እና ሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮችን በመጠቀም ከሌሎች ባለሙያዎች ጋር ይገናኙ።

5. የደንበኛ አገልግሎትዎን ያሻሽሉ

* ከደንበኞችዎ ጋር በመደበኛነት ይገናኙ: ደንበኞችዎ እንዴት እንደሚሰሩ ለማየት በመደበኛነት ያነጋግሩዋቸው።
* ለደንበኞችዎ ተደራሽ ይሁኑ: ደንበኞችዎ ጥያቄ ሲኖራቸው ወይም ችግር ሲያጋጥማቸው በፍጥነት እንዲደርሱባቸው ያድርጉ።
* ለደንበኞችዎ ተጨማሪ እሴት ይስጡ: ለደንበኞችዎ ጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ምክሮችን እና መረጃዎችን ይስጡ።
በተጨማሪም፣ እነዚህ ጥቂት ጠቃሚ ምክሮች ሊረዱዎት ይችላሉ፡-
* የግል ብራንድዎን ይገንቡ: በኢንዱስትሪው ውስጥ እንደ ባለሙያ እንዲታወቁ ያድርጉ።
* የደንበኛ ምስክርነቶችን ይሰብስቡ: ደስተኛ የሆኑ ደንበኞችዎ ስለእርስዎ ምን እንደሚሉ ለማሳየት የደንበኛ ምስክርነቶችን ይጠቀሙ።
* የማያቋምት ትምህርት ይኑርዎት: ኢንሹራንስ ኢንዱስትሪ በፍጥነት እየተለወጠ ነው፣ ስለዚህ እራስዎን ለማዘመን ጊዜ ይወስዱ።
ማስታወሻ: ኢንሹራንስ መሸጥ በጣም ውድድር የሚደረግበት ኢንዱስትሪ ነው። ስኬታማ ለመሆን ጠንካራ ሥራ፣ ቁርጠኝነት እና ትዕግስት ያስፈልግዎታል።


Financial Ethiopia
@Etstocks
ዘም ዘም ባንክ ሸሪዓን መሰረት ያደረገ "አንሳር" የተባለ የዲጅታል ፋይናንስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ።

ዘም ዘም ባንክ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውንና በሙሉ ሸሪዓን መሰረት ያደረገ "አንሳር" የተባለ የዲጅታል ፋይናንስ መተግበሪያ ይፋ አድርጓል።

ባንኩ ይህንን መተግበሪያ በትላንትናው ዕለት በአዲስ አበባ ኃይሌ ግራንድ ሆቴል ላይ አስመርቋል።

በዚህ ወቅት የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ወ/ሮ መሊካ በድሪ በሀገራችን ከተለመደው የፋይናንስ አሰጣጥ ተገልለው ለቆዮ በተለይም በአነስተኛ እና መካከለኛ የስራ ዘርፍ ለተሰማሩ የማህበረሰብ ክፍሎች እና ለሴቶች መፍትሔ እንሚሆን ገልጸዋል።

"አንሳር  የፋይናንስ ተቋማት ዋስትና ሳያስፈልጋቸው ብድር የማግኘት ብቻ ሳይሆን ብድር የሚሰጥበትን ጊዜ ይቀንሳል ነው የተባለው።

አንሳር ሸሪአን መሰረት ያደረገ የፋይናንስ መርሆዎችን እና የዲጂታል ፈጠራ ኃይልን በመጠቀም ለማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን እና እድሎችን በፍትሃዊነት እና በእኩልነት የሚያቀርብ ይሆናል ሲሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ የተናገሩት።

በክፊያ የፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ የጎለበተው አንሳር መተግበሪያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ያካተተ እና አማራጭ ዳታን በመጠቀም የሚሰጥ አገልግሎት ነው ተብሏል።

የክፍያ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሀያት አብዱልመሊክ መተግበሪያው በኢትዮጵያ ያለውን የወደፊት ፍትሐዊነት እና የፋይናንሺያል አካታችነትን ከማረጋገጡም በላይ ከባንክ አገልግሎት ተገልለው የቆዩ ማህበረሰቦችን በቀላሉ ማገልገል እንደሚቻል ማሳያም ጭምር እንደሆነ በምርቃቱ ወቅት አብራርተዋል።
ግሎባል ባንክ ከ4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ!!

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በ2016 በጀት አመት ከ4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ አስታውቀዋል።

ከተገኘው ገቢም የባንኩ ትርፍ ታክስ ፤ከመጠባበቂያ እና ሌሎች ተቀናሾች በፊት ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ማትረፉን ገልፀዋል።

ይህም ካለፈው በጀት አመት ጋር ሲነፃፀር የ37 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ጠቅሰዋል።

ባንኩ የተቀማጭ ሂሳቡን ወደ 4 ቢሊዮን ብር በማሳደግ የተቀማጭ የገንዘብ መጠኑ ወደ 18.22 ቢሊዮን መድረሱን ተናግረዋል።

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተከፈለ ካፒታሉን 2.48 ቢሊዮን ብር ያደረሰ ሲሆን ጠቅላላ ሀብት ደግሞ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን አንስተዋል።

ግሎባል ባንክ የትርፍ ድርሻውን በ14 በመቶ በማሳደግ ለባለአክሲዮኖች 33.2 በመቶ የትርፍ ድርሻ መክፈሉን አስታውቋል።
ባንኮች የገዙት የመንግስት የብድር ሰነድ!!

የሀገሪቱ ንግድ ባንኮች ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ 110 ቢሊዮን ብር የሚደርስ ወጪ በማድረግ በብሔራዊ ባንክ የጸደቀውን የአምስት ዓመታት የመንግስት የብድር ሰነድ መግዛታቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው ሪፖርት ላይ ይፋ ተደርጓል፡፡

ለትርፍ የተቋቋሙት የንግድ ባንኮቹ ይህንን ያህል መጠን ያለው የመንግስት ብድር ሰነድ (በእንግሊዝኛው ትሬዠሪ ቢል) የገዙት በፈረንጆቹ ኖቬምበር 2024 የመጣውን የብሔራዊ ባንክ መመሪያ ድንጋጌን ተከትሎ ሲሆን መመሪያው ባንኮቹ ያበደሩትን ብድር 20 በመቶ የሚያክል መጠን ያለው ገንዘብን ለብድር ሰነዱ መግዣነት እንዲያውሉት ያዛል፡፡

ይህንን ተከሎም ባንኮቹ እስካለፈው ሴፕቴምበር 2024 ድረስ 109 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የሚደርስ የብድር ሰነድ መግዛታቸውን ነው የገንዘብ ሚኒስቴር ያወጣው ሪፖርት የሚያትተው፡፡

ይህ የብድር ሰነድ መንግስት ያለበትን የበጀት ጉድለቱን ከብሔራዊ ባንክ በቀጥታ መበደር ሳያስፈልገው የሚሞላበት አንዱ መላ ነው፡፡

በሌላም በኩል ይህ ሪፖርት እንደሚያሳየው የመንግስት ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ብድር እስከሴፕቴምበር 30፣ 2024 ድረስ በ2 ነጥብ 3 ትሪሊዮን ብር ደርሷል፡፡

ቅዳሜገበያ