ET Securities
648 subscribers
572 photos
7 videos
26 files
287 links
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
" የሂጅራ ባንክ አጠቅላይ ሀብት 8.1 ቢሊዮን ብር ደርሷል " - የሂጅራ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዱሰላም ከማል

ሂጅራ ባንክ አ.ማ የባለአክስዮኖች 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ታህሳስ 13 ቀን 2017 በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ በተሳካ ሁኔታ አካሂዷል፡፡

በጉባኤው ላይ የሂጅራ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዱሰላም ከማል የ2023/2024 የበጀት ዓመት ዓመታዊ ሪፖርት ለባለ አክሲዮኖች ያቀረቡ ሲሆን ባንኩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከታክስ በፊት 100 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ በማስመዝገብ ማጠናቀቁን ያበሰሩ ሲሆን፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ334.78%  ብልጫ ማሳየቱን ገልጸዋል፡፡

ባንኩ ከምን ጊዜውም በላይ የአገልግሎት ተደራሽነቱን በማስፋት በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ቅርንጫፎችን በመክፈት አጠቃላይ የቅርንጫፍ ብዛቱን ወደ 100+ ከፍ ማድረጉን ገልጸው ይህም 40% እድገት ማሳየቱን አብራርተዋል።

ባንኩ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የደንበኞች ብዛቱን በማሳደግ ከ700,000 በላይ ደንበኞችን ማፍራቱንም ገልጸዋል።

በዚሁ ረገድ ባንኩ ስኬታማ አፈፃፀም በማስመዝገብ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የባንኩ አጠቃላይ ሀብት 8.1 ቢሊዮን ብር መድረሱን ለባንኩ ባለአክሲዮኖች አብስረዋል።

ባንኩ ከፋይናንሺያል አፈፃፀም በተጨማሪ  የማህበረሳችንን እሴቶች ማእከል ያደረጉ ምርትና አገልግሎቶች በማስተዋወቅ በደንበኞቹ ዘንድ ተመራጭ እና ተወዳዳሪ ባንክ የመሆን ራዕዩን አጠናክሮ መቀጠሉን አብራርተዋል::

#HijraBank