ET Securities
662 subscribers
584 photos
7 videos
28 files
297 links
At ET Securities, our goal is to provide services in the financial sector, with a special focus on capital markets and financial markets.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
Official and Parallel Exchange Rates—Recognizing Reality.pdf
2 MB
IMF በ2021 ስለ መደበኛ እና የጥቁር ገበያ ምንዛሬን ስለማቀራረብ (Recognizing Reality፡ Unification of Official and Parallel Exchange Rates) ሪፎርም የሰሩ ሀገራትን ሁኔታ የተነተነበት የጥናት ሰነድ ነው! ምንዛሬን በገበያ የመወሰን ጉዳይ ላይ ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ለምትፈልጉ ሰዎች! https://www.condoaddis.com/category/etstocks
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የ2025 በጀት ዓመት የሩብ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።

በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 4.6 ሚሊዮን የሚሆኑ ንቁ ደንበኞች በተከታታይ ባሉ 90 ቀናት ውስጥ የሳፋሪኮምን ኔትወርክን መጠቀማቸውን ያመለክታል።

በተከታታይ ባሉ 30 ቀናት የሳፋሪኮምን ኔትዎርክ የተጠቀሙ ንቁ ደንበኞቹ ቁጥር ደግሞ 3.4 ሚሊዮን እንደሆነ ገልጿል።

(ይህ ማለት ሳይጠቀሙ 90 ቀን ወይም 30 ቀን ያለፋቸው ደንበኞች ንቁ ተጠቃሚ በሚለው ውስጥ አይካተቱም።)

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል አገልግሎቱን ከጀመረ በኋላ ባሉት ጊዜያት ከፍተኛ የደንበኞች ቁጥር ማግኘቱን አስታውቋል።

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት በተከታታይ ባሉ 30 ቀናት የተጠቀሙ ደንበኞቹ ቁጥር በዚህ ደግሞ 2.4 ሚሊዮን ደንበኞች ናቸው።

በሪፖርቱ እንደተጠቀሰው አንድ የሳፋሪኮም ደንበኛ በወር ውስጥ በአማካይ 6.5 GB ኢንተርኔት ይጠቀማል።

ተቋሙ በቅርቡ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ በኤም ፔሳ መክፈል የሚያስችል ሥርዓት ከዘረጋ በኋላ 3ሺ 500 ደንበኞች ማስተናገዱን ገልጿል። በዚህም 13 ሺ ክፍያዎች የተስተናገዱ ሲሆን 8.1 ሚሊየን ብር ክፍያ ተፈጽሟል።

በተጠቀሰው ጊዜ 2 ቢሊዮን የኬንያን ሽልንግ (1.6 ቢሊየን ብር ) በላይ ገቢ መገኘቱን የገለጸው ተቋሙ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው ከኢንተርኔት አገልግሎት ያገኘው እንደሆነ አስታውቋል። ይህም ከገቢው 78 በመቶ የሚሆነውን የሚሸፍን ነው።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአማካኝ ኢንተርኔት የሚጠቀሙ ደንበኞቹ 244.7 የኬንያ ሽልንግ (196.6 ብር) በወር የሚያወጡ ሲሆን ከአጠቃላይ አገልግሎቱ 155.3 የኬንያ ሽልንግ (124.8 ብር) በወር ያወጣሉ።

Source: tikvahethmagazine
@Etstocks
የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ   ዓለም አቀፍ የካፒታል ገበያ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎችን አቅራቢ ከሆነው ከኢንፎቴክ ፕራይቬት ሊሚትድ ጋር ሁለት የቴክኖሎጂ ስምምነቶችን መፈራረሙን ገልጿል ።

የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያው ከአለም አቀፉ የቴክኖሎጂ አቅራቢ ጋር አድርጌያለሁ ያላቸዉ ስምምነቶች  የኤሌክትሮኒክ መገበያያ መድረክ እና የደላላ የኃላ ቢሮ እና የትዕዛዝ አስተዳደር ስርዓት ናቸዉ።

እነዚህ ስርዓቶች ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ እና ግልጽ የካፒታል ገበያ በኢትዮጵያ እንዲመሰረት፣ ንግዱን በማሳለጥ አጠቃላይ የገበያ መሠረተ ልማትን ለማሳደግ ወሳኝ ናቸው ተብሏል።

በመጪው ጥቅምት ወር ስራ ይጀምራል ተብሎ የሚጠበቀው ገበያዉ ትላንት ያደረገዉ ባደረገው ስምምነት መሰረት አዲሱ ሥርዓት ኢንቨስተሮችን ተቀብሎ የመመዝገብ፣ ትዕዛዞችን የመቀበል፣ ሪፖርት የማድረግ፣ ግብይትን ማቀነባበር እና የመሳሰሉትን ዋና ዋና ተግባራትን እንደሚያስተናግድ ይጠበቃል ።

Read more
Currency Exchange Rates and the Need for Forward Exchange Rate Market Financial Instruments: A Call for New Competencies in Local Banks

It is essential to distinguish between an individual currency and an exchange rate. While one can possess a specific currency, an exchange rate indicates the value of one currency in relation to another (for instance, the exchange rate between the Birr and the USD).

Read More

Source: capitalethiopia
@Etstocks
አሊባባ

እ.ኤ.አ በ1999 በጃክ ማ የተመሰረተው አሊባባ ኩባንያ፡ የኢ-ኮሜርስ፣ የክፍያ ስርዓት፣ የገበያ መረጃና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን ያካተተ ሁለገብ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ነው።

አሊባባ በቻይና ውስጥ የኢ-ኮሜርስ ለውጥ ያመጣ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ቢሆን በተለይም አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች (SME's) ወደ ገበያ እንዲደርሱ እና ስራቸውን እንዲያስፋፉ ረድቷል። ከዚህ በተጨማሪም የአሊባባ ሎጂስቲክስ በዓለም ደረጃ የሎጂስቲክስ ኢንዱስትሪውን እንደቀየረ ይታመናል። በአሊባባ የቴክኖሎጂ ካምፓኒ ከሚሰጡ አገልግሎቶች መካከል የሚከተሉት በዋናነት ይጠቀሳሉ :-

🥢 Alibaba.com - A B2B platform connecting global buyers and suppliers.
🥢 Taobao - A C2C platform similar to eBay, popular for a wide range of products.
🥢 Tmall - A B2C platform featuring branded products and stores.
🥢 Alipay - A mobile and online payment platform. 🥢 Alibaba Cloud - A cloud computing service provider.

አሊባባ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ በርካታ የኤክስፖርት እድሎችን የሚፈጥር ሲሆን በተለይ . . . .

Read more
የአሜሪካ ዶላር ለመግዛት ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ነው።
በካፒታል ማርኬት ውስጥ የሚግኙ የግብይት መሣሪያዎች
፟ _ አክሲዮኖች
_ የዕዳ ሠነዶች
_ የግል ዘርፍ የዕዳ ሰነዶቸ
_ የግምጃ ቤት ሠነዶች
_ የጋራ ፈንዶች
_ የኪራይ ሰነዶች
_ የንብረት ባለቤትነት
#Daily_Tips

TelegramTips

ቴሌግራም በቅርቡ "ቴሌግራም ስታርስ/Telegram Stars" የተሰኘ አዲስ ምናባዊ ገንዘብ (virtual currency) ማስተዋወቁ ይታወሳል።

ይህን ሥርዓት በመጠቀም ቴሌግራም ለይዘት ፈጣሪዎች እና ለቻናል ባለቤቶች አዲስ ነገር አስተዋውቋል።

አንደኛው ቀጥታ ከቻናሉ አባላት የሚሰጥ የስታር ሥጦታ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ተከታዮች በክፍያ ይዘቶችን እንዲያገኙ የሚያስችላቸው ነው።

1. ሥጦታ

የቻናል ባለቤቶች ሥጦታዎችን ከአባሎቻቸው መቀበል ከፈለጉ በመጀመሪያ የቻናላቸውን ገጽ ማስተካከያ ላይ በመግባት Reaction የሚለው ውስጥ Enable Paid Reaction የሚለውን መፍቀድ/ማብራት ይጠበቅባቸዋል።

ተጠቃሚዎች በበኩላቸው የሚፈልጉትን ይዘት ለመደገፍ ሲፈልጉ ወይም የወደዱት ልጥፍ ካለ የስታር ሥጦታ ልክ ከዚህ ቀደም የተለያዩ ኢሞጂዎችን ሪአክት በሚያደርጉበት መንገድ የሚፈልጉትን ያክል መጠን መስጠት ይችላሉ።

2. በክፍያ የሚቀርብ ይዘት (Subscription)

ይዘት አቅራቢዎች በክፍያ ለሚያቀርቡት ይዘት ወርኃዊ ክፍያ ማስከፈል የሚያስችላቸው ሲሆን ይህንም ተጠቃሚዎች ለየት ያሉ ይዘቶችን ቀድመው ወይም በልዩነት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው። (ይህ አገልግሎት አሁን ላይ አልጀመረም)

ቴሌግራም ለተጠቃሚዎች ከደረሰ 11 ዓመት ሞልቶታል። እስካሁን 950 ሚሊዮን ንቁ ተሳታፊዎች እንዳሉት የገለጸ ሲሆን በ2024 1 ቢሊዮን ለመገንባት እቅድ አለው።
The National Bank of Ethiopia NBE suspended the foreign exchange licenses of 12 banks for under invoicing.
ያለ ውጭ ምንዛሬ ክፍያ (በፍራንኮ ቫሉታ) ዕቃዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት የሚችሉበት አሰራር ተዘርግቷል፡፡
መንግሥት በቅርቡ ተግባራዊ ባደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ምንዛሬ በገበያው አማካኝነት እንዲወስን ማድረጉ እና ይኸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡

ማሻሻያው ተከትሎ የገቢ ንግዱን በይበልጥ እንዲያሳልጥ ወደ አገር እንዳይገቡ በሕግ ክልከላ ከተደረገባቸው ፣ የነዳጅ አውቶሞቢሎች እና ከፀጥታና ከደህንነት ዕቃዎች ውጪ ሌሎች ዕቃዎች ያለ ውጭ ምንዛሬ ክፍያ (በፍራንኮ ቫሉታ) ወደ አገር እንዲገቡ በመንግሥት ተወስኗል፡፡

ዕቃዎች በፍራንኮ ባሉታ በቀጥታ እንድገቡ መንግስት መፍቀዱ አሁን ላይ ያለውን ወቅታዊ የገበያና የንግድ እንቅስቃሴ ወደ መደበኛው የሚመልስ በመሆኑ ገበያውን የተረጋጋ እንደሆን አወንታዊ ሚና ይጫወታል፡፡

ET Securities
ድረ ገጽ: www.condoaddis.com/category/etstocks
ቴሌግራም: t.me/Etstocks1
ትዊተር፡ https://twitter.com/Etstocks
ፌስ ቡክ፡   https://www.facebook.com/Etstocks
ዩቲዩብ :https://www.youtube.com/@etstocks
Macroeconomic Reforms open new opportunities for renewable energy investment

Ethiopia’s recent macroeconomic reforms have created significant opportunities for renewable energy investment, a sector that has long faced challenges due to regulatory and financial constraints. Despite the government’s ongoing efforts to promote renewable energy development in the private sector, progress has been limited. However, the introduction of a floating exchange rate by the National Bank of Ethiopia (NBE) and the focus on convertibility guarantees are now seen as game-changers for foreign investors.



Source: capitalethiopia
#News አማራ ባንክ ከታክስ በፊት ከ 377 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡን የገለፀ ሲሆን ተቀማጭ ገንዘብ ከ 25 ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷል ሲል አስታዉቋል ።

ባንኩ በተጠናቀቀው የ2023/24 በጀት ዓመት የተሻለ ከታክስ በፊት ብር 377.2 ሚሊየን ትርፍ ያስመዘገበ መሆኑን እና ብር ተቀማጭ ገንዘብ ከ 25.1 ቢሊየን ብር ላይ መድረሱን ገሌጿል።

ከ1.8 ሚሊየን በላይ ደንበኞች እንዳሉት የሚነገርለት ባንኩ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች አጠቃላይ ብር 20.3 ቢሊየን ብድር መስጠቱን ገለጿል።

አማራ ባንክ የበጀት ዓመቱን አፈፃፀም በተመከለተ በሰጠዉ መግለጫ ከ 571 ሺ በላይ የሞባይል ባንክ ተጠቃሚዎችን እንዲሁም ከ50 ሺ በላይ የካርድ ተገልጋዮችን ማፍራት የቻለ ሲሆን በርካታ የኤቲኤም እና የፖስ ማሽኖችን በተለያዩ ቦታዎች በማኖር በዲጂታል ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ ችያለሁ ብሏል ።

ካፒታል
የኅብረት ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መላኩ ከበደ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ!
***
በኅብረት ባንክ በተለያዩ የኃለፊነት መደቦች ከ20 ዓመታት በላይ ሲያገለግሉ የቆዩት፣ ባለፉት 5 ዓመታት ደግሞ በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የነበሩት አቶ መላኩ ከበደ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ፡፡

የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት አቶ መላኩ ከኃላፊነታቸው የለቀቁት በገዛ ፈቃዳቸው ሲሆን፣ ይህንንም በመልቀቂያ ደብዳቤያቸው ላይ ያሰፈሩ ቢሆንም፣ ውሳኔያቸው ድንገተኛ ነው ተብሏል፡፡ ከባንኩ የተገኘው መረጃ ደግሞ አቶ መላኩ ኃላፊነታቸውን የለቀቁት ከግል ምክንያት ጋር በተያያዘ ነው፡፡

ድንገተኛ የተባለውን የአቶ መላኩ የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ የተቀበለው የባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ፣ ጥያቄያቸውን ተቀብሎ አዎንታዊ መልስ እንደሰጣቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

ቦርዱ በአቶ መላኩ ምትክ ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እንዲያገለግሉ፣ የባንኩ ሲኒየር ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ (ኦፕሬሽን) ሆነው በማገልገል ላይ የሚገኙትን ወ/ሮ ጽጌሬዳ ተስፋዬን መሰየሙ ታውቋል፡፡

በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ልምድ አላቸው ተብለው ከሚጠቀሱ የባንክ ባለሙያዎች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ መላኩ፣ በኅብረት ባንክ ብቻ ከ20 ዓመታት በላይ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡ በተለይ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ከመሾማቸው በፊት፣ ከ11 ዓመታት በላይ በምክትል ሥራ አስፈጻሚነት ሲያገለግሉ ነበር፡፡

አቶ መላኩ በኅብረት ባንክ ቆይታቸው በተለይ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ የተከናወኑ ሥራዎችን በሙሉ በማስተባበርና በመምራት፣ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደነበራቸው ይጠቀሳል፡፡

ም/ፕሬዚዳንትና ዳይሬክተር በመሆን የዲጂታል የባንክ አገልግሎት ዘርፉን  ለ11 ዓመታት መምራታቸውን የተገኘው የባንኩ መረጃ ያስረዳል፡፡
Siket Bank registers 1.6 billion birr profit in first year after banking transition

Siket Bank, formerly known as Addis Credit and Saving S.C., has marked a significant milestone in its first year as a full-fledged bank, reporting an impressive profit of 1.6 billion birr for the 2023/24 financial year. This marks the end of a successful inaugural year since its transition from a microfinance institution to a commercial bank.

The bank, which became Ethiopia’s 32nd commercial bank after receiving approval from the National Bank of Ethiopia last year, earned more than 2.3 billion birr in revenue during the fiscal year. This represents a 42 percent increase in income compared to the previous year, when the institution was still operating as a microfinance entity.



Source: capitalethiopia
የአሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችለውን እንቅስቃሴ ጀመረ

የአሊባባ ግሩፕ (AliExpress) በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችለውን እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገለጸ።
የቻይናው አሊባባ ግሩፕ ከኢትዮጵያ አየር መንገድና ከኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማህበር ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ስራ ለመጀመር የሚያስችለውን እንቅስቃሴ መጀመሩን ይፋ ያደረገበት መድረክ ዛሬ ተካሄዷል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽሩን አለማየሁ(ዶ/ር) የአሊባባ አሊ ኤክስፕረስ በኢትዮጵያ ስራ መጀመሩ
ኢትዮጵያውያን ሸማቾችና ነጋዴዎች በአዲሱ የዓለም ገበያ ምርትና አገልግሎትን ለመገበያየትና ኢትዮጵያን ወደ ዓለም አቀፍ ንግድ እንዲገቡ ማስቻሉን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢኮሜርስ ሎጂስቲክስ አገልግሎት ስራ አስኪያጅ ቴዎድሮስ አያሌው አየር መንገዱ አሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የሚጀምረውን የኢኮሜርስ ስራ ለማሳለጥ የሚያስችል የኢኮሜርስ ሎጂስቲክስ አገልግሎትን የሚሰጥ ማዕከል(ሀብ) ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።

የአሊ ኤክስፕረስ ቢዝነስ ዳይሬክተር ጄፍሪ ጂያንግ ድርጅቱ በኢኮሜርስ ያለውን ዓለም አቀፍ ልምድ በመጠቀም የኢትዮጵያውያን ሸማቾችንና የንግድ ቦታዎችን እንቅስቃሴ ለማስተሳሰር እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ምንጭ :ኢዜአ
Source ~ Banks Ethiopia
@etstocks