#StockMarket
ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ የ ' ስቶክ ማርኬት ' ስራ እንደሚጀመር ተገለፀ።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በኢትዮጵያ የሚጀምረውን የ ' ስቶክ ማርኬት ' ለመደገፍ ከወዲሁ እንዲዘጋጅ ጥሪ አቅርበዋል።
ስቶክ ማርኬት በከፍተኛ ደረጃ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ይደግፋል ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ " በጣም ብዙ ሰው ሃሳብ አለው ገንዘብ የለውም፤ ጥቂት ሰዎች ደግሞ ገንዘብ አላቸው ሃሳብ የላቸውም ፤ ጥቂቶች ደግሞ ገንዘብ አላቸው ሃሳብም ገብቷቸዋል ተቋም የላቸውም ፤ ስቶክ ማርኬት ማለት ገንዘብ ያለውን ሃሳብ ያለውንና ተቋምን የሚያገናኝ ምርጥ ሀሳብ ማለት ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" ለአብነት ፦
- በአረብ ሀገራት ያሉ እህቶች ' ስቶክ ማርኬት ' ውስጥ ሼር ገዝተው እዛ እየሰሩ ኢንቨስት ማድረግ እንደሚችሉ ፤
- አርሶ አደሮችም ከስቶክ ማርኬት ሼር ገዝተው እያረሱ ኢንቨስት ማድረግ ይችላሉ ፤
- ዲያስፖራዎችም ወደ ሀገር ሲመለሱ ምንም የሌላቸው እንዳይሆኑ ከወዲሁ ዋና ዋና ኩባንያዎች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይችላሉ " ሲሉ ተናግረዋል።
ዶ/ር ዐቢይ ፤ ቴሌኮሚኒኬሽን በቅርቡ የተወሰነ ፐርሰንት ለህዝቡ እንደሚሸጥ አሳውቀዋል።
በሂደት ቴሌን፣ አየር መንገድን የህዝብ ተቋማት የማድረግ ስራ እንደሚሰራ አመልክተዋል።
" እኛ ሂልተንንም፣ ጊዮንንም፣ አየር መንገድንም፣ ቴሌኮምን ይዘን አንዘልቀውም " ያሉ ሲሆን እነዚህ ኩባንያዎች ላይ ብዙዎች ኢንቨስት እንዲያደርጉበት ካደረግን የተሻለ እድገት ሊያመጡ ይችላሉ፤ ለኢትዮጵያ እድገትም እገዛ ያደርጋል ሲሉ ተናግረዋል።
ለዚህም ተግባራዊነት ምክር ቤቱ ከወዲሁ ድጋፍ ለማድረግ እንዲዘጋጅ ጠይቀዋል።
#etstocks
ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ የ ' ስቶክ ማርኬት ' ስራ እንደሚጀመር ተገለፀ።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በኢትዮጵያ የሚጀምረውን የ ' ስቶክ ማርኬት ' ለመደገፍ ከወዲሁ እንዲዘጋጅ ጥሪ አቅርበዋል።
ስቶክ ማርኬት በከፍተኛ ደረጃ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ይደግፋል ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ " በጣም ብዙ ሰው ሃሳብ አለው ገንዘብ የለውም፤ ጥቂት ሰዎች ደግሞ ገንዘብ አላቸው ሃሳብ የላቸውም ፤ ጥቂቶች ደግሞ ገንዘብ አላቸው ሃሳብም ገብቷቸዋል ተቋም የላቸውም ፤ ስቶክ ማርኬት ማለት ገንዘብ ያለውን ሃሳብ ያለውንና ተቋምን የሚያገናኝ ምርጥ ሀሳብ ማለት ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" ለአብነት ፦
- በአረብ ሀገራት ያሉ እህቶች ' ስቶክ ማርኬት ' ውስጥ ሼር ገዝተው እዛ እየሰሩ ኢንቨስት ማድረግ እንደሚችሉ ፤
- አርሶ አደሮችም ከስቶክ ማርኬት ሼር ገዝተው እያረሱ ኢንቨስት ማድረግ ይችላሉ ፤
- ዲያስፖራዎችም ወደ ሀገር ሲመለሱ ምንም የሌላቸው እንዳይሆኑ ከወዲሁ ዋና ዋና ኩባንያዎች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይችላሉ " ሲሉ ተናግረዋል።
ዶ/ር ዐቢይ ፤ ቴሌኮሚኒኬሽን በቅርቡ የተወሰነ ፐርሰንት ለህዝቡ እንደሚሸጥ አሳውቀዋል።
በሂደት ቴሌን፣ አየር መንገድን የህዝብ ተቋማት የማድረግ ስራ እንደሚሰራ አመልክተዋል።
" እኛ ሂልተንንም፣ ጊዮንንም፣ አየር መንገድንም፣ ቴሌኮምን ይዘን አንዘልቀውም " ያሉ ሲሆን እነዚህ ኩባንያዎች ላይ ብዙዎች ኢንቨስት እንዲያደርጉበት ካደረግን የተሻለ እድገት ሊያመጡ ይችላሉ፤ ለኢትዮጵያ እድገትም እገዛ ያደርጋል ሲሉ ተናግረዋል።
ለዚህም ተግባራዊነት ምክር ቤቱ ከወዲሁ ድጋፍ ለማድረግ እንዲዘጋጅ ጠይቀዋል።
#etstocks
#StockMarket
(የኢትዮጵያን ምጣኔ ሀብታዊ ጉዳዮችን በቅርበት በሚከታተሉት አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ በአንድ ወቅት ለቢቢሲ ድረገፅ ከሰጡት ቃለምልልስ የተወሰደ)
ስቶክ ገበያ ምንድነው ?
ለስቶክ ማርኬት ‘ የድርሻ ገበያ ’ የሚል አቻ የአማርኛ ትርጉም ልንሰጠው እንችላለን።
ኩባንያዎች የኩባንያውን የባለቤትነት ድርሻ ለገበያ ያቀርባሉ።
ሰዎች ይህን ድርሻ ከገዙ በኋላ ኩባንያው ትርፋማ በሆነ መጠን ያላቸውን ድርሻ መልሰው በመሸጥ ወይም ከትርፍ ክፍፍል ትርፋማ የሚያደርግ አሠራር ነው።
ስቶክ ማርኬት ለኢትዮጵያ ምን ይዞ ይመጣል ?
የስቶክ ገበያ በዋናነኝነት ለኢትዮጵያ የሚከተሉትን ጥቅሞች ይዞ ይመጣል።
1. የካፒታል ገበያ
በርካታ የአገር ውስጥ ባንክ እንዲሁም ኢንሹራንሶች ሲመሠረቱ እና ከምሥረታቸውም በኋላ የአክሲዮን ድርሻዎችን ሲሸጡ ቆይረዋል።
የስቶክ ገበያን ከዚህ የተለየ የሚያደርገው ፤ ይፋዊ በሆነ መልኩ ተደራጅቶ ቁጥጥር እየተገደረገበት በግልጽ መገበያየት ማስቻሉ ነው።
የኢትዮጵያን ሴኪዩሪቲስ ኤክስቼንጅ እውን ሲሆን ፤ ባንኮች እና ኢንሹራንሶች ሲቋቋሙም ሆነ ማስፋፋት ሲፈልጉ አክሲዮን ለመሸጥ ይከተሉት የነበረውን ረዥም መንገድ ያሳጥርላቸዋል።
እነዚህ ኩባንያዎች ሲቋቋሙ ስቶክ ኤክስቼንጅ ስላልነበረ በጣም ረዥም ሂደት በማለፍ ለእያንዳንዱ ሰው እየዞሩ ነው ሼር የሚሸጡት።
ይህ ረዥም ጊዜ እና ገንዘብ ይወስዳል። አዋጭም አይደለም።
የኢትዮጵያን ሴኪዩሪቲስ ኤክስቼንጅ አንዱ ጥቅም አዲስ ለመሚሠረቱም ሆነ ለነባር ኩባንያዎች የካፒታል ገበያን መፍጠሩ ነው።
ካፒታል ማሰባሰብ ለሚፈልጉ ስቶክ ገበያ መልካም አማራጭ ነው።
ጥሩ ሐሳብ ኖሯቸው የካፒታል እጥረት ላለባቸው ሰዎች ይጠቅማል።
ዛሬ ላይ ከባንክ ብድር ማግኘትም ቀላል አይለደም። ለዘመድ ወይም ለጓደኛ ሼር የመሸጥ ሂደት ቀላል አይደለም። ስቶክ ማርኬት አዲስ ለሆኑም ይሁን መስፋፋት ለሚፈልጉ ኩባንያዎች የካፒታል ገበያን ይፈጥራል።
2. ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል
የስቶክ ገበያ ፣ ፍትሐዊ እና ተመጣጣኝ በሆነ ሁኔታ ሀብት ማከፋፈል የሚችል ሥርዓት ነው።
በአሁኑ ጊዜ ግዙፍ መንግሥታዊ ኩባንያዎች ወደ ግሉ ዘርፍ እየተሸጋገሩ ነው።
እነዚህ ከመንግሥት ወደ ግሉ የሚዘዋወሩት ግዙፍ ኩባንያዎችን ሲገዙ የቆዩት ጥቂት ግለሰቦች እና ኮርፖሬሽኖች ናቸው። ስቶክ ማርኬት ሲመጣ ግን መንግሥት የሕዝብን ሀብት ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ማከፋፈል ይችላል።
ስቶክ ማርኬት ላይ 1 ሼር በአምስትም፣ በአሥርም ዶላር ሲሸጥ ሁሉም የየአቅሙን በመግዛት ኢትዮጵያ ያካበተችውን ሀብት ማከፋፈል ይቻላል።
እነዚህ ወደ ግሉ ዘርፍ የሚዘዋወሩ ኩባንያዎች ወደ ስቶክ ገበያው ሲገቡ፣ ሁሉም የአቅሙን ያህል ባለቤት ይሆናል። ይህም የሀብት ክፍፍልን ያመጣል።
3. ቁጠባ እና የኢንቨስትመንት አማራጭን ማስፋት
የቁጠባ ባህልን ከፍ ያደርጋል። ሰዎች በአሁኑ ጊዜ ኪሳራ አያስከትልም ብለው በሚያስቡት ዘርፍ ላይ ብቻ መዋዕለ ንዋያቸውን እያፈሰሱ ይገኛሉ።
ገንዘብ ያላቸው ሰዎች #የቤቶች_ልማት ላይ ብቻ ትኩረት ሲያደርጉ ይታያል። የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ደግሞ ተጎድቷል። ይህም ኢንቨስት የሚደረግባቸው ዘርፎችን ውስን በማድረግ የቁጠባ አለመመጣጠን ይፈጥራል።
ስቶክ ማርኬቱ ግን ውጤታማ በሆነ መንገድ ካፒታል በሁሉም ዘርፎች ላይ ማሰራጨት ያስችላል።
4. ግልጽነት
የድርሻ ገበያዎችን በቀላሉ፣ ግልጸኝነት በሰፈነበት መልኩ መግዛት እና መሸጥ ማስቻሉ ነው።
ምን ያህል ሼር በምን ያህል ዋጋ ለገበያ እንደቀረበ ግልጽ ነው።
ሰዎች ስልካቸው ላይ በሚጭኑት መተግበሪያ በቀላሉ የገበያ ድርሻዎችን መግዛት እና የገዙትንም መሸጥ ይችላሉ።
የባንክ ባለ አክሲዮኖች ዓመት ጠብቀው ትርፍ ከመከፋፈል ውጪ በቀላሉ ያላቸውን አክሲዮን መሸጥ አይቻላቸውም።
ስቶክ ማርኬት ሲሆን በቀላሉ አክሲዮን የመሸጥ ዕድል ይዘረጋል።
በስቶክ ገበያ ትርፍና ኪሳራ እንዴት ያጋጥማል ?
ይህንን ጥያቄ ከመመለሳችን በፊት ስቶክ ገበያ ምንድን ነው ? እንዴትስ መሸጥ እና መለወጥ ይቻላል ? የሚለውን እንመልከት።
ስቶክ ገበያን በቀላል ቋንቋ ለመረዳት የምጣሄ ሀብት ባለሙያዎች አዘወትረው የሚጠቀሙትን ቀላል ምሳሌ እንውሰድ። 'ሀ'፣ 'ለ' እና 'ሐ' የሚባሉ ሦስት ምናባዊ የሞባይል ስልክ አምራች ኩባንያዎችን አሉ አንበል።
እርስዎ 6 ዶላር አውጥተው ከእያንዳንዱ ኩባንያ የሁለት ዶላር የገበያ ድርሻ ይገዛሉ።
'ሀ' ለገበያ ያቀረበው ሞባይል ስልክ ባትሪ እየፈነዳ ሰዎችን ለጉዳት እየዳረገ መሆኑን የሚያመለክት ሪፖርት መውጣት ይጀምራል።
የ'ለ' ኩባንያ የሆነው ምርት ደግሞ ባትሪ በፍጥነት እያለቀ ከተጠቃሚዎች ቅሬታ ይደርሰዋል።
የ'ሐ' ምርት የሆነው ሞባይል ስልክ ግን በአግባቡ ይሠራል።
ይህ በገበያ ላይ ያጋጠመው ክስተት በሦስቱ ኩባንያዎች ስቶክ ገበያ ዋጋ ላይ ለውጥ ያመጣል። የአንድ ኩባንያ ምርት ጥራት ሲወርድ የዚያ ኩባንያ ፈላጊዎች ይቀንሳሉ።
በተቀራኒው አንድ ኩባንያ ትርፍማ የሚያደርገውን ውሳኔ ወስኖ ትርፍ ሲያጋብስ፣ የትርፉ ተቋዳሽ መሆን የሚሹ ሰዎች ቁጥር ከፍ ይላል።
በዚህ መሠረት ባትሪው እየፈነዳ ሰዎችን ለአደጋ እያጋለጠ ያለው የሞባይል ኩባንያ ድርሻ በከፍተኛ መጠን ሊወርድ ይችላል።
በሁለት ዶላር የገዙትን ድርሻ መልሰው መሸጥ ቢፈልጉ ከግማሸ ባነሰ ዋጋ እንኳን የሚገዛዎትን ላያገኙ ይችላሉ።
ይህ ሞባይል አምራች ኩባንያ ሲከስር እርስዎም የኩባንያው ባለድርሻ እንደመሆንዎ ኪሳራ ያጋጥምዎታል።
ስለዚህ በኩባንያ 'ሀ' ላይ ያደረጉት ኢንቨስትመንት ኪሳራን ያስከትላል።
የ 'ሐ' ምርት የሆነው ስልክ ግን በገበያ ተፈላጊነቱ ሲጨምር የኩባንያው ዋጋም ከፍ ይላል።
ምናልባት በሁለት ዶላር የገዙትን የኩባንያውን ድርሻ፣ አሁን ላይ በ4 ዶላር ሸጠው ትርፍ ሊያገኙ ይችላሉ።
@etstocks
(የኢትዮጵያን ምጣኔ ሀብታዊ ጉዳዮችን በቅርበት በሚከታተሉት አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ በአንድ ወቅት ለቢቢሲ ድረገፅ ከሰጡት ቃለምልልስ የተወሰደ)
ስቶክ ገበያ ምንድነው ?
ለስቶክ ማርኬት ‘ የድርሻ ገበያ ’ የሚል አቻ የአማርኛ ትርጉም ልንሰጠው እንችላለን።
ኩባንያዎች የኩባንያውን የባለቤትነት ድርሻ ለገበያ ያቀርባሉ።
ሰዎች ይህን ድርሻ ከገዙ በኋላ ኩባንያው ትርፋማ በሆነ መጠን ያላቸውን ድርሻ መልሰው በመሸጥ ወይም ከትርፍ ክፍፍል ትርፋማ የሚያደርግ አሠራር ነው።
ስቶክ ማርኬት ለኢትዮጵያ ምን ይዞ ይመጣል ?
የስቶክ ገበያ በዋናነኝነት ለኢትዮጵያ የሚከተሉትን ጥቅሞች ይዞ ይመጣል።
1. የካፒታል ገበያ
በርካታ የአገር ውስጥ ባንክ እንዲሁም ኢንሹራንሶች ሲመሠረቱ እና ከምሥረታቸውም በኋላ የአክሲዮን ድርሻዎችን ሲሸጡ ቆይረዋል።
የስቶክ ገበያን ከዚህ የተለየ የሚያደርገው ፤ ይፋዊ በሆነ መልኩ ተደራጅቶ ቁጥጥር እየተገደረገበት በግልጽ መገበያየት ማስቻሉ ነው።
የኢትዮጵያን ሴኪዩሪቲስ ኤክስቼንጅ እውን ሲሆን ፤ ባንኮች እና ኢንሹራንሶች ሲቋቋሙም ሆነ ማስፋፋት ሲፈልጉ አክሲዮን ለመሸጥ ይከተሉት የነበረውን ረዥም መንገድ ያሳጥርላቸዋል።
እነዚህ ኩባንያዎች ሲቋቋሙ ስቶክ ኤክስቼንጅ ስላልነበረ በጣም ረዥም ሂደት በማለፍ ለእያንዳንዱ ሰው እየዞሩ ነው ሼር የሚሸጡት።
ይህ ረዥም ጊዜ እና ገንዘብ ይወስዳል። አዋጭም አይደለም።
የኢትዮጵያን ሴኪዩሪቲስ ኤክስቼንጅ አንዱ ጥቅም አዲስ ለመሚሠረቱም ሆነ ለነባር ኩባንያዎች የካፒታል ገበያን መፍጠሩ ነው።
ካፒታል ማሰባሰብ ለሚፈልጉ ስቶክ ገበያ መልካም አማራጭ ነው።
ጥሩ ሐሳብ ኖሯቸው የካፒታል እጥረት ላለባቸው ሰዎች ይጠቅማል።
ዛሬ ላይ ከባንክ ብድር ማግኘትም ቀላል አይለደም። ለዘመድ ወይም ለጓደኛ ሼር የመሸጥ ሂደት ቀላል አይደለም። ስቶክ ማርኬት አዲስ ለሆኑም ይሁን መስፋፋት ለሚፈልጉ ኩባንያዎች የካፒታል ገበያን ይፈጥራል።
2. ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል
የስቶክ ገበያ ፣ ፍትሐዊ እና ተመጣጣኝ በሆነ ሁኔታ ሀብት ማከፋፈል የሚችል ሥርዓት ነው።
በአሁኑ ጊዜ ግዙፍ መንግሥታዊ ኩባንያዎች ወደ ግሉ ዘርፍ እየተሸጋገሩ ነው።
እነዚህ ከመንግሥት ወደ ግሉ የሚዘዋወሩት ግዙፍ ኩባንያዎችን ሲገዙ የቆዩት ጥቂት ግለሰቦች እና ኮርፖሬሽኖች ናቸው። ስቶክ ማርኬት ሲመጣ ግን መንግሥት የሕዝብን ሀብት ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ማከፋፈል ይችላል።
ስቶክ ማርኬት ላይ 1 ሼር በአምስትም፣ በአሥርም ዶላር ሲሸጥ ሁሉም የየአቅሙን በመግዛት ኢትዮጵያ ያካበተችውን ሀብት ማከፋፈል ይቻላል።
እነዚህ ወደ ግሉ ዘርፍ የሚዘዋወሩ ኩባንያዎች ወደ ስቶክ ገበያው ሲገቡ፣ ሁሉም የአቅሙን ያህል ባለቤት ይሆናል። ይህም የሀብት ክፍፍልን ያመጣል።
3. ቁጠባ እና የኢንቨስትመንት አማራጭን ማስፋት
የቁጠባ ባህልን ከፍ ያደርጋል። ሰዎች በአሁኑ ጊዜ ኪሳራ አያስከትልም ብለው በሚያስቡት ዘርፍ ላይ ብቻ መዋዕለ ንዋያቸውን እያፈሰሱ ይገኛሉ።
ገንዘብ ያላቸው ሰዎች #የቤቶች_ልማት ላይ ብቻ ትኩረት ሲያደርጉ ይታያል። የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ደግሞ ተጎድቷል። ይህም ኢንቨስት የሚደረግባቸው ዘርፎችን ውስን በማድረግ የቁጠባ አለመመጣጠን ይፈጥራል።
ስቶክ ማርኬቱ ግን ውጤታማ በሆነ መንገድ ካፒታል በሁሉም ዘርፎች ላይ ማሰራጨት ያስችላል።
4. ግልጽነት
የድርሻ ገበያዎችን በቀላሉ፣ ግልጸኝነት በሰፈነበት መልኩ መግዛት እና መሸጥ ማስቻሉ ነው።
ምን ያህል ሼር በምን ያህል ዋጋ ለገበያ እንደቀረበ ግልጽ ነው።
ሰዎች ስልካቸው ላይ በሚጭኑት መተግበሪያ በቀላሉ የገበያ ድርሻዎችን መግዛት እና የገዙትንም መሸጥ ይችላሉ።
የባንክ ባለ አክሲዮኖች ዓመት ጠብቀው ትርፍ ከመከፋፈል ውጪ በቀላሉ ያላቸውን አክሲዮን መሸጥ አይቻላቸውም።
ስቶክ ማርኬት ሲሆን በቀላሉ አክሲዮን የመሸጥ ዕድል ይዘረጋል።
በስቶክ ገበያ ትርፍና ኪሳራ እንዴት ያጋጥማል ?
ይህንን ጥያቄ ከመመለሳችን በፊት ስቶክ ገበያ ምንድን ነው ? እንዴትስ መሸጥ እና መለወጥ ይቻላል ? የሚለውን እንመልከት።
ስቶክ ገበያን በቀላል ቋንቋ ለመረዳት የምጣሄ ሀብት ባለሙያዎች አዘወትረው የሚጠቀሙትን ቀላል ምሳሌ እንውሰድ። 'ሀ'፣ 'ለ' እና 'ሐ' የሚባሉ ሦስት ምናባዊ የሞባይል ስልክ አምራች ኩባንያዎችን አሉ አንበል።
እርስዎ 6 ዶላር አውጥተው ከእያንዳንዱ ኩባንያ የሁለት ዶላር የገበያ ድርሻ ይገዛሉ።
'ሀ' ለገበያ ያቀረበው ሞባይል ስልክ ባትሪ እየፈነዳ ሰዎችን ለጉዳት እየዳረገ መሆኑን የሚያመለክት ሪፖርት መውጣት ይጀምራል።
የ'ለ' ኩባንያ የሆነው ምርት ደግሞ ባትሪ በፍጥነት እያለቀ ከተጠቃሚዎች ቅሬታ ይደርሰዋል።
የ'ሐ' ምርት የሆነው ሞባይል ስልክ ግን በአግባቡ ይሠራል።
ይህ በገበያ ላይ ያጋጠመው ክስተት በሦስቱ ኩባንያዎች ስቶክ ገበያ ዋጋ ላይ ለውጥ ያመጣል። የአንድ ኩባንያ ምርት ጥራት ሲወርድ የዚያ ኩባንያ ፈላጊዎች ይቀንሳሉ።
በተቀራኒው አንድ ኩባንያ ትርፍማ የሚያደርገውን ውሳኔ ወስኖ ትርፍ ሲያጋብስ፣ የትርፉ ተቋዳሽ መሆን የሚሹ ሰዎች ቁጥር ከፍ ይላል።
በዚህ መሠረት ባትሪው እየፈነዳ ሰዎችን ለአደጋ እያጋለጠ ያለው የሞባይል ኩባንያ ድርሻ በከፍተኛ መጠን ሊወርድ ይችላል።
በሁለት ዶላር የገዙትን ድርሻ መልሰው መሸጥ ቢፈልጉ ከግማሸ ባነሰ ዋጋ እንኳን የሚገዛዎትን ላያገኙ ይችላሉ።
ይህ ሞባይል አምራች ኩባንያ ሲከስር እርስዎም የኩባንያው ባለድርሻ እንደመሆንዎ ኪሳራ ያጋጥምዎታል።
ስለዚህ በኩባንያ 'ሀ' ላይ ያደረጉት ኢንቨስትመንት ኪሳራን ያስከትላል።
የ 'ሐ' ምርት የሆነው ስልክ ግን በገበያ ተፈላጊነቱ ሲጨምር የኩባንያው ዋጋም ከፍ ይላል።
ምናልባት በሁለት ዶላር የገዙትን የኩባንያውን ድርሻ፣ አሁን ላይ በ4 ዶላር ሸጠው ትርፍ ሊያገኙ ይችላሉ።
@etstocks
A 50 million birr equity investment is made by Siinqee Bank in the Ethiopian Securities Exchange (ESX).
Source:#Capital
According to the soon-to-be secondary market platform, Siinqee Bank's investment in the ESX will move the launch date of the exchange closer to reality as it strives to operationalize by the fourth quarter of 2024.
It went on to note that this investment is a testament of the Bank's long-standing commitment to societal financial empowerment, which has lasted for more than 29 years and contributed in Ethiopia's economic growth. The Bank was recently upgraded from microfinance.
It is anticipated that the 50 million equity investment from Siinqee will represent 5 percent of the shares in ESX's paid capital.
In addition to Ethiopian Investment Holdings (EIH) and its 4 subsidiaries who provided initial investment, Siinqee Bank will also be joined other investors who will be signing as shareholders before ESX winds up its capital raise.
Zemen Bank was the first to arrive at a decision to become a private investor with a share in the stock exchange.
It is anticipated that ESX will be founded with one billion birr in funding.
#investment #ESx #Ethiopia #capitalmarkets #stocks #stockmarket
Source:#Capital
According to the soon-to-be secondary market platform, Siinqee Bank's investment in the ESX will move the launch date of the exchange closer to reality as it strives to operationalize by the fourth quarter of 2024.
It went on to note that this investment is a testament of the Bank's long-standing commitment to societal financial empowerment, which has lasted for more than 29 years and contributed in Ethiopia's economic growth. The Bank was recently upgraded from microfinance.
It is anticipated that the 50 million equity investment from Siinqee will represent 5 percent of the shares in ESX's paid capital.
In addition to Ethiopian Investment Holdings (EIH) and its 4 subsidiaries who provided initial investment, Siinqee Bank will also be joined other investors who will be signing as shareholders before ESX winds up its capital raise.
Zemen Bank was the first to arrive at a decision to become a private investor with a share in the stock exchange.
It is anticipated that ESX will be founded with one billion birr in funding.
#investment #ESx #Ethiopia #capitalmarkets #stocks #stockmarket
የተወሰነ ድርሻቸውን ለሕዝብ የሚሸጡ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ተለዩ!
*
#ሪፖርተር
»ባህር ትራንስፖርትና የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በድርሻ ሽያጩ ተካተዋል።
በሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ላይ የተወሰ ድርሻቸውን ለሕዝብ የሚሸጡ ስድስት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች መለየታቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ (Ethiopian Investment Holdings – EIH) ኃላፊዎች ገለጹ፡፡
በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያን መጀመር አስመልክቶ የተወሰኑ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች (State Owned Enterprises) ውስን ድርሻዎቻቸውን በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ላይ እንደሚሸጡ ሲገለጽ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
ከቅርብ ጊዜያት በፊት ይፋ እንደሆነውም መንግሥት የኢትዮ ቴሌኮምን አሥር በመቶ ድርሻ ለሕዝብ እንደሚሸጥ ገልጾ ነበር፡፡ ምን ያህል መጠናቸው እንደሆነ ውሳኔ ላይ ባይደረስም ሌሎች አምስት የልማት ድርጅቶች ድርሻዎቻቸው በገበያው ላይ እንዲሸጡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ መወሰኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አብዱረህማን ዒድ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ድርሻቸው ለሽያጭ የሚቀርበው የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት (አባትሎአድ)፣ የኢትዮጵያ መድኅን ድርጅት፣ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት፣ የትምህርት ማምረቻና ማሠራጫ ድርጅትና የኢትዮጵያ የቱሪስት ንግድ ሥራ ድርጅት ሲሆኑ፣ አምስቱ ተጨማሪ የልማት ድርጅቶች፣ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመሆን ስድስት ድርጅቶች ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ላይ ድርሻቸውን ይሸጣሉ፡፡
ከትምህርት ማምረቻና ማሠራጫ ድርጅትና ከኢትዮጵያ የቱሪስት ንግድ ሥራ ድርጅት ውጭ ያሉት አራቱ የልማት ድርጅቶች፣ በበላይ ከሚቆጣጠራቸው ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ጋር አምስት በመሆን የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን (ESX) 25 በመቶ ድርሻ በመግዛት ገበያውን በዚህ ዓመት መስከረም ወር ላይ ማቋቋማቸው የሚታወስ ነው፡፡
እንደ አቶ አብዱረህማን ገለጻ፣ እነዚህን አራቱ ድርጅቶች የገበያውን አክሲዮን ገዝተው እንዲያቋቁሙ የተመረጡበት ምክንያትም በገበያው ላይ በኋላ ድርሻቸውን እንዲሸጡ በመወሰኑ ነው፡፡ በኋላ ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአራቱ የልማት ድርጅቶችና ከሆልዲንጉ ጋር በመግባት ስድስተኛ ተቋም ሆኖ የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይን 25 በመቶ ድርሻ በጋራ መግዛቱ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድርሻቸውን እንደ ኢትዮ ቴሌኮምና ሌሎቹ የልማት ድርጅቶች ለሕዝብ እንዲሸጥ አለመወሰኑን አቶ አብዱረህማን ተናግረዋል፡፡
‹‹የንግድ ባንክ አሁን አይሆንም፡፡ ምናልባት ወደፊት ከሆነ እንጂ አሁን አልተወሰነም፤›› ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ ‹‹ኢትዮ ቴሌኮም በጣም ግዙፍ ድርጅት ነው፣ የእሱን ድርሻ በተወሰነ መጠን ከሸጥን የንግድ ባንክ አለመሸጥ ምንም አይደል፤›› ሲሉ አክለዋል፡፡
የኢትዮጵያ መድኅን ድርጅትም ግዙፍ መሆኑንና ከ50 በመቶ በላይ የመድኅን ገበያውን የሚቆጣጠር መሆኑን፣ ኢባትሎአድም በጣም ትልቅ ድርጅት እንደሆነ፣ እንዲሁም ብርሃንና ሰላም በአገሪቱ ትልቁ የኅትመት ድርጅት እንደሆነ ያስታወሱት አቶ አብዱረህማን፣ የእነዚህ ድርጅቶች በገበያው ላይ መቅረብ ትልቅ ነገር እንደሆነ ለሪፖርተር አብራርተዋል፡፡
ድርጅቶቹ ምን ያህል የድርሻ መጠናቸውን ለሕዝብ እንደሚያቀርቡ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ሥራ አስፈጻሚው፣ ‹‹የኢትዮ ቴሌኮም አሥር በመቶ እንደሆነ ይታወቃል፣ ነገር ግን ሌሎቹ ምን ያህል መጠናቸውን እንደሆነ የሚሸጡት ገና አልወሰንም፤›› ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ በውጭ አጋሮቹ ድጋፍ በቅርብ የድርጅቱን ዝግጁነት እያስጠና ሲሆን፣ በገበያው ላይ ለመሸጥ በጣም ጥብቅ የሆኑ መሟላት ያለባቸውን መሥፈርቶች ማሟላት ያለባቸው እንዳሉ ተገልጿል፡፡
የልማት ድርጅቶቹ በገበያው ለመቅረብ ምን መቀየር እንዳለባቸው ሐሳቡ ያላቸው መሆኑን፣ በዚህ ሳምንትም ጨምሮ በየጊዜው ጥልቅ ውይይት እንደሚያደርጉ አቶ አብዱረህማን ተናግረዋል፡፡
ሆልዲንጉ በካፒታል ገበያ ላይ ትኩረ አድርጎ የሚሠራ ልዩ ቡድን የሚያቋቁም ሲሆን፣ ቡድኑ የልማት ድርጅቶቹን ለገበያ ለማቅረብ እንዲዘጋጁ የሚያግዛቸው ይሆናል፡፡
#ESX #Stockmarket #ኢትዮጵያ #አክሲዮን
*
#ሪፖርተር
»ባህር ትራንስፖርትና የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በድርሻ ሽያጩ ተካተዋል።
በሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ላይ የተወሰ ድርሻቸውን ለሕዝብ የሚሸጡ ስድስት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች መለየታቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ (Ethiopian Investment Holdings – EIH) ኃላፊዎች ገለጹ፡፡
በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያን መጀመር አስመልክቶ የተወሰኑ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች (State Owned Enterprises) ውስን ድርሻዎቻቸውን በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ላይ እንደሚሸጡ ሲገለጽ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
ከቅርብ ጊዜያት በፊት ይፋ እንደሆነውም መንግሥት የኢትዮ ቴሌኮምን አሥር በመቶ ድርሻ ለሕዝብ እንደሚሸጥ ገልጾ ነበር፡፡ ምን ያህል መጠናቸው እንደሆነ ውሳኔ ላይ ባይደረስም ሌሎች አምስት የልማት ድርጅቶች ድርሻዎቻቸው በገበያው ላይ እንዲሸጡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ መወሰኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አብዱረህማን ዒድ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ድርሻቸው ለሽያጭ የሚቀርበው የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት (አባትሎአድ)፣ የኢትዮጵያ መድኅን ድርጅት፣ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት፣ የትምህርት ማምረቻና ማሠራጫ ድርጅትና የኢትዮጵያ የቱሪስት ንግድ ሥራ ድርጅት ሲሆኑ፣ አምስቱ ተጨማሪ የልማት ድርጅቶች፣ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመሆን ስድስት ድርጅቶች ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ላይ ድርሻቸውን ይሸጣሉ፡፡
ከትምህርት ማምረቻና ማሠራጫ ድርጅትና ከኢትዮጵያ የቱሪስት ንግድ ሥራ ድርጅት ውጭ ያሉት አራቱ የልማት ድርጅቶች፣ በበላይ ከሚቆጣጠራቸው ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ጋር አምስት በመሆን የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን (ESX) 25 በመቶ ድርሻ በመግዛት ገበያውን በዚህ ዓመት መስከረም ወር ላይ ማቋቋማቸው የሚታወስ ነው፡፡
እንደ አቶ አብዱረህማን ገለጻ፣ እነዚህን አራቱ ድርጅቶች የገበያውን አክሲዮን ገዝተው እንዲያቋቁሙ የተመረጡበት ምክንያትም በገበያው ላይ በኋላ ድርሻቸውን እንዲሸጡ በመወሰኑ ነው፡፡ በኋላ ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአራቱ የልማት ድርጅቶችና ከሆልዲንጉ ጋር በመግባት ስድስተኛ ተቋም ሆኖ የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይን 25 በመቶ ድርሻ በጋራ መግዛቱ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድርሻቸውን እንደ ኢትዮ ቴሌኮምና ሌሎቹ የልማት ድርጅቶች ለሕዝብ እንዲሸጥ አለመወሰኑን አቶ አብዱረህማን ተናግረዋል፡፡
‹‹የንግድ ባንክ አሁን አይሆንም፡፡ ምናልባት ወደፊት ከሆነ እንጂ አሁን አልተወሰነም፤›› ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ ‹‹ኢትዮ ቴሌኮም በጣም ግዙፍ ድርጅት ነው፣ የእሱን ድርሻ በተወሰነ መጠን ከሸጥን የንግድ ባንክ አለመሸጥ ምንም አይደል፤›› ሲሉ አክለዋል፡፡
የኢትዮጵያ መድኅን ድርጅትም ግዙፍ መሆኑንና ከ50 በመቶ በላይ የመድኅን ገበያውን የሚቆጣጠር መሆኑን፣ ኢባትሎአድም በጣም ትልቅ ድርጅት እንደሆነ፣ እንዲሁም ብርሃንና ሰላም በአገሪቱ ትልቁ የኅትመት ድርጅት እንደሆነ ያስታወሱት አቶ አብዱረህማን፣ የእነዚህ ድርጅቶች በገበያው ላይ መቅረብ ትልቅ ነገር እንደሆነ ለሪፖርተር አብራርተዋል፡፡
ድርጅቶቹ ምን ያህል የድርሻ መጠናቸውን ለሕዝብ እንደሚያቀርቡ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ሥራ አስፈጻሚው፣ ‹‹የኢትዮ ቴሌኮም አሥር በመቶ እንደሆነ ይታወቃል፣ ነገር ግን ሌሎቹ ምን ያህል መጠናቸውን እንደሆነ የሚሸጡት ገና አልወሰንም፤›› ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ በውጭ አጋሮቹ ድጋፍ በቅርብ የድርጅቱን ዝግጁነት እያስጠና ሲሆን፣ በገበያው ላይ ለመሸጥ በጣም ጥብቅ የሆኑ መሟላት ያለባቸውን መሥፈርቶች ማሟላት ያለባቸው እንዳሉ ተገልጿል፡፡
የልማት ድርጅቶቹ በገበያው ለመቅረብ ምን መቀየር እንዳለባቸው ሐሳቡ ያላቸው መሆኑን፣ በዚህ ሳምንትም ጨምሮ በየጊዜው ጥልቅ ውይይት እንደሚያደርጉ አቶ አብዱረህማን ተናግረዋል፡፡
ሆልዲንጉ በካፒታል ገበያ ላይ ትኩረ አድርጎ የሚሠራ ልዩ ቡድን የሚያቋቁም ሲሆን፣ ቡድኑ የልማት ድርጅቶቹን ለገበያ ለማቅረብ እንዲዘጋጁ የሚያግዛቸው ይሆናል፡፡
#ESX #Stockmarket #ኢትዮጵያ #አክሲዮን