ET Securities
675 subscribers
593 photos
7 videos
30 files
300 links
At ET Securities, our goal is to provide services in the financial sector, with a special focus on capital markets and financial markets.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
The Ethiopian Securities Exchange has just commenced its Capital raise Roadshow today. ESX is showcasing its Business plan and Financials to prospective investors from the financial industry. 25% of ESX is owned by the Government of Ethiopia through Ethiopian Investment Holdings and the remaining 75% is open to both international and domestic private investors. More on https://www.condoaddis.com/230517 -----------------------------------------------------------------------------------------የኢትዮጵያ ሴኩሪቲስ ገበያ የካፒታል ማሳደጊያ ሮድሾው ዛሬ ጀምሯል። ESX የቢዝነስ እቅዱን እና ፋይናንሺያልን ከፋይናንሺያል ኢንደስትሪ ለሚመጡ ኢንቨስተሮች እያሳየ ነው። የኢኤስኤክስ 25 በመቶው በኢትዮጵያ መንግስት ባለቤትነት የተያዘው በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በኩል ሲሆን ቀሪው 75 በመቶው ለአለም አቀፍ እና ለአገር ውስጥ የግል ባለሀብቶች ክፍት ነው። ተጨማሪ በ https://www.condoaddis.com/230517 ላይ
ሙዓለ ንዋይ ገበያ ለማቋቋም አንድ ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ታወቀ

፦መንግሥት 25 በመቶ የግል ኢንቨስተሮች ደግሞ 75 በመቶ ድርሻ ይኖራቸዋል

የኢትዮጵያ ‹‹የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ›› ለማቋቋም አንድ ቢሊዮን ብር ገደማ የመነሻ ካፒታል ያስፈልጋል ተባለ፡፡

በ2016 ዓ.ም. ወደ ሥራ የሚገባው የሙዓለ ንዋይ ገበያው ትርፍ ለማስመዝገብ ከሦስት እስከ አራት ዓመታት እንደሚፈጅበት፣ በጥናት መታወቁን የሪፖርተር ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡

በሙዓለ ንዋይ ገበያው ውስጥ መንግሥት 25 በመቶ ድርሻ እንደሚኖረው፣ ይህም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ በኩል 250 ሚሊዮን ብር ገደማ ያወጣል ተብሏል፡፡ የተቀረው 75 በመቶ ወይም 750 ሚሊዮን ብር ገደማ ደግሞ ለግል ኢንቨስተሮች ከሚሸጥ አክሲዮን እንደሚሰበሰብ ተገልጿል፡፡ ለግል ኢንቨስተሮች አክሲዮን የመሸጥ ሥራ ማክሰኞ ግንቦት 8 ቀን 2015 ዓ.ም. በይፋ ተጀምሯል፡፡

ሪፖርተር ያነጋገራቸው ባለሙያዎች አንድ ቢሊዮን ብር መነሻ ካፒታል ትንሽ ቢሆንም፣ በሌላ በኩል ደግሞ መነሻ ካፒታሉን ከዚያ በላይ ከፍ ማድረግ፣ ትርፍ የማስገኛ ጊዜውን ስለሚያረዝም ጉዳት ይኖረዋል ብለዋል፡፡

የሙዓለ ንዋይ ገበያው ሥራ ለማስጀመር ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ፈቃድ ማግኘት ያስፈልጋል፡፡ ባለሥልጣኑ ከስድስት ወራት በፊት የተቋቋመ ሲሆን፣ ፈቃድ ለመስጠት የሚያስፈልጉ በርካታ ሕጎችን እያዘጋጀ ነው፡፡ ሕጎቹ ከፀደቁ በኋላ ማንኛውም ሰው አክሲዮን ሸጦ ድርጅት ለማቋቋም ከባለሥልጣኑ ፈቃድ ማግኘት ይኖርበታል፡፡

የሙዓለ ንዋይ ገበያው በሚቀጥለው ዓመት በአንድ ቢሊዮን ብር መነሻ ካፒታል ወደ ሥራ እስኪገባ ድረስ፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ የማስተባበርና ከግል ኢንቨስተሮች የሚሰበሰበውን አክሲዮን የመሸጥ ሥራ ያከናውናል ተብሏል፡፡

የባለሥልጣኑ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ማቋቋሚያ ሒደት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የተውጣጡ ባለሙያዎች፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥና የገንዘብ ሚኒስትሩ ትናንት ማክሰኞ ግንቦት 8 ቀን 2015 ዓ.ም. ትናንት በሸራተን አዲስ ከባንክና ኢንሹራንስ ኃላፊዎች ጋር ዝግ ስብሰባ አድርገዋል፡፡

‹‹ባንኮችና የኢንሹራንስ ተቋማት ለካፒታል ገበያ ቅርብ ስለሆኑ የመጀመርያዎቹ ኢንቨስተሮች ይሆናሉ ብለን እንጠብቃለን፡፡ ሌሎች የአገር ውስጥና የውጭ ኢንቨስተሮችም አክሲዮን መግዛት ይችላሉ፤›› ሲሉ የሙዓለ ንዋይ ገበያው ምሥረታ ሒደት አስተባባሪ ኃላፊ ጥላሁን እስማኤል (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

የግልና የመንግሥት ጡረታ ተቋማት በቀዳሚነት ኢንቨስት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ኢትዮ ቴሌኮምና የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ 26 አትራፊ የሆኑ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሥር ያሉ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ አራቱ 250 ሚሊዮን ብር የመንግሥትን ድርሻ ያዋጣሉ ተብሏል፡፡ የተቀሩት ደግሞ ሙዓለ ንዋይ ገበያው ሲቋቋም አክሲዮኖቻቸው ለሽያጭ እንደሚቀርቡ ታውቋል፡፡

የውጭ ኢንቨስተሮችን ለመሳብ በቅርቡ በኬንያ፣ በእንግሊዝ፣ በተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና በሌሎች አገሮች የማስተዋወቅ ሥራ እንደሚጀመር ለማወቅ ተችሏል፡፡
የሙዓለ ንዋይ ገበያ ማለት ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች (Securities) ወይም አክሲዮኖች የሚገዙበትና የሚሸጡበት በቴክኖሎጂ የታገዘ ገበያ ነው፡፡

ነባር ባለአክሲዮኖች አክሲዮን የሚሻሻጡበት፣ እንዲሁም አዲስ ድርጅት የማቋቋም ሐሳብ ያላቸው ገንዘብ የሚያሰባስቡበት ገበያ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የዕዳ ገበያን ጨምሮ ብዙ ተግባራት ይኖሩታል ተብሎ በአዋጅ ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡(ሪፖርተር)


- በዌብሳይት :- condoaddis.com/230517-2
- በፌስቡክ ፡- https://fb.me/etstocks

ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑን እናመሰግናለን
ቅዳሜ ጠዋት ግንቦት 5 እና 7 ቀን 2015 ዓም በኢትዮ የንግድ እና ኢንቨስትመንት መድረክ

-በቢዝነስ ቅኝት የሰሞኑ የቢዝነስ ዜናዎች ቀርበዋል።

-በእንግዳ ሰዓት በምስረታ ላይ ስላለዉ የካፒታል ገበያ ተወያይተናል።

እንግዳችን የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ናቸዉ፡፡

ከዶ/ር ብሩክ ታዬ ጋር ስለ ካፒታል ገበያ አመሰራረት እና አሁናዊ ሁኔታ ዙሪያ ረዘም ያለ ቆይታ አድርገናል፡፡

የመጀመሪያውን ክፍል ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው እንዲያደምጡን ተጋብዘዋል።

https://soundcloud.com/user-953568/05-9-15a?si=7718bc5e6ba64c839c64967509bd9725&utm_source=clipboard&utm_medium=text&utm_campaign=social_sharing

ሁለተኛውን እና የመጨረሻውን ክፍል ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው እንዲያደምጡን ተጋብዘዋል። https://soundcloud.com/user-953568/07-9-15-2?si=b51f70ccd4ae4b8094f33360010c2a35&utm_source=clipboard&utm_medium=text&utm_campaign=social_sharing

– በዌብሳይት :- condoaddis.com/230517-3
– በፌስቡክ ፡- https://fb.me/etstocks

ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑን እናመሰግናለን
CFI presents good opportunity online courses for certification in capital market . Register and try your luck on the link below for the grant.
https://l1nq.com/dHOmw

CFI (ሲኤፍአይ) ለፈላጊዊች ጥሩ የሆነ ዕድል አቅርቧል። ይኸውም በመዋለ ንዋይ( Capital) ገበያ ላይ ዕውቅና የሚያስገኝ በይነ መረብ ስልጠና ስለተዘጋጅ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ ተመዝግበው ዕድሎትን ይሞክሩ።
https://l1nq.com/dHOmw
Forwarded from Financial _ Ethiopia (Hailu Mekonnen)
👉Crowdfunding...

የኢትዮጵያ የመዋእለ-ነዋይ ገበያ /Ethiopian Capital Market Authority/ የመዋእለ-ነዋይ ገበያው ሲጀመር ፈቃድ እንደሚሰጣቸው ከዘረዘራቸው የገበያ ተዋናዮች መ ካከል Crowd funding አንዱ ነው።

ለመሆኑ rowdfunding ምንድነው?

Equity Crowdfunding አዲስ ወደ ንግድ ለሚገቡ /Startups/ አሊያም ለጀማሪ ኩባንያዎች የካፒታል ማሰባሰቢያ ዘዴ ነው።

Crowd የሚለው ቃል "ብዝሐ" በሚለው የሚወከል ሲሆን ለብዙሀኑ በትንሽ ገንዘብ አክሲዮን በመሸጥ ካፒታል የሚሰበሰብበት ዘዴ ነው። እያንዳንዱ ኢንቨስተር ባዋጣው ገንዘብ እኩሌታ አክሲዮን ይሰጠዋል፣ የትርፍ ድርሻ ተካፋይም ይሆናል።

ከEquity Crowdfunding ሌላ ግለሰቦችን ለመርዳት እንዲሁም ለመሸለም የሚደረጉ የCrowdfunding ዓይነቶችም አሉ። (ለምሳሌ Gofundme)

ይህ ገንዘብ ትንንሽ ብሮችን ኢንቨስት ከሚያደርገው ብዙሀን የሚሰበሰበው በቴክኖሎጂ በታጀበ የኦንላይን ስርዓት ሲሆን እያንዳንዱ ሰው በገዛው አክሲዮን ልክ ወዲያውኑ ኢ-ሰርተፊኬት ያገኛል። ድርሻውን መሸጥ ሲፈልግም በቀላሉ በኦንላይን ሽጦ መውጣት ይችላል።
--------
Tilahun G.
New capital market rule to curb misleading claims in share sale

Ethiopian Capital Market Authority (ECMA) is expediting steps to regulate initial public offerings (IPOs) through a new directive aimed at curbing overpromising by companies seeking to sell shares to the public.

The move comes as the Authority prepares to launch the stock exchange next year and boost investor protection by preventing companies from making misleading claims about returns.

The directive is one of eight in the drafting stage and a top priority for the Authority, which is empowered to regulate larger share companies and is working to standardize the sale of shares by companies through strict procedures.

“We’re expediting the drafting process at a bullet speed just because of the issues we are recently seeing in the market,” said Brook Taye (PhD), the founding director-general of ECMA.

Recent instances of companies selling shares to the public with unclear prospectuses have prompted the Authority to quickly prepare and approve the directive.

Brook added that he has seen advertisements where companies claim to generate high returns.

“We see these every day,” he said, assuring that the Authority’s efforts will put an end to it soon.

“Currently, the law allows us to stop that but as a new institution, we have not yet designed the legal framework,” he explained. “To be clear, this will stop once we have the directive in place.”

Companies seeking to attract investment through share sales must follow procedures that include submitting a prospectus to the Authority in advance.




The prospectus must contain all relevant information about the company, its promoters, associated investment risks and potential for loss, according to Brook. The primary goal is to provide investors with the information needed to make informed decisions before investing in a company.

Failure to fulfill these requirements grants the Authority the power to stop and could constitute a criminal offense, according to Brook. The companies will also be required to submit advertising materials to the Authority for approval before soliciting public investments.

In light of recent incidents in which the public bought shares based on exaggerated claims, the director general hopes the public will not fall for such tactics until the directive is in place to regulate share sales.

Although the specific threshold has not been set yet, gatherings of up to 50 people may not have to comply with procedures to sell shares, which are considered private placements under the capital market proclamation.

Brook stressed that the Authority does not evaluate whether the investment offers a lucrative opportunity, but rather ensures the prospectus contains sufficient information for investors to make their own assessment.

Reporter

More👉 condoaddis.com/etstocks-230612
የአክሲዮን ሽያጭ ወይንም ተያያዥ ማስታወቂያዎች ለማድረግ ሲታሰብ በቅድሚያ ከባለስልጣኑ መስሪያ ቤት ህጋዊ ፈቃድ ማግኘት አስገዳጅ መሆኑ ተገለፀ።

ከዚህ ጋር በተያያዘም የአክሲዮን ገዢዎች ግዢ ከማካሄዳቸው በፊት የሚገዙት አክሲዮን ከባለስልጣኑ እና ከንግድ ሚንስትር የአክሲዮን ሽያጭ ፈቃድ ያለው መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባ አሳውቀዋል።
condoaddis.com/etstocks-230634
አዲስ አክሲዮን በመግዛት እና ነባር አክሲዮን በመግዛት መካከል ያለው ልዩነት፤ እድል እና ስጋት! አክሲዮኖችን መግዛት ኢንቨስትመንት መሆን የሚችለው የተጠና እና ምክንያታዊ ሲሆን ነው። የአክሲዮን ትርፋማነት እንዴት ይለካል?


ስለዚህ አዲስ የሚመሰረት አክሲዮን ለመግዛት እና ስራ ከጀመሩ ተቋማት ነባር አክሲዮን ለመግዛት ከመወሰን በፊት ከግምት መከተት ያለባቸው ጠቃሚ ሃሳቦችን https://youtu.be/x0niSsaddBc  ይመልከቱ።
ET Securities pinned «አዲስ አክሲዮን በመግዛት እና ነባር አክሲዮን በመግዛት መካከል ያለው ልዩነት፤ እድል እና ስጋት! አክሲዮኖችን መግዛት ኢንቨስትመንት መሆን የሚችለው የተጠና እና ምክንያታዊ ሲሆን ነው። የአክሲዮን ትርፋማነት እንዴት ይለካል? ስለዚህ አዲስ የሚመሰረት አክሲዮን ለመግዛት እና ስራ ከጀመሩ ተቋማት ነባር አክሲዮን ለመግዛት ከመወሰን በፊት ከግምት መከተት ያለባቸው ጠቃሚ ሃሳቦችን https://youtu.be/x0niSsaddBc …»
የካፒታል ገበያ ጥቅም ምንድነው? በዶ/ር እዮብ ታዬ ሲብራራ 👇👇 https://fb.watch/mrwpg-psOq/
በዋስትና ልውውጥ (securities exchanges) ላይ ኩባንያን ለመዘርዘር የተለያዩ መንገዶች አሉ። ይህ በኩባንያው ስትራቴጂ እና ፍላጎቶች ላይ ይወሰናል። ለኢትዮጵያ ኩባንያዎች ሊገኙ የሚችሉ አንዳንድ የዝርዝር አቀራረቦች እዚህ አሉ።
1. ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕዝብ መቅረብ (Initial Public Offer)
ማለት አንድ ኩባንያ አዲስ አክሲዮኖችን ለሽያጭ ሲያወጣ እንዲሁም በተመረጡ የዋስትና ልውውጦች(securities exchanges) ላይ አዳዲስ አክሲዮኖችን የሚያወጣ ኩባንያን ያካትታል።
ይህም በተቀመጠ የአክሲዮን መግዣ ዋጋ መሠረት አክሲዮኖችን የሚገዙ ተጨማሪ አዲስ የባለአክሲዮኖች ስብስብ ያስከትላል፣ ስለሆነም ኩባንያው መዋዕለ-ንዋይን ከፍ ያደርገዋል።
2. ተሻጋሪ ዝርዝሮች(cross-listing)
የምንለው በአንድ ዋስትና ልውውጥ ገበያ ዝርዝር ላይ የቀረበ ኩባንያ ወደ ሌላ ዋስትና ልውውጥ ገበያ ዝርዝሮች ላይ በመቅረብ ትልቅ የመዋዕለ-ንዋይ(capital) ከተለያዩ እርከኖች እና ከተለያዩ ባለሐብቶች ለማግኘት ሲወስን ነው።
3. ዝርዝሮች ላይ በማስገባት(listing by introduction)
የሚከሰተው አንድ ኩባንያ ያሉትን የአዲስ አክሲዮኖችን በልውውጥ ገበያ ላይ ሲያቀርብ ነው። ዝርዝሮች ላይ ማስገባት የምንለው በኩባንያው የሚቀርቡት አክሲዮኖች ሙሉ ለሙሉ የተከፈሉ እንደመሆኑ ዓላማ ያደረገው መዋዕለ-ንዋይ ወድያውኑ ለማግኘት ሳይሆን ኩባንያው ወደፊት ሲያስፈልገው የሚጠቀምበት ይሆናል። ለኩባንያዎች አክሲዮኖችን ለማሻሻጥ እንዲሁም ዋጋዎችን ለማወቅ የሚረዳ መድረክን ይፈጥራል።
4. የተገላቢጦሽ ዝርዝሮች (Reverse listing)
ይህ ብርቅ የሆነ ዝርዝር ማቅረቢያ ስትራቴጂ ሲሆን ይህም አንድ ኩባንያ በልውውጥ ገበያው ዝርዝር ላይ ያልቀረበ ሆኖ እያለ ነገር ግን በዝርዝሩ ላይ የቀረበን ኩባንያ ሲገዛና በዚህም ግብይት ምክንያት የዝርዝሩ አባል ሲሆን ነው።

ለተጨማሪ 👇👇
www.condoaddis.com/etstocks-230820-1