Afar Mass Media Agency (AFMMA)
1.09K subscribers
3.65K photos
161 videos
2 files
655 links
This channel is an official channel of Afar Mass Media Agency (AFMMA).
AFMMA is an autonomous government organization accountable to the regional Council of the Afar region.
Download Telegram
#ከሰሜን ዕዝ ከተለያዩ ብርጌዶችና ክፍለ ጦሮች በጁንታው ኃይል ታግተው የነበሩ 1240 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወደ ዋግኸምራ ዞን ሠቆጣ ከተማ ገብተዋል።

አፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት- ህዳር 23/2013

ከሰሜን ዕዝ ከተለያዩ ብርጌዶችና ክፍለ ጦሮች በጁንታው ኃይል ታግተው የነበሩ 1240 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወደ ዋግኸምራ ዞን ሠቆጣ ከተማ ገብተዋል።

የሠራዊት አባላቱ ከህዳር 20፣2013 ዓ.ም ከ 8 ሰዓት ጀምሮ እስከ እስከ ትላንት ማታ 12 ሰዓት ድረስ ነው ወደ ሰቆጣ የገቡት።

የመከላከያ ሰራዊት አባላቱ ሰቆጣ ለመግባት በርካታ ውጣ ውረድ ማለፋቸውንም ገልጸዋል።

በተለይም የተከዜን ኮሪደር ተከትለው በቀን እና ሌሊት የእግር ጉዞ እንዲሁም ወንዝና ጫካ እያቆራረጡ ሰቆጣ መግባታቸውን የሠራዊቱ አባላት መናገራቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።

የአካባቢው አስተዳደር ለሰራዊቱ የምግብ እና የህክምና አቅርቦት ማመቻቸቱም ተመልክቷል።

#OBN