Afar Mass Media Agency (AFMMA)
1.09K subscribers
3.65K photos
161 videos
2 files
655 links
This channel is an official channel of Afar Mass Media Agency (AFMMA).
AFMMA is an autonomous government organization accountable to the regional Council of the Afar region.
Download Telegram
#ለ6ኛው አገራዊ ምርጫ ከታህሳስ እስከ ጥር ባሉት ጊዜያት የመራጮች ምዝገባ እንደሚካሄድ ተገለጸ

Afar Mass Media-ጥቅምት 20, 2013

ለ6ኛው አገራዊ ምርጫ ከታህሳስ እስከ ጥር ባሉት ጊዜያት የመራጮች ምዝገባ እንደሚካሄድ ተገለጸ

ለ6ኛው አገራዊ ምርጫ ከታህሳስ እስከ ጥር ባሉት ጊዜያት የመራጮች ምዝገባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

ቦርዱ ለ6ኛው አገራዊ ምርጫ በሚከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ከሲቪክ እና ከመገናኛ ብዙሃን አባላት ጋር እየመከረ ነው።

በምክክር መድረኩ መክፈቻ ላይ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ እንደተናገሩት ከታህሳስ እስከ ጥር ወር 2013 ዓ.ም ለ6ኛው አገራዊ ምርጫ የመራጮች መዝግባ ይካሄዳል።

"ከጥር የመጀመሪያው ሳምንት እስከ የካቲት አጋማሽ ደግሞ የእጩዎች ምዝገባ እንዲሁም ከየካቲት አጋማሽ ጀምሮ የምረጡኝ ቅሰቀሳ ይጀመራል" ሲሉም ተናግረዋል።

በምክክር መድረኩ ላይ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ እና በምርጫ ሂደት ስለሚወሰዱ የኮቪድ-19 የጥንቃቄ እርምጃዎችን በተመለከተ ከሲቪክ ማህበራት እና ከመገናኛ ብዙሃን አባላት ጋር በመወያየት ግብዓት ይወሰዳል ተብሏል።

በተጨማሪም ሲቪክ ማህበራት አና መገናኛ ብዙሃንን የሚመለከቱ ዋና ዋና የምርጫ እንቅስቃሴዎች እና ዝግጅቶች ላይ ውይይት እንደሚደረግም ነው የተገለጸው።

እንደ ወይዘሪት ብርቱካን ገለጻ፣ መድረኩ የተዘጋጀው የሲቪክ ማህበራት እና የመገናኛ ብዙሃን የሚያነሷቸውን ሀሳቦች በመጨረሻ ለሚወጣው የምርጫ ጊዜ ሰለዳ እና የአፈጻጸም ዕቅድ ላይ በግብዓትነት ለመጠቀም ታስቦ ነው።

በመድረኩ በምርጫ ሂደት የሚተገበሩ የኮቪድ-19 የጥንቃቄ መመሪያ መነሻ ሀሳቦች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል።

በተጨማሪም ዋና ዋና የምርጫ ተግባራት በሚተገበሩበት ጊዜ የሲቪክ ማህበራት እና የመገናኛ ብዙሃን ያላቸውን ሚና የተመለከቱና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ውይይት ያደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

#ENA