#የደሴ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት የሞተር እና ባለ3 እግር ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ እንዲቆም መወሰኑ ተሰማ።
ሰመራ-ጥቅምት 14/2014 (አፍ.ብ.መ.ድ)
የደሴ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት የሞተር እና ባለ3 እግር ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ እንዲቆም መወሰኑ ተሰማ።
ከዛሬ ጀምሮ የሚተገበረው ውሳኔ እስኪነሳ ወይም እስኪሻሻል ሞተር ሳይክሎች እና ባለ3 እግር ተሽከርካሪዎች በየትኛውም ሰዓት ከተማዋ ላይ መንቀሳቀስ አይችሉም።
ውሳኔው የተላለፈው የደሴ ከተማን ፀጥታና ደኅንነት ለማስጠበቅና የአሸባሪውን ሕወሓት ሰርጎ ገቦች ለመቆጣጠር እንዲቻል በሚል መሆኑን የደሴ ከተማ አስተዳደር ለዋልታ ገልጿል።
ንግድ ቤቶች በተለይም መድኃኒት ቤቶች በአስቸኳይ ተከፍተው አገልግሎት መስጠት እንዲጀምሩ የፀጥታ ምክር ቤቱ ትዕዛዝ አስተላልፏል።
ውሳኔውን በማያከብሩ ላይ ጠንካራ እርምጃ እንደሚወስድም ምክር ቤቱ አስጠንቅቋል።
#Walta
ሰመራ-ጥቅምት 14/2014 (አፍ.ብ.መ.ድ)
የደሴ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት የሞተር እና ባለ3 እግር ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ እንዲቆም መወሰኑ ተሰማ።
ከዛሬ ጀምሮ የሚተገበረው ውሳኔ እስኪነሳ ወይም እስኪሻሻል ሞተር ሳይክሎች እና ባለ3 እግር ተሽከርካሪዎች በየትኛውም ሰዓት ከተማዋ ላይ መንቀሳቀስ አይችሉም።
ውሳኔው የተላለፈው የደሴ ከተማን ፀጥታና ደኅንነት ለማስጠበቅና የአሸባሪውን ሕወሓት ሰርጎ ገቦች ለመቆጣጠር እንዲቻል በሚል መሆኑን የደሴ ከተማ አስተዳደር ለዋልታ ገልጿል።
ንግድ ቤቶች በተለይም መድኃኒት ቤቶች በአስቸኳይ ተከፍተው አገልግሎት መስጠት እንዲጀምሩ የፀጥታ ምክር ቤቱ ትዕዛዝ አስተላልፏል።
ውሳኔውን በማያከብሩ ላይ ጠንካራ እርምጃ እንደሚወስድም ምክር ቤቱ አስጠንቅቋል።
#Walta