General Wingate Polytechnic college-Official channel
9.95K subscribers
3.35K photos
43 videos
204 files
196 links
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን።

የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።
Download Telegram
ሐሙስ፡- ህዳር 26 ቀን 2017 ዓ.ም

#የብሔር_ብሔረሰቦች_ቀን_በኮሌጁ_ተከበረ!!

19ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ሀገራዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት በሚል መሪ ቃል በኮሌጁ ተከበረ

የኮሌጁ ሰራተኞች እና ሰልጣኞች በተገኙበት 19ኛው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዛሬው ዕለት በኮሌጁ በድምቀት የተከበረ ሲሆን በመድረኩ ላይ ልዩ ልዩ አዝናኝ እና አስተማሪ ይዘት ያላቸው ዝግጅቶች ቀርበዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ስለሕብረ ብሔራዊ ሥርዓታችንና እያጋጠሙት ስላሉት ተግዳሮቶች እንዲሁም የመፍትሔ ሀሳቦች የተካተቱበት ሰነድ የቀረበ ሲሆን ዓላማውም አገራዊ መግባባትን በመፍጠር ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር ታቅዶ መሆኑን ሰምተናል።

ከዚህ ባሻገር ስነ ጽሑፍና ሙዚቃ በሰልጣኞች እንዲሁም የሰርከስ ትርኢት በሰርከስ ዊንጌት አባላት ቀርቧል።

የበዓሉ ዝግጅት በድምቀት እንዲከበር በማድረግ ረገድ የኮሌጁ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት እና የሰልጣኞች መማክርት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ።  

"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"