አርብ፡- ህዳር 13 ቀን 2017 ዓ.ም
ኮሌጁ ከአዲስ ሚዲያ ኔትወር /AMN/ ጋር በትብብር ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ /AMN/ በትብብር ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል።
የሚዲያው የስራ ኃላፊዎች ዛሬ ህዳር 13 ቀን 2017 ዓ.ም በኮሌጁ ተገኝተው ተቋማዊ ጉብኝት እና የስራ ውይይት ካደረጉ በኋላ በቀጣይ አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት መፈራረም ችለዋል፡፡
ኮሌጁ ከተለያዩ ሚዲዎች ጋር አብሮ ሲሰራ ቢቆይም ከሚዲያ አንፃር የስምምነት ሰነድ ተፈራርሞ በጋራ ለመስራት በዚህ መልኩ ስምምነት ሲያደርግ ይህ የመጀመሪያ ነው ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ #መለስ ይግዛው ናቸው። ዲን አክለውም ከበርካታ አገር አቀፍና ዓለም ተቋማት ጋር በጋራ እየሰራ ያለ ሲሆን አገልግሎቶቻችን ተደራሽ ለማድረግ ከእናንተና መሰል መገናኛ ብዙሃን ጋር ተባብረን መስራት ግድ ይለናል ብለዋል።
በሌላ በኩል የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ የገበያ ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ #መሀመድ ናስር በበኩላቸው ስምምነቱ የብዙሃን ድምጽ የሆነው አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በስሩ ለሚገኙ ባለሙያዎች የቴክኒክ እና ሙያ ድጋፍ እንዲያገኙ ያስችለዋል ብለዋል።
ሚዲያ አንጋፋ በሆነው በዚህ ኮሌጅ የሚከናወኑ የልማትና የፈጠራ ስራዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በዜናና በዶክመንተሪ ሽፋን ለመስጠት ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ኮሌጁ ከአዲስ ሚዲያ ኔትወር /AMN/ ጋር በትብብር ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ /AMN/ በትብብር ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል።
የሚዲያው የስራ ኃላፊዎች ዛሬ ህዳር 13 ቀን 2017 ዓ.ም በኮሌጁ ተገኝተው ተቋማዊ ጉብኝት እና የስራ ውይይት ካደረጉ በኋላ በቀጣይ አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት መፈራረም ችለዋል፡፡
ኮሌጁ ከተለያዩ ሚዲዎች ጋር አብሮ ሲሰራ ቢቆይም ከሚዲያ አንፃር የስምምነት ሰነድ ተፈራርሞ በጋራ ለመስራት በዚህ መልኩ ስምምነት ሲያደርግ ይህ የመጀመሪያ ነው ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ #መለስ ይግዛው ናቸው። ዲን አክለውም ከበርካታ አገር አቀፍና ዓለም ተቋማት ጋር በጋራ እየሰራ ያለ ሲሆን አገልግሎቶቻችን ተደራሽ ለማድረግ ከእናንተና መሰል መገናኛ ብዙሃን ጋር ተባብረን መስራት ግድ ይለናል ብለዋል።
በሌላ በኩል የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ የገበያ ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ #መሀመድ ናስር በበኩላቸው ስምምነቱ የብዙሃን ድምጽ የሆነው አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በስሩ ለሚገኙ ባለሙያዎች የቴክኒክ እና ሙያ ድጋፍ እንዲያገኙ ያስችለዋል ብለዋል።
ሚዲያ አንጋፋ በሆነው በዚህ ኮሌጅ የሚከናወኑ የልማትና የፈጠራ ስራዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በዜናና በዶክመንተሪ ሽፋን ለመስጠት ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"