አርብ:- ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም
የዳግማዊ ምኒልክ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሴት ተማሪዎች በኮሌጁ የሚሰጠውን የሙያ ስልጠና ጎበኙ!!
የዘመናዊ ትምህርት ችቦ የተለኮሰበት ተቋም ነው በሚባለው ዳግማዊ ምኒልክ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እየተማሩ የሚገኙ ሴት ተማሪዎች በኮሌጁ እየተሰጠ ያለውን የሙያ ስልጠና በዛሬው ዕለት ምልከታ አድርገዋል።
ጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የ9ኛ እና የ10 ክፍል እንዲሁም ከ11ኛ እና ከ12ኛ ክፍል ደግሞ የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ የተውጣጡ ሴት ተማሪዎች እንደሆነ ተነግሯል።
ስለኮሌጁ ታሪካዊ ዳራና እየተሰጡ ስላሉ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶች በኮሌጅ ባለሙያዎች ገለፃ ተደርጎላቸው የኮሌጁን አጠቃላይ ስነ ምህዳርና የማሰልጠኛ ወርክሾፖችን እንዲጎበኙ ተደርጓል።
በዕለቱ 150 የሚሆኑ ሴት ተማሪዎች ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የሀሁ ጆብስ ዲጂታል ጆብ ማቺንግ ድርጅት አካል የሆነውና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ 4 የመንግስት 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለሚማሩ ሴት ተማሪዎች የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የምህንድስና እና የሒሳብ ትምህርቶች ላይ አቅም ለማሳደግ እየሰራ የሚገኘው ስቴም ኢዱኬሽን ፎር ኢምፓወርመንት ፕሮጀክት ከኮሌጁ ስራ ትስስር እና ምክር አገልግሎት የስራ ክፍል ጋር በመተባበር ነው።
የጉብኝቱ መሠረታዊ ዓላማ ሴት ተማሪዎች በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማጎልበትና ለቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎች አጠቃላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማድረግ ነው ተብሏል።
ፕሮጀክቱ ዳግማዊ ምኒልክ 2ኛ ደረጃን ጨምሮ ደጃዝማች ወንድራድ፣ ኮከበ ፅባህ እና ተስፋ ብርሃን 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ እየሰራ ሲሆን ከዚህ በፊት የደ/ ወንድራድ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሴት ተማሪዎችም በተመሳሳይ ጉብኝት አድርገዋል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የዳግማዊ ምኒልክ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሴት ተማሪዎች በኮሌጁ የሚሰጠውን የሙያ ስልጠና ጎበኙ!!
የዘመናዊ ትምህርት ችቦ የተለኮሰበት ተቋም ነው በሚባለው ዳግማዊ ምኒልክ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እየተማሩ የሚገኙ ሴት ተማሪዎች በኮሌጁ እየተሰጠ ያለውን የሙያ ስልጠና በዛሬው ዕለት ምልከታ አድርገዋል።
ጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የ9ኛ እና የ10 ክፍል እንዲሁም ከ11ኛ እና ከ12ኛ ክፍል ደግሞ የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ የተውጣጡ ሴት ተማሪዎች እንደሆነ ተነግሯል።
ስለኮሌጁ ታሪካዊ ዳራና እየተሰጡ ስላሉ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶች በኮሌጅ ባለሙያዎች ገለፃ ተደርጎላቸው የኮሌጁን አጠቃላይ ስነ ምህዳርና የማሰልጠኛ ወርክሾፖችን እንዲጎበኙ ተደርጓል።
በዕለቱ 150 የሚሆኑ ሴት ተማሪዎች ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የሀሁ ጆብስ ዲጂታል ጆብ ማቺንግ ድርጅት አካል የሆነውና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ 4 የመንግስት 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለሚማሩ ሴት ተማሪዎች የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የምህንድስና እና የሒሳብ ትምህርቶች ላይ አቅም ለማሳደግ እየሰራ የሚገኘው ስቴም ኢዱኬሽን ፎር ኢምፓወርመንት ፕሮጀክት ከኮሌጁ ስራ ትስስር እና ምክር አገልግሎት የስራ ክፍል ጋር በመተባበር ነው።
የጉብኝቱ መሠረታዊ ዓላማ ሴት ተማሪዎች በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማጎልበትና ለቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎች አጠቃላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማድረግ ነው ተብሏል።
ፕሮጀክቱ ዳግማዊ ምኒልክ 2ኛ ደረጃን ጨምሮ ደጃዝማች ወንድራድ፣ ኮከበ ፅባህ እና ተስፋ ብርሃን 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ እየሰራ ሲሆን ከዚህ በፊት የደ/ ወንድራድ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሴት ተማሪዎችም በተመሳሳይ ጉብኝት አድርገዋል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
እሁድ:- ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ለውጦችና በተፈጠሩ ተግዳሮቶች ዙሪያ ወይይት ተካሄደ!!
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ዘርፈ ብዙ ለውጦችና በተከሰቱ ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከኮሌጁ አሰልጣኞች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
"የበቃ አሰልጣኝ ክህሎት የጨበጠ ወጣት ለሀገር ብልፅግና!" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለውን ውይይት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ #ጥራቱ #በየነ ከማዕከል በገለፃ አቅረበዋል።
ክቡር አቶ ጥራቱ በገለፃቸው እንደ ሀገር የመጡ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የወጪ ግንኙነት ፖሊሲና ዲፕሎማሲ ስኬቶችን እንዲሁም ሀገራዊ ለውጡን የፈተኑ ውስጣዊና ወጫዊ ተግዳሮቶችን አብራርተዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ብቁ ባለሙያ በማፍራትና የቴክኖሎጂ ሽግግር በማድረግ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ለሀገራዊ ብልፅግና ያላቸው ሚና ትልቅ መሆኑን አውስተዋል፡፡ በገለፃው የመዲናቱ ኮሌጆች ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ በጥንካሬና በክፍተት ማሳየት ተችሏል፡፡
በቀረበው ገለፃ መሰረት ከኮሌጁ አሰልጣኞች የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች እየተነሱ ሲሆን የውይይት መድረኩን በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ #አቶ #መሀመድ #ልጋኒ እና የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ #መለሰ #ይግዛው እየመሩት ይገኛሉ፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ለውጦችና በተፈጠሩ ተግዳሮቶች ዙሪያ ወይይት ተካሄደ!!
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ዘርፈ ብዙ ለውጦችና በተከሰቱ ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከኮሌጁ አሰልጣኞች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
"የበቃ አሰልጣኝ ክህሎት የጨበጠ ወጣት ለሀገር ብልፅግና!" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለውን ውይይት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ #ጥራቱ #በየነ ከማዕከል በገለፃ አቅረበዋል።
ክቡር አቶ ጥራቱ በገለፃቸው እንደ ሀገር የመጡ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የወጪ ግንኙነት ፖሊሲና ዲፕሎማሲ ስኬቶችን እንዲሁም ሀገራዊ ለውጡን የፈተኑ ውስጣዊና ወጫዊ ተግዳሮቶችን አብራርተዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ብቁ ባለሙያ በማፍራትና የቴክኖሎጂ ሽግግር በማድረግ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ለሀገራዊ ብልፅግና ያላቸው ሚና ትልቅ መሆኑን አውስተዋል፡፡ በገለፃው የመዲናቱ ኮሌጆች ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ በጥንካሬና በክፍተት ማሳየት ተችሏል፡፡
በቀረበው ገለፃ መሰረት ከኮሌጁ አሰልጣኞች የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች እየተነሱ ሲሆን የውይይት መድረኩን በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ #አቶ #መሀመድ #ልጋኒ እና የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ #መለሰ #ይግዛው እየመሩት ይገኛሉ፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ረቡዕ:- ግንቦት 13 ቀን 2017 ዓ.ም
ለአሰልጣኞችና ለኢንዱስትሪ ባለሙያዎች የሶላር ስልጠና ተሰጠ!!
ለኮሌጁ ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክ አሰልጣኞችና ከኢንዱስትሪዎች ለተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች የሶላር ክህሎት አቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኔዘርላንድ ከሚገኝ እና የሶላር ክህሎት ስልጠናን በበጎ ፈቃደኝነት ከሚሰጠው PUM ከሚባለው ድርጅት ጋር በመተባበር ለ8 የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች እና ለ11 የኮሌጁ አሰልጣኞች በዛሬው ዕለት ተግባራዊ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።
የፅንሰ ሀሳብ ትምህርቱ ከዚህ በፊት በበየነ መረብ በሳምንት 3 ጊዜ ለ24 የቀናት የተሰጠ ሲሆን የተግባር ስልጠናው ደግሞ በአካል ዛሬ ተጀምሮ ለ7 ቀን ይሰጣል።
የስልጠናው ዓላማ የግሪን ኢኮኖሚ አካል የሆነውን ታዳሽ ኃይል ለመጠቀም የሚያስችል ክህሎትን ለማዳበር ሲሆን ይዘቱም የሶላር ኃይልን በመጠቀም የቤት ውስጥ መብራት ፍጆታ፣ የመንገድ ዳር ብርሃን ዝርጋታና የከርሰምድር ውሃ ጉልበታ ለመከወን የሚያስችልበት አቅም ለማሳደግ ነው ተብሏል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ለአሰልጣኞችና ለኢንዱስትሪ ባለሙያዎች የሶላር ስልጠና ተሰጠ!!
ለኮሌጁ ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክ አሰልጣኞችና ከኢንዱስትሪዎች ለተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች የሶላር ክህሎት አቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኔዘርላንድ ከሚገኝ እና የሶላር ክህሎት ስልጠናን በበጎ ፈቃደኝነት ከሚሰጠው PUM ከሚባለው ድርጅት ጋር በመተባበር ለ8 የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች እና ለ11 የኮሌጁ አሰልጣኞች በዛሬው ዕለት ተግባራዊ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።
የፅንሰ ሀሳብ ትምህርቱ ከዚህ በፊት በበየነ መረብ በሳምንት 3 ጊዜ ለ24 የቀናት የተሰጠ ሲሆን የተግባር ስልጠናው ደግሞ በአካል ዛሬ ተጀምሮ ለ7 ቀን ይሰጣል።
የስልጠናው ዓላማ የግሪን ኢኮኖሚ አካል የሆነውን ታዳሽ ኃይል ለመጠቀም የሚያስችል ክህሎትን ለማዳበር ሲሆን ይዘቱም የሶላር ኃይልን በመጠቀም የቤት ውስጥ መብራት ፍጆታ፣ የመንገድ ዳር ብርሃን ዝርጋታና የከርሰምድር ውሃ ጉልበታ ለመከወን የሚያስችልበት አቅም ለማሳደግ ነው ተብሏል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
አርብ:- ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም
የኮሌጁ ሜታል ማኑፋክቸሪንግ ዲፓርትመንት የዶሮ ኬጂዎችን እያመረተ ነው!!
የኮሌጁ ሜታል ማኑፋክቸሪንግ ዲፓርትመንት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ስር ለሚገኙ ወረዳዎች አገልግሎት የሚውል የዶሮ ኬጂዎችን በማምረት ላይ ይገኛል፡፡
ዲፓርትመንቱ እያንዳንዳቸው 50 ዶሮዎችን የሚይዙ 48 ኬጂዎች እና 100 ዶሮዎችን ማስተናገድ የሚችሉ 24 የዶሮ ኪጂዎችን በጥራት አምርቶ ለማስረከብ እየተጋ ነው፡፡
እየተሰሩ ያሉ ኬጂዎች ለእንቅላል ጣይ ዶሮዎች መኖሪያ አገልግሎት እንደሚውሉ የተገለጸ ሲሆን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ስር የሚገኙ የወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤቶች የከተማ ግብርና ውጤት በሆኑት የሌማት ትሩፋት ስራዎች ላይ አጠናክረው እንዲሰሩ ያግዛል መባሉን ሰምተናል፡፡
ዲፓርትመንቱ ከዚህ በፊት ለከተማይቱ ኮሪደር ልማት አገልግሎት የሚውሉ የኮንቲነር ሱቆችን ጨምሮ የተለያዩ የብረታ ብረት ምርት ውጤቶችን በጥራትና በፍጥነት ሰርቶ አስረክቧል፡፡
የስልጠና ዘርፉ በኮሌጁ በአካባቢያዊ የመልማት ፀጋ ልየታም ከተመሩጡ 5 ዲፓርትመንቶች መካከል አንዱ መሆኑ አይዘነጋም፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የኮሌጁ ሜታል ማኑፋክቸሪንግ ዲፓርትመንት የዶሮ ኬጂዎችን እያመረተ ነው!!
የኮሌጁ ሜታል ማኑፋክቸሪንግ ዲፓርትመንት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ስር ለሚገኙ ወረዳዎች አገልግሎት የሚውል የዶሮ ኬጂዎችን በማምረት ላይ ይገኛል፡፡
ዲፓርትመንቱ እያንዳንዳቸው 50 ዶሮዎችን የሚይዙ 48 ኬጂዎች እና 100 ዶሮዎችን ማስተናገድ የሚችሉ 24 የዶሮ ኪጂዎችን በጥራት አምርቶ ለማስረከብ እየተጋ ነው፡፡
እየተሰሩ ያሉ ኬጂዎች ለእንቅላል ጣይ ዶሮዎች መኖሪያ አገልግሎት እንደሚውሉ የተገለጸ ሲሆን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ስር የሚገኙ የወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤቶች የከተማ ግብርና ውጤት በሆኑት የሌማት ትሩፋት ስራዎች ላይ አጠናክረው እንዲሰሩ ያግዛል መባሉን ሰምተናል፡፡
ዲፓርትመንቱ ከዚህ በፊት ለከተማይቱ ኮሪደር ልማት አገልግሎት የሚውሉ የኮንቲነር ሱቆችን ጨምሮ የተለያዩ የብረታ ብረት ምርት ውጤቶችን በጥራትና በፍጥነት ሰርቶ አስረክቧል፡፡
የስልጠና ዘርፉ በኮሌጁ በአካባቢያዊ የመልማት ፀጋ ልየታም ከተመሩጡ 5 ዲፓርትመንቶች መካከል አንዱ መሆኑ አይዘነጋም፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››