ማክሰኞ፡- መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ.ም
ማርች 8 የሴቶች ቀን በኮሌጁ ተከበረ!!
በኢትዮጵያ ለ49ኛ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ114 ጊዜ የሚከበር ማርች 8 የሴቶች ቀን የኮሌጁ ሰራተኞችና ሰልጣኞች በተገኙበት ተከበረ፡፡
ማርች 8 እንደ ጎርጎሮሳዊያን የዘመን ቀመር 1908 ላይ ኗሪነታቸው በአሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ የሆኑና በተለይ ደግሞ በጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎች ሰራተኞች የነበሩ 15,000 ሴቶች በአደባባይ ወጥተው የሥራ ሰዓት እንዲሻሻል /እንዲያጥር/፣ የደመወዝ ክፍያ እኩልነት እንዲፈጠር እና የመምረጥ መብታቸው እንዲከበር ለጥያቄ የወጡበት ታሪካዊ ቀን እንደሆነ ይነገራል፡፡
በ1975 ዓ.ም ደግሞ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሴቶች ቀንን ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ በይፋ እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
‹‹የሴቶች ቀን ሲከበር ለመድረክ ፍጆታ ብቻ ሳይሆን ሴቶች ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፏቸው እንዲያዲግ እንዲሁም ተጠቃሚነታቸውና አበርክቷችሁ የጎላ እንዲሆን መሆን አለበት፡፡ ይህንን ተነሳሽትና ትጋት እንደ ኮሌጅ ስንመለከት በተዘጋጀው ተቋማዊ የልማት ስራዎች ላይ ሴቶችም በእኔ እችላለው መንፈስ ተሳትፏችሁ የበለጠ ጎልቶ መታየት ይኖርበታል›› ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ናቸው፡፡
በሌላ በኩል ከፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት የመጡ የስርዓተ ፆታ ባለሙያዎች ስለ ማርች 8 ምንነትና በህይወት ክህሎት ላያ ያተኮረ ሙያዊ ገለፃ ሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም ለኮሌጃችን ሴት ሰራተኞች እና ሰልጣኞች ለማርች 8 እንኳን አደረሳችሁ እያልን መልካም የስኬት ጊዜ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ማርች 8 የሴቶች ቀን በኮሌጁ ተከበረ!!
በኢትዮጵያ ለ49ኛ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ114 ጊዜ የሚከበር ማርች 8 የሴቶች ቀን የኮሌጁ ሰራተኞችና ሰልጣኞች በተገኙበት ተከበረ፡፡
ማርች 8 እንደ ጎርጎሮሳዊያን የዘመን ቀመር 1908 ላይ ኗሪነታቸው በአሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ የሆኑና በተለይ ደግሞ በጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎች ሰራተኞች የነበሩ 15,000 ሴቶች በአደባባይ ወጥተው የሥራ ሰዓት እንዲሻሻል /እንዲያጥር/፣ የደመወዝ ክፍያ እኩልነት እንዲፈጠር እና የመምረጥ መብታቸው እንዲከበር ለጥያቄ የወጡበት ታሪካዊ ቀን እንደሆነ ይነገራል፡፡
በ1975 ዓ.ም ደግሞ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሴቶች ቀንን ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ በይፋ እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
‹‹የሴቶች ቀን ሲከበር ለመድረክ ፍጆታ ብቻ ሳይሆን ሴቶች ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፏቸው እንዲያዲግ እንዲሁም ተጠቃሚነታቸውና አበርክቷችሁ የጎላ እንዲሆን መሆን አለበት፡፡ ይህንን ተነሳሽትና ትጋት እንደ ኮሌጅ ስንመለከት በተዘጋጀው ተቋማዊ የልማት ስራዎች ላይ ሴቶችም በእኔ እችላለው መንፈስ ተሳትፏችሁ የበለጠ ጎልቶ መታየት ይኖርበታል›› ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ናቸው፡፡
በሌላ በኩል ከፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት የመጡ የስርዓተ ፆታ ባለሙያዎች ስለ ማርች 8 ምንነትና በህይወት ክህሎት ላያ ያተኮረ ሙያዊ ገለፃ ሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም ለኮሌጃችን ሴት ሰራተኞች እና ሰልጣኞች ለማርች 8 እንኳን አደረሳችሁ እያልን መልካም የስኬት ጊዜ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ማክሰኞ:- መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ.ም
የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኮሌጁ ጉብኝት አደረጉ!!
የአዲስ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች ዛሬ መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ.ም በኮሌጁ ትምህርታዊ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በዕለቱ ከ150 በላይ የሚሆኑ እና ከ11ኛ ክፍሎች የተውጣጡ ተማሪዎች ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን ተቋማዊ ስነ ምህዳር እና አጠቃላይ የስራ እንቅሰቃሴ ገለፃ ተሰጥቷቸው የልዩ ልዩ ዲፓርትመንቶችን ወርክሾፖች እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡
የጉብኝቱ መሰረታዊ ዓላማ ቀጣይ የ12 ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከወሰዱ በኋላ ወደ ቴክኒክና ሙያ ለሚቀላቀሉ ተማሪዎች ስለ ሙያ ስልጠና ከአሁኑ አዎንታዊ አመለካከት እንዲኖራቸው እና ለምርጫ እንዳይቸገሩ ለማድረግ ነው ተብሏል፡፡
ከዚህ ባሻገር አሁን ላይ እስከ ደረጃ 2 ያለውን የሙያ ስልጠና ከቀለም ትምህርት ጋር አቀናጅተው ስለሚማሩ ወርክሾፖችን በመጎብኘት መሰረታዊ መረጃ ለማሰጨበጥ ይረዳል መባሉንም ሰምተናል፡፡
ተማሪዎቹ በተሰጣቸው ማብራሪያ እና በጉብኝት ወቅቱ ባዩት የስራ እንቅስቃሴ በጣም እንደተደሰቱ ገልፀው የሙያ ትምህርት ለመማር ተነሳሽነት እንደፈጠረላቸው ምስክርነትን ሰጥተዋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኮሌጁ ጉብኝት አደረጉ!!
የአዲስ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች ዛሬ መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ.ም በኮሌጁ ትምህርታዊ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በዕለቱ ከ150 በላይ የሚሆኑ እና ከ11ኛ ክፍሎች የተውጣጡ ተማሪዎች ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን ተቋማዊ ስነ ምህዳር እና አጠቃላይ የስራ እንቅሰቃሴ ገለፃ ተሰጥቷቸው የልዩ ልዩ ዲፓርትመንቶችን ወርክሾፖች እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡
የጉብኝቱ መሰረታዊ ዓላማ ቀጣይ የ12 ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከወሰዱ በኋላ ወደ ቴክኒክና ሙያ ለሚቀላቀሉ ተማሪዎች ስለ ሙያ ስልጠና ከአሁኑ አዎንታዊ አመለካከት እንዲኖራቸው እና ለምርጫ እንዳይቸገሩ ለማድረግ ነው ተብሏል፡፡
ከዚህ ባሻገር አሁን ላይ እስከ ደረጃ 2 ያለውን የሙያ ስልጠና ከቀለም ትምህርት ጋር አቀናጅተው ስለሚማሩ ወርክሾፖችን በመጎብኘት መሰረታዊ መረጃ ለማሰጨበጥ ይረዳል መባሉንም ሰምተናል፡፡
ተማሪዎቹ በተሰጣቸው ማብራሪያ እና በጉብኝት ወቅቱ ባዩት የስራ እንቅስቃሴ በጣም እንደተደሰቱ ገልፀው የሙያ ትምህርት ለመማር ተነሳሽነት እንደፈጠረላቸው ምስክርነትን ሰጥተዋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
አርብ፡- መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም
በኮሌጁ የስራ አፈፃፀምና የሪፎርም ትግበራ ግምገማ ተካሄደ!!
ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት የኮሌጁ የ8 ወር ዕቅድ አፈፃፀም እና የስራና ክህሎት ቢሮ የሪፎርም ትግበራ ሂደት ቀርቦ ውይይት ተደረገበት፡፡
በውይይቱ ላይ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ አካማሪ አቶ ቸርነት በላቸው፣ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ም/ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ከበደ እና የኮሌጁ አመራሮች ተገኛተዋል፡፡
እንደ ኮሌጅ ከአዲሱ የቴክኒክና ሙያ እሳቤ አተገባበር ጋር በተያያዘ ያለውን አፈፃፀም ያቀረቡት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ሲሆኑ በተቋሙ ከ11 የቴክነክና ሙያ ዘረመሎች /DNA/ አንፃር የተከናወኑ አበየት ተግባራትን በየዘርፉ አቅርበዋል፡፡
በዚህም ተቋሙን ለሰራተኞችና ሰልጣኞች ምቹ ከማድረግ ረገድ፣ የኢንዱስትሪዎችን ገበያ ፍላጎት ያደረገ ስልጠና ከመስጠትና ከግሉ አልሚ ጋር በአጋርነት ከመስራት አንፃር፣ በአካባቢ ፀጋ ለይቶ ከማሰልጠንና ተቋማዊ ኢንተርፕራይዞችን ፈጥሮ የሀብት ማግኛ ከማድረግ አኳያና መሰል ሀሳቦች በአፈፃፀሙ ተገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የከተማ አስተዳደሩ ስራና ክህሎት ቢሮ የሰራቸውንና እያከናወናቸው ያሉትን የሪፎርም ትግበራ ያቀረቡት በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የቢሮ አካማሪ አቶ ቸርነት በላቸው ሲሆኑ አሰራሩን ማስተካከል፣ አመራሩን መልሶ ማደራጀት፣ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፣ የስራ አካባቢን ለአገልግሎት ምቹ ማድረግ፣ የዲሲፕሊን ክፍተቶች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ የሚሉት ሲተገበሩ በቀጣይ መረጃዎችን በቴክኖሎጂ አጠናክሮ መቀጠል፣ የተቋማት አካባቢያዊ ፀጋ ልየታን መተግበር፣ የኮሌጆችን ኢንተርፕራይዞች አጠናክሮ ማስቀጠል የሚሉት ተግባራት ይገኙበታል፡፡
በመድረኩ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎችም በቀረበው ተቋማዊ አፈፃፀምና ቢሮው እየተገበረው ባለው የሪፎርም ስራ ጠንካራ አቅሞች ናቸው ያሏቸውን አድንቀው፤ ማስተካከያ ቢደረግባቸው የሚሏቸውን ደግሞ ገንቢ አስተያየቶች አቅርበዋል፡፡ በመጨረሻም ከመድረኩ የማጠቃለያ ምላሾች ተሰጥተው ውይይቱ ተጠናቋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
በኮሌጁ የስራ አፈፃፀምና የሪፎርም ትግበራ ግምገማ ተካሄደ!!
ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት የኮሌጁ የ8 ወር ዕቅድ አፈፃፀም እና የስራና ክህሎት ቢሮ የሪፎርም ትግበራ ሂደት ቀርቦ ውይይት ተደረገበት፡፡
በውይይቱ ላይ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ አካማሪ አቶ ቸርነት በላቸው፣ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ም/ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ከበደ እና የኮሌጁ አመራሮች ተገኛተዋል፡፡
እንደ ኮሌጅ ከአዲሱ የቴክኒክና ሙያ እሳቤ አተገባበር ጋር በተያያዘ ያለውን አፈፃፀም ያቀረቡት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ሲሆኑ በተቋሙ ከ11 የቴክነክና ሙያ ዘረመሎች /DNA/ አንፃር የተከናወኑ አበየት ተግባራትን በየዘርፉ አቅርበዋል፡፡
በዚህም ተቋሙን ለሰራተኞችና ሰልጣኞች ምቹ ከማድረግ ረገድ፣ የኢንዱስትሪዎችን ገበያ ፍላጎት ያደረገ ስልጠና ከመስጠትና ከግሉ አልሚ ጋር በአጋርነት ከመስራት አንፃር፣ በአካባቢ ፀጋ ለይቶ ከማሰልጠንና ተቋማዊ ኢንተርፕራይዞችን ፈጥሮ የሀብት ማግኛ ከማድረግ አኳያና መሰል ሀሳቦች በአፈፃፀሙ ተገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የከተማ አስተዳደሩ ስራና ክህሎት ቢሮ የሰራቸውንና እያከናወናቸው ያሉትን የሪፎርም ትግበራ ያቀረቡት በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የቢሮ አካማሪ አቶ ቸርነት በላቸው ሲሆኑ አሰራሩን ማስተካከል፣ አመራሩን መልሶ ማደራጀት፣ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፣ የስራ አካባቢን ለአገልግሎት ምቹ ማድረግ፣ የዲሲፕሊን ክፍተቶች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ የሚሉት ሲተገበሩ በቀጣይ መረጃዎችን በቴክኖሎጂ አጠናክሮ መቀጠል፣ የተቋማት አካባቢያዊ ፀጋ ልየታን መተግበር፣ የኮሌጆችን ኢንተርፕራይዞች አጠናክሮ ማስቀጠል የሚሉት ተግባራት ይገኙበታል፡፡
በመድረኩ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎችም በቀረበው ተቋማዊ አፈፃፀምና ቢሮው እየተገበረው ባለው የሪፎርም ስራ ጠንካራ አቅሞች ናቸው ያሏቸውን አድንቀው፤ ማስተካከያ ቢደረግባቸው የሚሏቸውን ደግሞ ገንቢ አስተያየቶች አቅርበዋል፡፡ በመጨረሻም ከመድረኩ የማጠቃለያ ምላሾች ተሰጥተው ውይይቱ ተጠናቋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ረቡዕ:- መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም
የመስከረም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኮሌጁ የሚሰጠውን የሙያ ስልጠና ምልከታ አደረጉ!!
በአራዳ ክፍለ ከተማ የሚገኘው መስከረም የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ዛሬ መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም በኮሌጁ ትምህርታዊ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በዕለቱ 135 የሚሆኑ ተማሪዎች ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን ተቋማዊ ስነ ምህዳር እና አጠቃላይ የስራ እንቅሰቃሴ ገለፃ ተሰጥቷቸው የተለያዩ ዲፓርትመንቶችን ወርክሾፖች እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡
የጉብኝቱ መሰረታዊ ዓላማ አሁን ላይ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎች በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፉ የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ በተጓዳኝነት የሚሰጥ በመሆኑ ስለሙያ ስልጠና አጠቃላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማድረግ ነው፡፡
ተማሪዎቹ እየተማሯቸው የሚገኙትን የሙያ ዘርፍ ስልጠና ወርክሾፖች የተመለከቱ ሲሆን እነሱም ኮንስትራክሽን፣ ጋርመንት /ልብስ ስፌት/፣ ከተማ ግብርና እና ሆቴል / ምግብ ዝግጅት/ የተግባር ስልጠና መስጫዎችን ተመልክተዋል፡፡
ተማሪዎቹ በተሰጣቸው ማብራሪያ እና በጉብኝት ወቅቱ ባዩት የስራ እንቅስቃሴ በጣም መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡
ሰሞኑን የአዲስ ከተማ እና የጀ/ ታደሰ ብሩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተማሪዎች በተመሳሳይ በተቋሙ ትምህርታዊ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን የሙያ ስልጠና ሂደት የተለያዩ ት/ቤቶች ጉብኝት እንዲያደርጉ የሚያስተባብረው በኮሌጁ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ቢሮ ስር የስራ ትስስርና ካውንስሊንግ የስራ ክፍል ነው፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የመስከረም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኮሌጁ የሚሰጠውን የሙያ ስልጠና ምልከታ አደረጉ!!
በአራዳ ክፍለ ከተማ የሚገኘው መስከረም የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ዛሬ መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም በኮሌጁ ትምህርታዊ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በዕለቱ 135 የሚሆኑ ተማሪዎች ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን ተቋማዊ ስነ ምህዳር እና አጠቃላይ የስራ እንቅሰቃሴ ገለፃ ተሰጥቷቸው የተለያዩ ዲፓርትመንቶችን ወርክሾፖች እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡
የጉብኝቱ መሰረታዊ ዓላማ አሁን ላይ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎች በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፉ የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ በተጓዳኝነት የሚሰጥ በመሆኑ ስለሙያ ስልጠና አጠቃላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማድረግ ነው፡፡
ተማሪዎቹ እየተማሯቸው የሚገኙትን የሙያ ዘርፍ ስልጠና ወርክሾፖች የተመለከቱ ሲሆን እነሱም ኮንስትራክሽን፣ ጋርመንት /ልብስ ስፌት/፣ ከተማ ግብርና እና ሆቴል / ምግብ ዝግጅት/ የተግባር ስልጠና መስጫዎችን ተመልክተዋል፡፡
ተማሪዎቹ በተሰጣቸው ማብራሪያ እና በጉብኝት ወቅቱ ባዩት የስራ እንቅስቃሴ በጣም መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡
ሰሞኑን የአዲስ ከተማ እና የጀ/ ታደሰ ብሩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተማሪዎች በተመሳሳይ በተቋሙ ትምህርታዊ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን የሙያ ስልጠና ሂደት የተለያዩ ት/ቤቶች ጉብኝት እንዲያደርጉ የሚያስተባብረው በኮሌጁ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ቢሮ ስር የስራ ትስስርና ካውንስሊንግ የስራ ክፍል ነው፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››