ቅዳሜ፡- ታህሳስ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
#ማስታወቂያ
ለኮሌጃችን የውስጥ ሰራተኞች እና ለውጪ የተቋማችን አጋር ማኅበረሰብ በሙሉ
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ እያለ ለበዓል ያደለባቸውን ምርጥ #በሬዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማህበረሰብ ለመሸጥ እንሆ ይላል፡፡
ስለሆነም በተዘጋጀው ጥቂት የመሸጫ ቀናት ውስጥ ፈጥነው በመምጣት የመረጡትን ሰንጋ በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመት የሚችሉ መሆኑን ስንገልጽልዎት በታላቅ ደስታ ነው፡፡
ዝም ብሎ በሬ አለ በሬ ብሎ ዝምም አለ። የእኛዎቹ በሬ ብሎ ዝም ናቸው ይላል ጀነራል ዊንጌት የግል ኢንተርፕራይዝ።
እንደ ስማችን ዊን_ጌት የሆኑ ሰንጋዎችንን መርጠው ለመግዛት ከፈለጉ ይምጡ ለበዓል ይሸምቱ ተብላችኋል።
#አድራሻ፡- ቦታ - ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ
ስልክ - 0991824160
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
#ማስታወቂያ
ለኮሌጃችን የውስጥ ሰራተኞች እና ለውጪ የተቋማችን አጋር ማኅበረሰብ በሙሉ
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ እያለ ለበዓል ያደለባቸውን ምርጥ #በሬዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማህበረሰብ ለመሸጥ እንሆ ይላል፡፡
ስለሆነም በተዘጋጀው ጥቂት የመሸጫ ቀናት ውስጥ ፈጥነው በመምጣት የመረጡትን ሰንጋ በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመት የሚችሉ መሆኑን ስንገልጽልዎት በታላቅ ደስታ ነው፡፡
ዝም ብሎ በሬ አለ በሬ ብሎ ዝምም አለ። የእኛዎቹ በሬ ብሎ ዝም ናቸው ይላል ጀነራል ዊንጌት የግል ኢንተርፕራይዝ።
እንደ ስማችን ዊን_ጌት የሆኑ ሰንጋዎችንን መርጠው ለመግዛት ከፈለጉ ይምጡ ለበዓል ይሸምቱ ተብላችኋል።
#አድራሻ፡- ቦታ - ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ
ስልክ - 0991824160
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ማክሰኞ፡- ጥር 6 ቀን 2017 ዓ.ም
የአሰልጣኞች ኢንዱስትሪ አታችመንት ቆይታ ግምገማ ተደረገ!!
ወደ ተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ሄደው የነበሩ አሰልጣኞች የአታችመንት ቆይታ ግምገማ ዛሬ ጥር 6 ቀን 2017 ዓ.ም
ተደረገ።
የአሰልጣኞች ኢንዱስትሪ አታችመንት ዓላማ አሰልጣኞቹ በጽንሰ ሀሳብ የሚያውቁትን ሙያ በኢንዱስትሪዎች ካዩት የስራ ባህል፣ ልምድ፣ ከሚጠቀሙት ቴክኖሎጂ እና ከአዳዲስ አስራር ስርዓት አንጻር ሰልጣኞቻቸውን ከገሀዱ የስራ ዓለም ጋር በተግባር አገናኝተው ስልጠና እንዲሰጡ ታቅዶ ነው።
በዚህ የኢንዱስትሪ አታችመንት ላይ ከ3 ዲፓርትመንቶች የተውጣጡ 9 አሰልጣኞች በተለያየ ምርት እና አገልግሎት በሚሰጡ 7 ኢንዱስትሪዎች ለአንድ ወር ያህል ቆይታ ማድረጋቸው የተገለፀ ሲሆን አብዛኛዎቹ /7ቱ/ የቴክስታይ ሌዘር ጋርመንት ዲፓርትመንት አሰልጣኞች ናቸው፡፡
አሰልጣኞቹ በቆይታቸው ያገኙትን ልምድና ለኢንዱስትሪው ያስተላለፉትን እውቀት በስፋት ገለፃ አድርገዋል፡፡
የአታችመንቱ መርሃ ግብር የአሰልጣኞችን አቅም ከማጎልበት አንጻር ከሚከወኑ ተግባራት አንዱ ሲሆን አሰልጣኞች የስራ ገበያውን ስርዓት በአካል ልምድ ቀስመው እና ስልጠናውን ከነባራዊ የኢንዱስትሪ ፍላጎት ጋር አዛምደው እንዲተገብሩ ቀጣይም ይህንን ስራ በስፋት ለማከናወን ዕቅድ መያዙን የኮሌጁ የተቋማት ልማት እና አስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ዲን ቢሮ አሳውቋል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
የአሰልጣኞች ኢንዱስትሪ አታችመንት ቆይታ ግምገማ ተደረገ!!
ወደ ተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ሄደው የነበሩ አሰልጣኞች የአታችመንት ቆይታ ግምገማ ዛሬ ጥር 6 ቀን 2017 ዓ.ም
ተደረገ።
የአሰልጣኞች ኢንዱስትሪ አታችመንት ዓላማ አሰልጣኞቹ በጽንሰ ሀሳብ የሚያውቁትን ሙያ በኢንዱስትሪዎች ካዩት የስራ ባህል፣ ልምድ፣ ከሚጠቀሙት ቴክኖሎጂ እና ከአዳዲስ አስራር ስርዓት አንጻር ሰልጣኞቻቸውን ከገሀዱ የስራ ዓለም ጋር በተግባር አገናኝተው ስልጠና እንዲሰጡ ታቅዶ ነው።
በዚህ የኢንዱስትሪ አታችመንት ላይ ከ3 ዲፓርትመንቶች የተውጣጡ 9 አሰልጣኞች በተለያየ ምርት እና አገልግሎት በሚሰጡ 7 ኢንዱስትሪዎች ለአንድ ወር ያህል ቆይታ ማድረጋቸው የተገለፀ ሲሆን አብዛኛዎቹ /7ቱ/ የቴክስታይ ሌዘር ጋርመንት ዲፓርትመንት አሰልጣኞች ናቸው፡፡
አሰልጣኞቹ በቆይታቸው ያገኙትን ልምድና ለኢንዱስትሪው ያስተላለፉትን እውቀት በስፋት ገለፃ አድርገዋል፡፡
የአታችመንቱ መርሃ ግብር የአሰልጣኞችን አቅም ከማጎልበት አንጻር ከሚከወኑ ተግባራት አንዱ ሲሆን አሰልጣኞች የስራ ገበያውን ስርዓት በአካል ልምድ ቀስመው እና ስልጠናውን ከነባራዊ የኢንዱስትሪ ፍላጎት ጋር አዛምደው እንዲተገብሩ ቀጣይም ይህንን ስራ በስፋት ለማከናወን ዕቅድ መያዙን የኮሌጁ የተቋማት ልማት እና አስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ዲን ቢሮ አሳውቋል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ማክሰኞ፡- ጥር 13 ቀን 2017 ዓ.ም
የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ዛሬ ጥር 13 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሄደ፡፡
ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት የግማሽ ዓመቱን የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የኮሌጁ ዕቅድና በጀት ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ባለሙያዎች ለታዳሚዎች አቅርበዋል፡፡
በቀረበው ሪፖርት መረጃ መሰረት በግማሽ ዓመቱ ልዩ ልዩ ግብዓቶችን ከማሟላት አንፃር፣ የተቋሙን መሰረተ ልማት ከማስተካከል አኳያ እና ሁሉም አካል በየዘርፉ ተነሳሽነት እና ቅንጅት ፈጥሮ ስራዎችን ከመከወን ረገድ እምርታዊ ለውጥ ያሳዬ እና ስኬታማ እንደነበር ተገልጿል፡፡
በእቅድ አፈፃፀም ውይይቱ ላይ የተገኙት ተሳታፊዎችም በቀሪው ግማሽ ዓመት ከስልጠና ሂደት፣ ከግብዓት አቅርቦት፣ ከውስጥ አሰራር፣ ከተቋማዊ ልማት እና ከማህበራዊ አግልግሎት አንፃር ቢስተካከሉ ያሏቸውን ገንቢ አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ዛሬ ጥር 13 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሄደ፡፡
ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት የግማሽ ዓመቱን የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የኮሌጁ ዕቅድና በጀት ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ባለሙያዎች ለታዳሚዎች አቅርበዋል፡፡
በቀረበው ሪፖርት መረጃ መሰረት በግማሽ ዓመቱ ልዩ ልዩ ግብዓቶችን ከማሟላት አንፃር፣ የተቋሙን መሰረተ ልማት ከማስተካከል አኳያ እና ሁሉም አካል በየዘርፉ ተነሳሽነት እና ቅንጅት ፈጥሮ ስራዎችን ከመከወን ረገድ እምርታዊ ለውጥ ያሳዬ እና ስኬታማ እንደነበር ተገልጿል፡፡
በእቅድ አፈፃፀም ውይይቱ ላይ የተገኙት ተሳታፊዎችም በቀሪው ግማሽ ዓመት ከስልጠና ሂደት፣ ከግብዓት አቅርቦት፣ ከውስጥ አሰራር፣ ከተቋማዊ ልማት እና ከማህበራዊ አግልግሎት አንፃር ቢስተካከሉ ያሏቸውን ገንቢ አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ቅዳሜ፡- ጥር 17 ቀን 2017 ዓ.ም
የአይደያ ባንክ /የሀሳብ ማቆር/ ማሰባሰብ ውይይት ተደረገ!!
በኮሌጁ የኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት አሰልጣኞች ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም የአይደያ ባንክ ማሰባሰብ ውይይት ተካሄደ፡፡
በስልጠና ዘርፉ ቀጣይ ላይ የሚተገበሩ አዳዲስ ሀሳቦችን በማሰባሰብና ወደ ተግባር በመቀየር ተቋሙ የሚጠበቅበትን ተከታታይ ለውጥ የማምጣት ኃላፊነት እንዲወጡ ለማድረግ የተካሄደ ሲሆን መድረኩን የመሩት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ናቸው፡፡
ከዚህ በፊት በኮሌጁ ላሉና በከተማ አስተዳደሩ ለሚገኙ አንዳንድ ቢሮች የዕድሳትና የማዘን ስራዎችን በመስራት ረገድ የዲፓርትመንቱ አሰልጣኞች ሚና የላቀ መሆኑ ተገልፆ ቀጣይም ይህ ተግባር ተጠናክሮ እንዲሰራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚመጡ በርካታ ተቋማት በኮሌጁ ያለውን እምርታዊ ለውጥ ልምድ ለመውሰድ የሚመጡት ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ አሻራ ያረፈበት ስኬት ሲሆን ወደ ፊትም የተሰበሰቡ ሀሳቦች በጥራት እንደሚተገበሩ እንተጋለን ተብሏል፡፡
የውይይት መድረኩ የተካሄደው በአስደማሚ ሁኔታ በታደሰው የኮንፈረስ ክፍል ሲሆን የዲን ቢሮ ጽ/ቤትን ጨምሮ የኮንፈረስ ሩሙ ውበትን እንዲጎናፀፍ ያደረጉት የኮንስትራክሽን፣ የውድ ወርክ፣ የኤሌክትሪክሲቲ፣ የጋርመንት እና ሌሎች ዘርፍ አሰልጣኞች የየድርሻቸውን በየሙያቸው ማበርከታቸው ታውቋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የአይደያ ባንክ /የሀሳብ ማቆር/ ማሰባሰብ ውይይት ተደረገ!!
በኮሌጁ የኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት አሰልጣኞች ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም የአይደያ ባንክ ማሰባሰብ ውይይት ተካሄደ፡፡
በስልጠና ዘርፉ ቀጣይ ላይ የሚተገበሩ አዳዲስ ሀሳቦችን በማሰባሰብና ወደ ተግባር በመቀየር ተቋሙ የሚጠበቅበትን ተከታታይ ለውጥ የማምጣት ኃላፊነት እንዲወጡ ለማድረግ የተካሄደ ሲሆን መድረኩን የመሩት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ናቸው፡፡
ከዚህ በፊት በኮሌጁ ላሉና በከተማ አስተዳደሩ ለሚገኙ አንዳንድ ቢሮች የዕድሳትና የማዘን ስራዎችን በመስራት ረገድ የዲፓርትመንቱ አሰልጣኞች ሚና የላቀ መሆኑ ተገልፆ ቀጣይም ይህ ተግባር ተጠናክሮ እንዲሰራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚመጡ በርካታ ተቋማት በኮሌጁ ያለውን እምርታዊ ለውጥ ልምድ ለመውሰድ የሚመጡት ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ አሻራ ያረፈበት ስኬት ሲሆን ወደ ፊትም የተሰበሰቡ ሀሳቦች በጥራት እንደሚተገበሩ እንተጋለን ተብሏል፡፡
የውይይት መድረኩ የተካሄደው በአስደማሚ ሁኔታ በታደሰው የኮንፈረስ ክፍል ሲሆን የዲን ቢሮ ጽ/ቤትን ጨምሮ የኮንፈረስ ሩሙ ውበትን እንዲጎናፀፍ ያደረጉት የኮንስትራክሽን፣ የውድ ወርክ፣ የኤሌክትሪክሲቲ፣ የጋርመንት እና ሌሎች ዘርፍ አሰልጣኞች የየድርሻቸውን በየሙያቸው ማበርከታቸው ታውቋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››