General Wingate Polytechnic college-Official channel
9.97K subscribers
3.37K photos
43 videos
204 files
198 links
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን።

የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።
Download Telegram
ረቡዕ፡- ሰኔ 19 ቀን 2016 ዓ.ም

ኮሌጁ ዛሬ ባቀረበው የፋሽን ሾው ውድድር የአሸናፊዎች አሸናፊ ተፋላሚ ኮሌጆች ጋር ተቀላቀለ!!

ፋሽን እንደተመልካቹ ሳይሆን እንደሰሪው ነው በተባለላቸው ዲዛይነሮች ተጌጠው ያሸበረቁ ቄንጠኛ አልባሳትን በውብ ተክለሰውነታቸው አዋህደው ባስተዋወቁ እንቁ ሞደሊስቶች ሲታዩ የዳኞችን ዐይን በመስረቃቸው ነገም በአሸናፊዎች አሸናፊ ሜዳ ላይ ደግመን እንያችሁ ተብለዋል።

ስለሆነም የዊንጌት ቆንጃጅቶች ነገ 5:30 ላይ በድጋሜ ከአቻዎቻቸው ጋር በመድረኩ ይወረገረጋሉ።

መቼም ከዐይን ያውጣችሁ አንልም ከዳኞች ዐይን ይጣላችሁ እንጂ ዳግመኛ መልካም ዕድል ተመኘን።

             ‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
🏆22👍124
ሐሙስ፡- ሰኔ 20 ቀን 2016 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ኤግዚቪሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ ተጠናቀቀ!!

ቴክኒክና ሙያ ለዘላቂ ልማት በሚል መሪ ቃል ለ6 ቀናት ሲካሄድ የቆየው 14ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።

በዕለቱ በክህሎት ውድድር፣ በጥናትና ምርምር፣ በቴክኖሎጂ፣ በፋሽን ሾው ትርኢትና በስፓርታዊ ጨዋታዎች ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ደረጃ  ለያዙ ኮሌጆች፣ አሰልጣኞች እና ሰልጣኞች የዋንጫ፣ የሰርተፍኬትና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በአጠቃላይ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ውድድር ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 2ኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ ተግባረ-ዕድ እና አቃቂ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጆች አንደኛና ሶስተኛ ደረጃ ሆነዋል።

በሌላ በኩል  በፋሽን ሾው ትርኢት ምስራቅ፣ እንጦጦ እና ተግባረ ዕድ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ጨርሰዋል።

በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መክብብ ወልደሐና ሲሆኑ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት የቴክኖሎጂ ዐውደ ርዕይ አጠቃላይ ዘርፉን ለህብረተሰቡ ለማስገንዘብ እና የተሰሩ የምርትና የማምረቻ ቴክኖሎጂዎች ወደ ኢንዱስትሪዎች ተሸጋግረው ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።

‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍244
Forwarded from General Wingate Students Channel (E l i a z 🌙 ኤ ል ያ ዝ | Элиаз)
ማስታወቂያ ለተመራቂ ሰልጣኞች


የባይንደር እና የመፅሄት ክፍያ ቀን እንዲጨመር በጠየቃችሁት መሰረት ለ10 ቀን ቀን ተጨምሮ እንደነበር ይታወቃል። በዚህም መሰረት ዛሬ ቅዳሜ 22/ 10 / 2016 ዓ.ም የመጨረሻ የክፍያ ቀን እንደሆነ ለማስታወስ እንወዳለን።
👍7
Forwarded from fikir
1
GWPTC 2016 GRADUATE TRAINEES LIST.xlsx
82.6 KB
ይህ የተመራቂዎች የተስተካከል የመጨረሻ ዝርዝር ነው፡፡ እዚህ ላይ ያልተካተተ ዲፓርትመኒቱን ያናግር
👍31
ሰኞ:- ሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓ.ም

ለተመራቂ ሰልጣኞች ሲሰጥ የቆየው የኬፕለር ስልጠና ተጠቀቀ!!

ለአንድ ወር ያህል ቆይታ የነበረው የተመራቂ ሰልጣኞች የኬፕለር ስልጠና ተጠናቀቀ።
                                                                                           ከ200 በላይ የሚሆኑ ተመራቂ ሰልጣኞች የኬፕለር ስልጠና የወሰዱ ሲሆን የስልጠናው መሰረታዊ ዓላማ ተመራቂዎች ወደ ስራ ኢንዱስትሪው ለመግባት የሚያስፈልጋቸውን ክህሎት ለማስጨበጥ እንደሆነ ተገልጿል።

ኬፕለር ተመራቂ ሰልጣኞችን ከኢንዱስትሪዎች ጋር ለማስተሳሰር እየሰራ ያለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን ለተመራቂዎቹ በስራ ላይ ተግባቦት፣ በጊዜ አጠቃቀም፣ በሲቪ አዘገጃጀት፣  ወዘተ ዙሪያ ትኩረት ያደረጉ የሶፍት ስኪል ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል። 

ስልጠናቸውን ላጠናቀቁ ሰልጣኞች በዛሬው ዕለት የማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት የተሰጠ ሲሆን በዕለቱ መርሃ ግብር ላይ የኮሌጁ አመራር አካላት፣ የኬፕለር ካንትሪ ዳይሬክተር ሚስተር GMV፣ ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የተውጣጡ ባለድርሻዎች እና የስልጠናው ተሳታፊ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች ተገኝተዋል። 

‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍28🙏3👌31