ሐሙስ:- ግንቦት 15 ቀን 2016 ዓ.ም
የሰልጣኞች የስምግባር ክበብ አባላት በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥ አደረጉ!!
በኮሌጁ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት የተዘጋጀው የሰልጣኞች ስነ ምግባር ክበብ አባላት ልምድ ልውውጥ በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ የተሰሩ የሰልጣኞች ስነምግባር ልምዶችን እንዲጋሩ ተደርጓል፡፡
በልምድ ልውውጡ ብልሹ አሰራሮችን ከማስወገድ አንፃር፣ የድሲፕሊን ግድፈቶችን ከማረም ረገድ፣ የግብዓት ብክነትን ከማስተካከል አኳያ ወዘተ የተሰሩ ተግባራትን የአቻ ለአቻ ተሞክሮ እንዲካፈሉ ተደርጓል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
የሰልጣኞች የስምግባር ክበብ አባላት በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥ አደረጉ!!
በኮሌጁ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት የተዘጋጀው የሰልጣኞች ስነ ምግባር ክበብ አባላት ልምድ ልውውጥ በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ የተሰሩ የሰልጣኞች ስነምግባር ልምዶችን እንዲጋሩ ተደርጓል፡፡
በልምድ ልውውጡ ብልሹ አሰራሮችን ከማስወገድ አንፃር፣ የድሲፕሊን ግድፈቶችን ከማረም ረገድ፣ የግብዓት ብክነትን ከማስተካከል አኳያ ወዘተ የተሰሩ ተግባራትን የአቻ ለአቻ ተሞክሮ እንዲካፈሉ ተደርጓል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
❤2👍2
ሐሙስ:- ግንቦት 15 ቀን 2016 ዓ.ም
የ14ኛ ቴክኒክና ሙያ ሳምንት አካል የሆነ የስፖርት ውድድር መክፈቻ ተካሄደ!!
ዘንድሮ ለ14ኛ ጊዜ የሚከበረውን የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ምክኒያት በማድረግ የተዘጋጀው የስፖርት ውድድር መክፈቻ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት ሳርቤት በሚገኘው ተስፋ ሜዳ ተካሄዷል፡፡
በመክፈቻ መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራ እና ክህሎት ቢሮ የስራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ተወካዮች እንደሁም የ15ቱም ኮሌጆች ዲኖችና የስፖርት ቤተሰቡ ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱ በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት የመክፈቻ መልዕክት ያስተላለፉት በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መክብብ ወለደ ሃና ናቸው፡፡
ኃላፊው በንግግራቸው የዝግጅቱ ዓላማ ኮሌጆች እርስ በእርስ የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉና ከስልጠና ባሻገር በስፖርት ልማቱና በማህበረሰብ አገልግሎቱ አበርክቷቸውን እንዲያረጋግጡ ነው ብለዋል፡፡ አቶ መክብብ አያይዘውም ለቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዝግጅት ከስፖርት ባሻገር የክህሎት ውድድር እየተካሄደ እንደሚገኝ እና ከሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የቴክኖሎጂ ዐውደ ርዕይ በኢግዚቪሽን ማዕከል እንደሚካሄድ ጠቁመዋል፡፡
በዛሬው መክፈቻ ዝግጅት ላይ አዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊ ከአቃቂ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር የአሰልጣኞች ጨዋታቸውን ያደረጉ ሲሆን ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአቻው ምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር ቀጣይ ቅዳሜ ግንቦት 17 ቀን 2016 ዓ.ም 3፡00 ላይ በእንጦጦ ሜዳ ግጥሚያ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
የ14ኛ ቴክኒክና ሙያ ሳምንት አካል የሆነ የስፖርት ውድድር መክፈቻ ተካሄደ!!
ዘንድሮ ለ14ኛ ጊዜ የሚከበረውን የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ምክኒያት በማድረግ የተዘጋጀው የስፖርት ውድድር መክፈቻ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት ሳርቤት በሚገኘው ተስፋ ሜዳ ተካሄዷል፡፡
በመክፈቻ መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራ እና ክህሎት ቢሮ የስራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ተወካዮች እንደሁም የ15ቱም ኮሌጆች ዲኖችና የስፖርት ቤተሰቡ ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱ በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት የመክፈቻ መልዕክት ያስተላለፉት በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መክብብ ወለደ ሃና ናቸው፡፡
ኃላፊው በንግግራቸው የዝግጅቱ ዓላማ ኮሌጆች እርስ በእርስ የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉና ከስልጠና ባሻገር በስፖርት ልማቱና በማህበረሰብ አገልግሎቱ አበርክቷቸውን እንዲያረጋግጡ ነው ብለዋል፡፡ አቶ መክብብ አያይዘውም ለቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዝግጅት ከስፖርት ባሻገር የክህሎት ውድድር እየተካሄደ እንደሚገኝ እና ከሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የቴክኖሎጂ ዐውደ ርዕይ በኢግዚቪሽን ማዕከል እንደሚካሄድ ጠቁመዋል፡፡
በዛሬው መክፈቻ ዝግጅት ላይ አዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊ ከአቃቂ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር የአሰልጣኞች ጨዋታቸውን ያደረጉ ሲሆን ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአቻው ምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር ቀጣይ ቅዳሜ ግንቦት 17 ቀን 2016 ዓ.ም 3፡00 ላይ በእንጦጦ ሜዳ ግጥሚያ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍8🏆3❤1👏1👌1
አርብ፦ ግንቦት 16 ቀን 2016 ዓ.ም
ማስታወቂያ
ውድ የኮሌጃችን ሰራተኞች እና ሰልጣኞች!
14ኛውን የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ምክኒያት በማድረግ የኮሌጃችን የአሰልጣኞች የእግር ኳስ ቡድን ነገ ቅዳሜ 3:00 ላይ በእንጦጦ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሜዳ ከአቻ ተጋጣሚው ምስራቅ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር ጨዋታውን ስለሚያደርግ በዕለቱ በቦታው በመገኘት የሞራል ድጋፋችሁን እንድትለግሱት እንገልፃለን።
በተመሳሳይ የኮሌጁ የሰልጣኞች የእግር ኳስ ቡድን ደግሞ በዚሁ ቀን 4:30 ላይ በየካ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከአቻው ተግባረ ዕድ ጋር ግጥሚያ ስለሚያደርግ ተገኝታችሁ ብርታት እንድትሆኑት እናሳውቃለን።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ማስታወቂያ
ውድ የኮሌጃችን ሰራተኞች እና ሰልጣኞች!
14ኛውን የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ምክኒያት በማድረግ የኮሌጃችን የአሰልጣኞች የእግር ኳስ ቡድን ነገ ቅዳሜ 3:00 ላይ በእንጦጦ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሜዳ ከአቻ ተጋጣሚው ምስራቅ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር ጨዋታውን ስለሚያደርግ በዕለቱ በቦታው በመገኘት የሞራል ድጋፋችሁን እንድትለግሱት እንገልፃለን።
በተመሳሳይ የኮሌጁ የሰልጣኞች የእግር ኳስ ቡድን ደግሞ በዚሁ ቀን 4:30 ላይ በየካ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከአቻው ተግባረ ዕድ ጋር ግጥሚያ ስለሚያደርግ ተገኝታችሁ ብርታት እንድትሆኑት እናሳውቃለን።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
👍8❤1
አርብ፦ ግንቦት 16 ቀን 2016 ዓ.ም
ማስታወቂያ
የቀን ለውጥ ማስተካከያ
ውድ የኮሌጃችን ሰራተኞች እና ሰልጣኞች!
14ኛውን የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ምክኒያት በማድረግ የኮሌጃችን የአሰልጣኞች እና የሰልጣኞች የእግር ኳስ ቡድን ነገ ቅዳሜ ውድድር እንዳለ መግለፃችን ይታወቃል።
ይሁን እንጂ ቅዳሜ ግንቦት 17 ቀን 2016 ዓ.ም የነበረው ጨዋታ ወደ እሁድ ማለትም ግንቦት 18 ቀን 2016 ዓ.ም የተቀየረ መሆኑን ዘግይቶ በደረሰ መረጃ አረጋግጠናል።
ስለሆነም ሁሉም ጨዋታዎች በተቀያሪው ቀን በተመሳሳይ ቦታ እና ሰዓት ስለሚካሄዱ ተገኝታችሁ ቡድኖቹን ድጋፍ እንድትሰጡ ከይቅርታ ጋር ደግመን እናሳውቀለን።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ማስታወቂያ
የቀን ለውጥ ማስተካከያ
ውድ የኮሌጃችን ሰራተኞች እና ሰልጣኞች!
14ኛውን የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ምክኒያት በማድረግ የኮሌጃችን የአሰልጣኞች እና የሰልጣኞች የእግር ኳስ ቡድን ነገ ቅዳሜ ውድድር እንዳለ መግለፃችን ይታወቃል።
ይሁን እንጂ ቅዳሜ ግንቦት 17 ቀን 2016 ዓ.ም የነበረው ጨዋታ ወደ እሁድ ማለትም ግንቦት 18 ቀን 2016 ዓ.ም የተቀየረ መሆኑን ዘግይቶ በደረሰ መረጃ አረጋግጠናል።
ስለሆነም ሁሉም ጨዋታዎች በተቀያሪው ቀን በተመሳሳይ ቦታ እና ሰዓት ስለሚካሄዱ ተገኝታችሁ ቡድኖቹን ድጋፍ እንድትሰጡ ከይቅርታ ጋር ደግመን እናሳውቀለን።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
🏆11👍8❤3👎1
አርብ:- ግንቦት 23 ቀን 2016 ዓ.ም
ለሦስት ሳምንታት ቆይታ የነበረው የአሰልጣኞች ስልጠና ተጠናቀቀ!!
ከተለያዩ ዲፓርትመንቶች የተውጣጡ አሰልጣኞች የተሳተፉበት የአሰልጣኞች ስልጠና #ኬፕለር በተሰኘ ግብረሰናይ ድርጀት አማካኝነት የተሰጠ ሲሆን መሠረታዊ ዓላማው ለተመራቂ ሰልጣኞች ከስራ ገበያው ጋር አዎንታዊ ምልከታ እና በጎ ተጽዕኖ እንዲናራቸው የሚያስችል የሶፍት ስኬል ስልጠና እንዲሰጡ ታቅዶ መሆኑን ሰምተናል።
ስልጠናው በሙያው ብዙ ልምድን ባካበቱ የዘርፉ ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን 20 የሚሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኞች እና ከጎፋ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተቀላቀሉ 3 አሰልጣኞች ተሳትፈዋል።
በሌላ ዜና ብቃት የወጣቶች ስልጠናን ወሰደው በኢንዱስትሪዎች ላይ የስራ ልምምድ እያደረጉ የነበሩ 400 ወጣቶች 3ኛ ወራቸው ላይ ወደ ኮሌጁ በመመለስ ለ5 ቀናት የዲጂታል ስኪል ስልጠና ሲወስዱ ቆይተው በትናንትናው ዕለት አጠናቀዋል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ለሦስት ሳምንታት ቆይታ የነበረው የአሰልጣኞች ስልጠና ተጠናቀቀ!!
ከተለያዩ ዲፓርትመንቶች የተውጣጡ አሰልጣኞች የተሳተፉበት የአሰልጣኞች ስልጠና #ኬፕለር በተሰኘ ግብረሰናይ ድርጀት አማካኝነት የተሰጠ ሲሆን መሠረታዊ ዓላማው ለተመራቂ ሰልጣኞች ከስራ ገበያው ጋር አዎንታዊ ምልከታ እና በጎ ተጽዕኖ እንዲናራቸው የሚያስችል የሶፍት ስኬል ስልጠና እንዲሰጡ ታቅዶ መሆኑን ሰምተናል።
ስልጠናው በሙያው ብዙ ልምድን ባካበቱ የዘርፉ ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን 20 የሚሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኞች እና ከጎፋ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተቀላቀሉ 3 አሰልጣኞች ተሳትፈዋል።
በሌላ ዜና ብቃት የወጣቶች ስልጠናን ወሰደው በኢንዱስትሪዎች ላይ የስራ ልምምድ እያደረጉ የነበሩ 400 ወጣቶች 3ኛ ወራቸው ላይ ወደ ኮሌጁ በመመለስ ለ5 ቀናት የዲጂታል ስኪል ስልጠና ሲወስዱ ቆይተው በትናንትናው ዕለት አጠናቀዋል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍11
ቅዳሜ :- ግንቦት 24 ቀን 2016 ዓ.ም
ሰልጣኛኞች የላብ አደሮች ቀንን አከበሩ!!
የዛሬዎቹ ሰልጣኞችና የነገዎቹ ሰራተኞች በትናንትው ዕለት የላብ አደሮች ቀን /ወርከርስ ደይ/ በሚል መነሻ በልዩ ልዩ ትርዒት አከበሩ።
በእኛ ሚያዚያ 23 በጎርጎሮሳዊያኑ ደግሞ ግንቦት /ሜይ/ 1 ተከብሮ እና ታስቦ የሚውለውን የላብ አደሮች ቀን ምክንያት በማድረግ ሜይ 31 ወይም የወሩ መጨረሻ ቀን ላይ አስበውታል።
በዚህ ዝግጅት የእሳት እና ድንገተኛ አደጋ መከላከያ ተሽከርካሪዎችን ጭምር በመጠቀም ልዩ ልዩ አዝናኝ እና አስተማሪ ትርኢቶች አሳይተዋል።
ግቢ ውስጥ በየዓመቱ በሰልጣኛኞች ለተዝናኖት እና ለትምህርት ከሚከበሩ መካከል አንዱ የሰራተኞች ቀን ነው።
የላብ አደሮች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲከበር ገፊ ምክንያቱ የቀን የስራ ሰዓት ከ10 እስከ 16 የነበረው 8:00 እንዲሆን፣ የስራ ቦታ ለህይወት ደህንነት አደጋ አጋላጭ ከሆኑ ነገሮች እንዲስተካከል፣ ቅዳሜም እንደ እሁድ የእረፍት ቀን እንዲቆጠርና መሰል ጥያቄዎች በጊዜው ለነበሩ አሜሪካዊ አሰሪ ከበርቲዎችና ባለ ስልጣናት በተለያየ ጊዜ በአመፅ ቀርቦና መሰዋትነት ተከፍሎ የመጨረሻ መልስ ያገኘው ሚያዝያ 23/ሜይ 1 ቀን 1880 ሲሆን አሁን ላይ ቀኑ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ66 አገራት ሲከበር በሌሎች ደግሞ ታስቦ እንደሚውል ይታወቃል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ሰልጣኛኞች የላብ አደሮች ቀንን አከበሩ!!
የዛሬዎቹ ሰልጣኞችና የነገዎቹ ሰራተኞች በትናንትው ዕለት የላብ አደሮች ቀን /ወርከርስ ደይ/ በሚል መነሻ በልዩ ልዩ ትርዒት አከበሩ።
በእኛ ሚያዚያ 23 በጎርጎሮሳዊያኑ ደግሞ ግንቦት /ሜይ/ 1 ተከብሮ እና ታስቦ የሚውለውን የላብ አደሮች ቀን ምክንያት በማድረግ ሜይ 31 ወይም የወሩ መጨረሻ ቀን ላይ አስበውታል።
በዚህ ዝግጅት የእሳት እና ድንገተኛ አደጋ መከላከያ ተሽከርካሪዎችን ጭምር በመጠቀም ልዩ ልዩ አዝናኝ እና አስተማሪ ትርኢቶች አሳይተዋል።
ግቢ ውስጥ በየዓመቱ በሰልጣኛኞች ለተዝናኖት እና ለትምህርት ከሚከበሩ መካከል አንዱ የሰራተኞች ቀን ነው።
የላብ አደሮች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲከበር ገፊ ምክንያቱ የቀን የስራ ሰዓት ከ10 እስከ 16 የነበረው 8:00 እንዲሆን፣ የስራ ቦታ ለህይወት ደህንነት አደጋ አጋላጭ ከሆኑ ነገሮች እንዲስተካከል፣ ቅዳሜም እንደ እሁድ የእረፍት ቀን እንዲቆጠርና መሰል ጥያቄዎች በጊዜው ለነበሩ አሜሪካዊ አሰሪ ከበርቲዎችና ባለ ስልጣናት በተለያየ ጊዜ በአመፅ ቀርቦና መሰዋትነት ተከፍሎ የመጨረሻ መልስ ያገኘው ሚያዝያ 23/ሜይ 1 ቀን 1880 ሲሆን አሁን ላይ ቀኑ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ66 አገራት ሲከበር በሌሎች ደግሞ ታስቦ እንደሚውል ይታወቃል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👎7👍3👌2