ማክሰኞ:- ሚያዚያ 22 ቀን 2016 ዓ.ም
ኮሌጁ ያደለባቸውን በሬዎች ለበዓል ገበያ አቀረበ!!
በኮሌጁ የከተማ ግብርና ዘርፍ ስልጠና ለመስጠት እና ተቋማዊ የውስጥ ገቢውን ለማሳደግ ከዚህ በፊት ገዝቶ ያደለባቸውን በሬዎች ለትንሳኤ በዓል ገበያ አቀረበ፡፡
የከተማ ግብርና ዲፓርትመንት ለሚሰጣቸው የእንሰሳት ሙያ ስልጠናዎች ወርክሾፕነት እና የኮሌጁን የውስጥ ገቢ አቅም ከፍ ለማድረግ ታቅዶ ተገዝተው እየደለቡ የሚገኙ ከ25 በላይ በሬዎችን ለበዓለ ትንሳኤ ገበያ አቅርቧል፡፡
በሬዎቹ ለኮሌጁ ማህበረሰብ እና ለአካባቢው ነዋሪ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተሸጡ ሲሆን ዝቅተኛው 40 ሺ ብር ከፍተኛው ደግሞ 80 ሺ ብር እየተከፈለባቸውም ይገኛል፡፡
ቀጣይም በሬዎችን በስፋት የማድለብ እና እሴት የተጨመረባቸው የፍጆታ ግብዓቶችን ለማህበረሰቡ በማቅረብ የተቋሙን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ እቅድ መያዙን የገለፁልን ደግሞ በኮሌጁ የውስጥ ገቢ አቅም ማሳደግ ዘርፍ ተጠሪ የሆኑት አቶ አበጀ በለጠ ናቸው፡፡
‹‹ በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ኮሌጁ ያደለባቸውን በሬዎች ለበዓል ገበያ አቀረበ!!
በኮሌጁ የከተማ ግብርና ዘርፍ ስልጠና ለመስጠት እና ተቋማዊ የውስጥ ገቢውን ለማሳደግ ከዚህ በፊት ገዝቶ ያደለባቸውን በሬዎች ለትንሳኤ በዓል ገበያ አቀረበ፡፡
የከተማ ግብርና ዲፓርትመንት ለሚሰጣቸው የእንሰሳት ሙያ ስልጠናዎች ወርክሾፕነት እና የኮሌጁን የውስጥ ገቢ አቅም ከፍ ለማድረግ ታቅዶ ተገዝተው እየደለቡ የሚገኙ ከ25 በላይ በሬዎችን ለበዓለ ትንሳኤ ገበያ አቅርቧል፡፡
በሬዎቹ ለኮሌጁ ማህበረሰብ እና ለአካባቢው ነዋሪ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተሸጡ ሲሆን ዝቅተኛው 40 ሺ ብር ከፍተኛው ደግሞ 80 ሺ ብር እየተከፈለባቸውም ይገኛል፡፡
ቀጣይም በሬዎችን በስፋት የማድለብ እና እሴት የተጨመረባቸው የፍጆታ ግብዓቶችን ለማህበረሰቡ በማቅረብ የተቋሙን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ እቅድ መያዙን የገለፁልን ደግሞ በኮሌጁ የውስጥ ገቢ አቅም ማሳደግ ዘርፍ ተጠሪ የሆኑት አቶ አበጀ በለጠ ናቸው፡፡
‹‹ በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍5👏1
ማክሰኞ:- ሚያዚያ 22 ቀን 2016 ዓ.ም
የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳው ግንባታ እየተፋጠነ ነው!!
በኮሌጁ ዋና በር መግቢያ ላይ የሚገኘውና በተለምዶ ትንሹ የእግር ኳስ ሜዳ እየተባለ የሚጠራው ቦታ ደረጃውን የጠበቀ ዘመናዊ የእግር ኳስ ማዘውተሪያ ሜዳ እንዲሆን ታቅዶ በቅርቡ ስራው የተጀመረ ሲሆን አሁን ላይ ግንባታው እየተፋጠነ ይገኛል::
ማህበረሰባዊ የግል አጋሮች ተሳትፎ /Public Private Partnership participation/ በሚለው መርህ መሰረት ፉት ፒች ኃላ/የተ/የግ ድርጅት በተሰኘ ኩባንያ ግንባታው እየተሰራ የሚገኘው የእግር ኳስ መለማመጃ ሜዳ አሁን ላይ ከ4 ውስጥ የአንደኛው ዘመናዊ ሜዳ ግንባታ በፍጥነት እየተሰራ ይገኛል፡፡
ወደ 20 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚጠይቀውን የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ ስራ ኮሌጁ የግል አልሚዎችን በመጋበዝ ወደ ስራ ከተገባ ጥቂት ቀናት ተቆጥረዋል፡፡
ሜዳው አርቲፊሻል ሳር ማልበስን ጨምሮ ልዩ ልዩ ግብዓቶች የሚሟሉለት ሲሆን ስራው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በማህበረስብ አገልገሎት ዘርፍ የአካባቢው ወጣቶች በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጊዜያቸውን እንዲያሳልፉ፣ የኮሌጁ ተቋማዊ ገጽታ ማራኪ እንዲሆን፣ የኮሌጁ የውስጥ ገቢ እንዲያድግ፣ ለተለያዩ የጤና ስፖርት ቡድኖችና ለኮሌጁ ማህበረሰብ ስፖርታዊ እንቀስቃሴ እንዲያደርጉ ታስቦ ወደ ስራ መገባቱን መዘገባችን ይታወቃል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳው ግንባታ እየተፋጠነ ነው!!
በኮሌጁ ዋና በር መግቢያ ላይ የሚገኘውና በተለምዶ ትንሹ የእግር ኳስ ሜዳ እየተባለ የሚጠራው ቦታ ደረጃውን የጠበቀ ዘመናዊ የእግር ኳስ ማዘውተሪያ ሜዳ እንዲሆን ታቅዶ በቅርቡ ስራው የተጀመረ ሲሆን አሁን ላይ ግንባታው እየተፋጠነ ይገኛል::
ማህበረሰባዊ የግል አጋሮች ተሳትፎ /Public Private Partnership participation/ በሚለው መርህ መሰረት ፉት ፒች ኃላ/የተ/የግ ድርጅት በተሰኘ ኩባንያ ግንባታው እየተሰራ የሚገኘው የእግር ኳስ መለማመጃ ሜዳ አሁን ላይ ከ4 ውስጥ የአንደኛው ዘመናዊ ሜዳ ግንባታ በፍጥነት እየተሰራ ይገኛል፡፡
ወደ 20 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚጠይቀውን የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ ስራ ኮሌጁ የግል አልሚዎችን በመጋበዝ ወደ ስራ ከተገባ ጥቂት ቀናት ተቆጥረዋል፡፡
ሜዳው አርቲፊሻል ሳር ማልበስን ጨምሮ ልዩ ልዩ ግብዓቶች የሚሟሉለት ሲሆን ስራው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በማህበረስብ አገልገሎት ዘርፍ የአካባቢው ወጣቶች በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጊዜያቸውን እንዲያሳልፉ፣ የኮሌጁ ተቋማዊ ገጽታ ማራኪ እንዲሆን፣ የኮሌጁ የውስጥ ገቢ እንዲያድግ፣ ለተለያዩ የጤና ስፖርት ቡድኖችና ለኮሌጁ ማህበረሰብ ስፖርታዊ እንቀስቃሴ እንዲያደርጉ ታስቦ ወደ ስራ መገባቱን መዘገባችን ይታወቃል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍13❤3👌2
ማክሰኞ:- ሚያዚያ 22 ቀን 2016 ዓ.ም
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ተደረገ።
የ2016 የትምህርት ዘመን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከሐምሌ 9 እስከ ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ/ም ደግሞ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል ተብሏል።
በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 6 እስከ 7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናልም መባሉን ሰምተናል።
መረጃውን እውቁልኝ ብሎ በማህበራዊ ትስስር ገጽ ያጋራው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ምንጭ፡- የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ተደረገ።
የ2016 የትምህርት ዘመን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከሐምሌ 9 እስከ ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ/ም ደግሞ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል ተብሏል።
በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 6 እስከ 7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናልም መባሉን ሰምተናል።
መረጃውን እውቁልኝ ብሎ በማህበራዊ ትስስር ገጽ ያጋራው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ምንጭ፡- የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
👍13❤4
ማክሰኞ:- ግንቦት 6 ቀን 2016 ዓ.ም
በክላስተር ደረጃ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር ተደረገ!!
ከተለያዩ ኮሌጁች ተውጣጥተው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በቡድን የሰሩ አሰልጣኞች የጥናት ውጤት ሰነዳቸውን በዛሬው ዕለት ለውውድር አቀረቡ።
በዚህ ውድድር በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ በአዲስ ከተማ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እና በኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ አሰልጣኞች የተሰሩ 3 የጥናትና ምርምር ሰነዶች ለባለሙያዎች ቀርበው ተወዳድረዋል፡፡
በውድድሩ ርዕሰ ጉዳዩ አንገብጋቢ ችግር መሆኑ፣ ከችግሩ ጋር የተሰናሰለ ዓላማ መቀረጹ፣ ችግሩን ለመፍታት የተደረገው ርቀት፣ በምርምር ሂደቱ የተገኙ ውጤቶች፣ ወዘተ የሚሉ መስፈርቶች ተካተዋል።
በዚህ ውድድር በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኞች የተሰራው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሰነድ አሸናፊ ሆኖ በከተማ ደረጃ ለሚደረገው ውድድር አልፏል፡፡
በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኞች የተሰራው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሰነድ የአዳዲስ ሰልጣኞችን መጠነ ማቋረጥና ማቆራረጥን ለመቀነስ የተነሳ እንደሆነ መዘገባችን ይታወቃል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
በክላስተር ደረጃ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር ተደረገ!!
ከተለያዩ ኮሌጁች ተውጣጥተው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በቡድን የሰሩ አሰልጣኞች የጥናት ውጤት ሰነዳቸውን በዛሬው ዕለት ለውውድር አቀረቡ።
በዚህ ውድድር በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ በአዲስ ከተማ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እና በኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ አሰልጣኞች የተሰሩ 3 የጥናትና ምርምር ሰነዶች ለባለሙያዎች ቀርበው ተወዳድረዋል፡፡
በውድድሩ ርዕሰ ጉዳዩ አንገብጋቢ ችግር መሆኑ፣ ከችግሩ ጋር የተሰናሰለ ዓላማ መቀረጹ፣ ችግሩን ለመፍታት የተደረገው ርቀት፣ በምርምር ሂደቱ የተገኙ ውጤቶች፣ ወዘተ የሚሉ መስፈርቶች ተካተዋል።
በዚህ ውድድር በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኞች የተሰራው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሰነድ አሸናፊ ሆኖ በከተማ ደረጃ ለሚደረገው ውድድር አልፏል፡፡
በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኞች የተሰራው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሰነድ የአዳዲስ ሰልጣኞችን መጠነ ማቋረጥና ማቆራረጥን ለመቀነስ የተነሳ እንደሆነ መዘገባችን ይታወቃል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍18
ረቡዕ:- ግንቦት 14 ቀን 2016 ዓ.ም
Unite in the fight against HIV/Aids!
ከኤች አይ ቪ/ ኤድስ መከላከያ ጋር በተያያዘ የግንዛቤ መድረክ ተደረገ!!
ለኮሌጁ ሰራተኞች እና ሰልጣኞች ከኤች አይ/ ኤድስ መከላከያ ጋር በተያያዘ የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ትናንት ግንቦት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ተደረገ፡፡
በአሁኑ ሰዓት ከሰዎች መዘናጋት ጋር ተያይዞ እንደ አዲስ ብዙ ሰዎችን ማጥቃት የጀመረው የኤች አይ ቪ ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ያስችል ዘንድ መድረኩ መዘጋጀቱን ሰምተናል፡፡
በዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ በመጡ ባለሙያ ወቅታዊ የቫይረሱን የስርጭት አድማስ እና በሽታውን የመከላከያ ስልቶች ገለፃ እንዲደረግባቸው ተደርጓል፡፡
መድረኩን በሁለት ዙር /ጧት እና ከሰዓት/ ያዘጋጁት የኮሌጁ ጤና ባለሙያዎች እና የሚኒስትሪሚንግ ኮሚቴ አባላት ሲሆኑ ዋና ዓላማው ለኮሌጁ ማህበረሰብ ግንዛቤ በመፍጠር በቫይረሱ ጉዳይ ላይ የአመለካከት ለውጥ እንዲመጣ ማድረግ ነው ብለዋል፡፡ TEST OFTEN, TREAT EARLY, STAY SAFE.
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
Unite in the fight against HIV/Aids!
ከኤች አይ ቪ/ ኤድስ መከላከያ ጋር በተያያዘ የግንዛቤ መድረክ ተደረገ!!
ለኮሌጁ ሰራተኞች እና ሰልጣኞች ከኤች አይ/ ኤድስ መከላከያ ጋር በተያያዘ የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ትናንት ግንቦት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ተደረገ፡፡
በአሁኑ ሰዓት ከሰዎች መዘናጋት ጋር ተያይዞ እንደ አዲስ ብዙ ሰዎችን ማጥቃት የጀመረው የኤች አይ ቪ ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ያስችል ዘንድ መድረኩ መዘጋጀቱን ሰምተናል፡፡
በዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ በመጡ ባለሙያ ወቅታዊ የቫይረሱን የስርጭት አድማስ እና በሽታውን የመከላከያ ስልቶች ገለፃ እንዲደረግባቸው ተደርጓል፡፡
መድረኩን በሁለት ዙር /ጧት እና ከሰዓት/ ያዘጋጁት የኮሌጁ ጤና ባለሙያዎች እና የሚኒስትሪሚንግ ኮሚቴ አባላት ሲሆኑ ዋና ዓላማው ለኮሌጁ ማህበረሰብ ግንዛቤ በመፍጠር በቫይረሱ ጉዳይ ላይ የአመለካከት ለውጥ እንዲመጣ ማድረግ ነው ብለዋል፡፡ TEST OFTEN, TREAT EARLY, STAY SAFE.
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍4