ረቡዕ:- መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም
የኮሌጁ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የንብረት አያያዜን ከማኑዋል ወደ ዲጅታል ላሸጋግር ነው አለ!!
ዳይሬክቶሬቱ ይህንን ያሳወቀው እንደ ከተማ አስተዳደር የለማውን ዘመናዊ የንበረት አስተዳደር ሶፍትዌር አጠቃቀም ለሚመለከታቸው የዳይሬክቶሬቱ እና የመንግስት ህንፃ አስተዳደር እና አገልግሎት ጽ/ቤት ባለሙያዎች ስልጠናዎችን እየሰጠ ባለበት ጊዜ ነው፡፡
በዚህ ስልጠና ላይ 16 ባለሙያዎች እየተሳተፉ የሚገኝ ሲሆን ከንብረት ጋር የተያያዙ ጽንሰ ሀሳባዊ ገለፃ ከመሰጠቱ ባሻገር መሰረታዊ የኮምፒውተር አጠቃቀም እና አጠቃላይ በለማው ሶፍትዊር ዙሪያ ተግባራዊ የክህሎት ስልጠና በኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ /ICT/ ዲፓርትመንት አሰልጣኞች እየተሰጠ ይገኛል፡፡
የተቋሙን ንብረት በቀላሉ ለመቆጣጠር፣ አሰራሩን ለማዘመን እና የንብረት አጠቃቀምን ፍትሐዊነት ለማምጣት ያስችል ዘንድ ተግባራዊ ለማድረግ የታቀደው ዲጅታላይዜሽን ስርዓት ስልጠናው እንደተጠናቀቀ ወደ ስራ ይገባል ያሉን የኮሌጁ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ጨመዳ ናቸው፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም ስርዓቱ የንብረት ብክነትን እና የተንዛዛ አሰራርን ያስቀራል ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን እና የከተማ አስተዳደሩ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ለዚህ ተግባር የለማው ሶፍትዌር በሁሉም የመንግስት ተቋማት ይተገበር ዘንድ ከዘርፉ ለተውጣጡ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና እንደሰጠ መዘገባችን አይዘነጋም፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
የኮሌጁ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የንብረት አያያዜን ከማኑዋል ወደ ዲጅታል ላሸጋግር ነው አለ!!
ዳይሬክቶሬቱ ይህንን ያሳወቀው እንደ ከተማ አስተዳደር የለማውን ዘመናዊ የንበረት አስተዳደር ሶፍትዌር አጠቃቀም ለሚመለከታቸው የዳይሬክቶሬቱ እና የመንግስት ህንፃ አስተዳደር እና አገልግሎት ጽ/ቤት ባለሙያዎች ስልጠናዎችን እየሰጠ ባለበት ጊዜ ነው፡፡
በዚህ ስልጠና ላይ 16 ባለሙያዎች እየተሳተፉ የሚገኝ ሲሆን ከንብረት ጋር የተያያዙ ጽንሰ ሀሳባዊ ገለፃ ከመሰጠቱ ባሻገር መሰረታዊ የኮምፒውተር አጠቃቀም እና አጠቃላይ በለማው ሶፍትዊር ዙሪያ ተግባራዊ የክህሎት ስልጠና በኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ /ICT/ ዲፓርትመንት አሰልጣኞች እየተሰጠ ይገኛል፡፡
የተቋሙን ንብረት በቀላሉ ለመቆጣጠር፣ አሰራሩን ለማዘመን እና የንብረት አጠቃቀምን ፍትሐዊነት ለማምጣት ያስችል ዘንድ ተግባራዊ ለማድረግ የታቀደው ዲጅታላይዜሽን ስርዓት ስልጠናው እንደተጠናቀቀ ወደ ስራ ይገባል ያሉን የኮሌጁ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ጨመዳ ናቸው፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም ስርዓቱ የንብረት ብክነትን እና የተንዛዛ አሰራርን ያስቀራል ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን እና የከተማ አስተዳደሩ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ለዚህ ተግባር የለማው ሶፍትዌር በሁሉም የመንግስት ተቋማት ይተገበር ዘንድ ከዘርፉ ለተውጣጡ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና እንደሰጠ መዘገባችን አይዘነጋም፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍7❤3
አርብ:- መጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም
ለኮሌጁ ሰልጣኞች በተቋማዊ ስነ ምግባር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ!!
ለኮሌጁ ሰልጣኞች በተቋማዊ ስነ ምግባር ዙሪያ ላይ ትኩረት ያደረገ የ2 ቀን ስልጠና ተሰጠ፡፡
የኮሌጁ የስነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት በስነምግባር ምንነትና አስፈላጊነት፣ በሰልጣኞች የስነምግባር ክበብ ምንነትና ጥቅም እንዲሁም የብልሹ አሰራር ዓይነቶች፣ የመከላከያ መንገዶች እና ስነ ምግባር ከሰልጣኞች የስልጠና አሰጣጥ አንጻር ያለውን ትርጉም ወዘተ በተመለከተ መጋቢት 18 እና 19 ቀን 2016 ዓ.ም የ2 ቀናት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ለኮሌጁ ሰልጣኞች በተቋማዊ ስነ ምግባር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ!!
ለኮሌጁ ሰልጣኞች በተቋማዊ ስነ ምግባር ዙሪያ ላይ ትኩረት ያደረገ የ2 ቀን ስልጠና ተሰጠ፡፡
የኮሌጁ የስነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት በስነምግባር ምንነትና አስፈላጊነት፣ በሰልጣኞች የስነምግባር ክበብ ምንነትና ጥቅም እንዲሁም የብልሹ አሰራር ዓይነቶች፣ የመከላከያ መንገዶች እና ስነ ምግባር ከሰልጣኞች የስልጠና አሰጣጥ አንጻር ያለውን ትርጉም ወዘተ በተመለከተ መጋቢት 18 እና 19 ቀን 2016 ዓ.ም የ2 ቀናት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍11❤5👎1
ቅዳሜ፦ መጋቢት 28 ቀን 2016 ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለኮሌጁ አሰልጣኞች እና አስተዳደር ሠራተኞች በሙሉ
ሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም በወቅታዊ የፐብሊክ ሰርቪስ ስራ አተገባበር ዙሪያ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ስላለ በእለቱ ከጧቱ 2:30 ላይ አስተዳደር ህንጻ 4ኛ ፎቅ በሚገኘው አዲሱ አዳራሽ እንዲትገኙ እያሳሰብን ነገር ግን መደበኛው የስልጠና ሂደት መኖሩን እናሳውቃለን።
የኮሌጁ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
ማስታወቂያ
ለኮሌጁ አሰልጣኞች እና አስተዳደር ሠራተኞች በሙሉ
ሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም በወቅታዊ የፐብሊክ ሰርቪስ ስራ አተገባበር ዙሪያ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ስላለ በእለቱ ከጧቱ 2:30 ላይ አስተዳደር ህንጻ 4ኛ ፎቅ በሚገኘው አዲሱ አዳራሽ እንዲትገኙ እያሳሰብን ነገር ግን መደበኛው የስልጠና ሂደት መኖሩን እናሳውቃለን።
የኮሌጁ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
👍8