Forwarded from Addis Ababa Education Bureau (Abebe Chernet)
የመምህራንን_የጋራ_መኖሪያ_ቤት_ዕጣ_የዕድለኞች_ዝርዝር.pdf
23.3 MB
👍16😢4
VISIT THIS PAGE :-http://www.gwptc.edu.et/
👍3
ረቡዕ:- መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም
የታደሰው ካፌ ዛሬ በይፋ ስራ ጀመረ!!
ዕፁብ ድንቅ ሆኖ በመታደስ ዛሬ ስራ የጀመረው የኮሌጁ ሰራተኞች መዝናኛ ክበብ ከምን ተነስቶ የት እንደደረሰ የሚያስቃኝ በወፍ በረር ለመዳሰስ ሞከረን፡፡
ኮሌጁ በዚህ ዓመት ከሰራቸው የብዙ ብዙ ስኬቶች አንዱ ነባሩን የሰራተኞች ካፌ ስርነቀላዊ እና እምርታዊ በሆነ ለውጥ ማደስ ነው፡፡ የዚህ ፕሮጀክት ዋና መሪ የዲራፍቲንግ ቴክኖሎጂ አሰልጣኝ እና የአርትቴክት ባለሙያ አሰልጣኝ ሳሙኤል ኤሊያስ ናቸው፡፡ ለዚህ ስራ ተነሳሽነታችሁን ያመጣው ገፊ ምክኒያት ምንድን ነው የሚለውን ጥያቄ ለአሰልጣኝ ሳሙኤል አነሳን፡፡ ‹‹በኮሌጁ የበላይ ኃላፊዎች ተቋማዊ ለውጥን ለማምጣት በሚደረገው አዳዲስ ሀሳቦችን የማሰባሰብ ሂደት ላይ ተነስቼ በመጀመሪያ ደረጃ ለሰራተኞች ምቹ ከባቢ በመፍጠር ለሁሉም ሌሎች ተግባራት መነቃቃትን ይፈጥራል የሚል እምነት ስላደረብኝ እና ለዚህ ደግሞ ሰራተኛውን የመጠነ ዘመናዊ የሰራተኞች መዝናኛ ክበብ መኖሩ ግድ መሆኑን ስለተገነዘብኩ ይህንን እድሳት ለማድረግ አቅጄ ወደ ስራ ገባሁ፡፡›› ይላሉ አሰልጣኝ ሳሙኤል፡፡
በዚህ ዕድሳት ላይ ስታንዳርዱን ያስጠበቁ ልዩ ልዩ አዳዲስ ተግባራት የተከናወኑ ሲሆን በአጠቃላይ 530 ካሬ ሜትር የሚሸፍን ስራ በጥራት እና በስፋት ተከናውኗል፡፡ ሁሉም ነገር በአዲስ መልኩ ነው የተሰራው፡፡ ለዚህ ስራ እውቀታቸውን የገለፁ፣ ክህሎታቸውን ያሳዩ፣ ልምዳቸውን ያጋራ ባለ አሻራዎች ብዙ መሆናቸውን ከአሰልጣኙ አንደበት ሰምተናል፡፡ ሰፊውን የሲቪል ስራ ኮንስትራክሽኖች፣ በሚያምር ውበት የኤሌክትሪክ ዝርጋታውን ኤሌክትሪክሲቲዎች፣ በሚስብ ዲዛይን የጥልፍ እና መጋረጃ ስራዎችን ጋርመንቶች፣ ማራኪ የእንጨት ስራዎችን ውድ ወርኮች፣ ውብ አደረጃጀቱን ሆቴሎች፣ ልዩ ልዩ የብረታብረት ምርቶችን ሜታል ወርኮች ወዘተ በመተባበር ሁሉም በባለቤትነት ስሜት አሻራቸውን እንዳስቀመጡ ታውቋል፡፡
ይህ ስራ የእንጨት፣ የብረት ብረት፣ የኤሌክትሪክ ግባዓቶችን ጨምሮ አጠቃላይ ወጪ ወደ 13.5 ሚሊዮን ብር ኢንቨስት እንደተደረገበትም ከአሰልጣኝ ሳሙኤል መረጃ አግኝተናል፡፡
ለሰራተኞች ምቹ መዝናኛ ክበብን ከማደስ ባሻገር የስራው ሂደት ያመጣው ፋይዳ ይኖር ይሆን የሚል የመሰናበቻ ጥያቄ ለአርትቴክተሩ አነሳን፡፡ ‹‹በዚህ ስራ ላይ የተካፈሉ ብዙዎች እርስ በእርሳቸው በሙያቸው ልምድ ልውውጥ አድርገዋል፣ ከማሰልጠን ባሻገር ያለውን ሙያዊ ብቃት አሳይተዋል እንዲሁም ለሰልጣኞቻቸው የተግባር ልምምድ እንዲያደርጉ ዕድል ፈጥሮላቸዋል የሚል ሀሳብ ሰጥተውናል፡፡
አሰልጣኝ ሳሙኤል ከዚህ ፕሮጀክት ውጪም ስማርት ክላስ መፍጠር የሚለውን ጽንሰ ሀሳብ ተጋርተው ለሁሉም ዲፓርመንቶች የተገጠሙ ኢንተራክቲቭ ቦርዶች እውን እንዲሆኑ ትግበራው ላይ የአንበሳውን ድርሻ ወስደዋል፡፡
በዚህ ድንቅ ውበት ተከሽኖ ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነውን መዝናኛ ክበብ በጥራት እና በተመጣጣኝ ዋጋ አገልግሎት እሰጣለሁ ብለው ጨረታውን ያሸነፉ ባለሀብት ዛሬ ስራቸውን በይፋ የጀመሩ ሲሆን የዛሬውን የምሳ መስተንግዶ ለሁሉም ሰራተኞች በባለ ሀብቱ ሙሉ ወጪ በግብዣ መልኩ እንደሚሸፈን ታውቋል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
የታደሰው ካፌ ዛሬ በይፋ ስራ ጀመረ!!
ዕፁብ ድንቅ ሆኖ በመታደስ ዛሬ ስራ የጀመረው የኮሌጁ ሰራተኞች መዝናኛ ክበብ ከምን ተነስቶ የት እንደደረሰ የሚያስቃኝ በወፍ በረር ለመዳሰስ ሞከረን፡፡
ኮሌጁ በዚህ ዓመት ከሰራቸው የብዙ ብዙ ስኬቶች አንዱ ነባሩን የሰራተኞች ካፌ ስርነቀላዊ እና እምርታዊ በሆነ ለውጥ ማደስ ነው፡፡ የዚህ ፕሮጀክት ዋና መሪ የዲራፍቲንግ ቴክኖሎጂ አሰልጣኝ እና የአርትቴክት ባለሙያ አሰልጣኝ ሳሙኤል ኤሊያስ ናቸው፡፡ ለዚህ ስራ ተነሳሽነታችሁን ያመጣው ገፊ ምክኒያት ምንድን ነው የሚለውን ጥያቄ ለአሰልጣኝ ሳሙኤል አነሳን፡፡ ‹‹በኮሌጁ የበላይ ኃላፊዎች ተቋማዊ ለውጥን ለማምጣት በሚደረገው አዳዲስ ሀሳቦችን የማሰባሰብ ሂደት ላይ ተነስቼ በመጀመሪያ ደረጃ ለሰራተኞች ምቹ ከባቢ በመፍጠር ለሁሉም ሌሎች ተግባራት መነቃቃትን ይፈጥራል የሚል እምነት ስላደረብኝ እና ለዚህ ደግሞ ሰራተኛውን የመጠነ ዘመናዊ የሰራተኞች መዝናኛ ክበብ መኖሩ ግድ መሆኑን ስለተገነዘብኩ ይህንን እድሳት ለማድረግ አቅጄ ወደ ስራ ገባሁ፡፡›› ይላሉ አሰልጣኝ ሳሙኤል፡፡
በዚህ ዕድሳት ላይ ስታንዳርዱን ያስጠበቁ ልዩ ልዩ አዳዲስ ተግባራት የተከናወኑ ሲሆን በአጠቃላይ 530 ካሬ ሜትር የሚሸፍን ስራ በጥራት እና በስፋት ተከናውኗል፡፡ ሁሉም ነገር በአዲስ መልኩ ነው የተሰራው፡፡ ለዚህ ስራ እውቀታቸውን የገለፁ፣ ክህሎታቸውን ያሳዩ፣ ልምዳቸውን ያጋራ ባለ አሻራዎች ብዙ መሆናቸውን ከአሰልጣኙ አንደበት ሰምተናል፡፡ ሰፊውን የሲቪል ስራ ኮንስትራክሽኖች፣ በሚያምር ውበት የኤሌክትሪክ ዝርጋታውን ኤሌክትሪክሲቲዎች፣ በሚስብ ዲዛይን የጥልፍ እና መጋረጃ ስራዎችን ጋርመንቶች፣ ማራኪ የእንጨት ስራዎችን ውድ ወርኮች፣ ውብ አደረጃጀቱን ሆቴሎች፣ ልዩ ልዩ የብረታብረት ምርቶችን ሜታል ወርኮች ወዘተ በመተባበር ሁሉም በባለቤትነት ስሜት አሻራቸውን እንዳስቀመጡ ታውቋል፡፡
ይህ ስራ የእንጨት፣ የብረት ብረት፣ የኤሌክትሪክ ግባዓቶችን ጨምሮ አጠቃላይ ወጪ ወደ 13.5 ሚሊዮን ብር ኢንቨስት እንደተደረገበትም ከአሰልጣኝ ሳሙኤል መረጃ አግኝተናል፡፡
ለሰራተኞች ምቹ መዝናኛ ክበብን ከማደስ ባሻገር የስራው ሂደት ያመጣው ፋይዳ ይኖር ይሆን የሚል የመሰናበቻ ጥያቄ ለአርትቴክተሩ አነሳን፡፡ ‹‹በዚህ ስራ ላይ የተካፈሉ ብዙዎች እርስ በእርሳቸው በሙያቸው ልምድ ልውውጥ አድርገዋል፣ ከማሰልጠን ባሻገር ያለውን ሙያዊ ብቃት አሳይተዋል እንዲሁም ለሰልጣኞቻቸው የተግባር ልምምድ እንዲያደርጉ ዕድል ፈጥሮላቸዋል የሚል ሀሳብ ሰጥተውናል፡፡
አሰልጣኝ ሳሙኤል ከዚህ ፕሮጀክት ውጪም ስማርት ክላስ መፍጠር የሚለውን ጽንሰ ሀሳብ ተጋርተው ለሁሉም ዲፓርመንቶች የተገጠሙ ኢንተራክቲቭ ቦርዶች እውን እንዲሆኑ ትግበራው ላይ የአንበሳውን ድርሻ ወስደዋል፡፡
በዚህ ድንቅ ውበት ተከሽኖ ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነውን መዝናኛ ክበብ በጥራት እና በተመጣጣኝ ዋጋ አገልግሎት እሰጣለሁ ብለው ጨረታውን ያሸነፉ ባለሀብት ዛሬ ስራቸውን በይፋ የጀመሩ ሲሆን የዛሬውን የምሳ መስተንግዶ ለሁሉም ሰራተኞች በባለ ሀብቱ ሙሉ ወጪ በግብዣ መልኩ እንደሚሸፈን ታውቋል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍9👎1
ሐሙስ:- መጋቢት 12 ቀን 2016 ዓ.ም
ስነምግባር
ስነምግባር ከቤተሰብ፣ ከጓደኛ፣ ከህብረተሰብ፣ ከተለያዩ ተቋማት /ለምሳል ከሃይማኖት እና ሌሎች/፣ ከህግ እና ፍትህ አካላት ወዘተ የሚመነጭ ሲሆን ስነ ምግባር ሰላምን ለማሰፈን፣ ሁሉም ሰው በእኩልነትና በመከባበር እንዲኖር ለማድረግ፣ የጋራ ተጠቃሚነትንና እድገትን ለማምጣት፣ ወዘተ ይጠቅማል፡፡
ስነ ምግባር ወሳኝ የሆኑ የህይወት መርሆዎችን በመከተል የሚኖር ሲሆን በመርህ ለመኖር ደግሞ ሁለንተናዊ የሆነ የሞራል ባህርይ መላበስ ያስፈልጋል፡፡
የኮሌጁ የስነምግባርና ጸረሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ስነምግባር
ስነምግባር ከቤተሰብ፣ ከጓደኛ፣ ከህብረተሰብ፣ ከተለያዩ ተቋማት /ለምሳል ከሃይማኖት እና ሌሎች/፣ ከህግ እና ፍትህ አካላት ወዘተ የሚመነጭ ሲሆን ስነ ምግባር ሰላምን ለማሰፈን፣ ሁሉም ሰው በእኩልነትና በመከባበር እንዲኖር ለማድረግ፣ የጋራ ተጠቃሚነትንና እድገትን ለማምጣት፣ ወዘተ ይጠቅማል፡፡
ስነ ምግባር ወሳኝ የሆኑ የህይወት መርሆዎችን በመከተል የሚኖር ሲሆን በመርህ ለመኖር ደግሞ ሁለንተናዊ የሆነ የሞራል ባህርይ መላበስ ያስፈልጋል፡፡
የኮሌጁ የስነምግባርና ጸረሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍1
ሐሙስ:- መጋቢት 12 ቀን 2016 ዓ.ም
ሁሉን አቀፍ ተቋማዊ የልማት ገጽታዎቻችን እንደ ቀጠሉ ናቸው!!
ኮሌጁ በዚህ በጀት ዓመት እጅግ በርካታ የስራ ስኬቶችን ያስመዘገበበት ጊዜ ሲሆን በርካታዎቹ ስራዎች ተጠናቀዋል፤ የተወሰኑት ጥቂት ጊዜን ይሻሉ አንዳንዶቹ ደግሞ እቅድ ተይዞላቸዋል፡፡
ተቋሙን ምቹ የስራ ከባቢ እና ለእይታ ሳቢ ለማድረግ እየተከወኑ ካሉ ዘረፈ ብዙ ትጋቶች መካከል ትልቁን ሚና የሚጋሩት የኮንስትራክሽን ዘርፍ አሰልጣኞች ናቸው፡፡ ስልጠና ዘርፉ በተለያዩ አሰልጣኞች ታቅደው እየተተገበሩ ያሉ በርካታ ፕሮጀክቶችን የያዘ ሲሆን በዚህ ምልከታችን በሁለት አሰልጣኞች እየተሰራ ያለን የውስጥ ለውስጥ መንገድ እና የአደባባይ ስራ በአጭር እንቃኛለን፡፡
በሁለት በኩል መተላለፊያ የሚሆኑ እና በቴራዞን ንጣፍ ለመስራት እቅድ የተያዘላቸውን የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ጨምሮ በልዩ ልዩ አበባዎችና ሳሮች እንዲያሸበርቁ ታልሞ እየተሰራ የሚገኝን መለስተኛ አደባባይ ለመስራት ሲታትሩ ሁለት የዘርፉን አሰልጣኞች በካሜራችን ዐይን ተመልክተናል፡፡
600 ካሬ ሜትር ገደማ በሚሸፍን ቦታ ላይ የመንገድ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን እየሰሩ ያሉ 2 አሰልጣኞች መርጋ አብዲሳ እና ገረመ ፍሪሳ ናቸው፡፡ አሰልጣኞቹ በኮሌጁ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን በመመልከት እነሱም የራሳቸውን አሻራ ለማኖር በማስብ ለመስራት መነሳታቸውን ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በግዢ ዳይሬክቶሬት ቢሮ አካባቢ የሚገኝ ሲሆን ከዚህ በፊት የነበረው ገጽታ ምቾትን የሚነሳ ነበር፡፡ ይህ ፕሮጀክት አሁን ላይ 80 ከመቶው መጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ አሰልጣኞቹ የገለፁ ሲሆን ከ20 ቀናት ባልበለጡ ጊዜያት ለማጠናቀቅ ማቀዳቸውን ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የአካባቢውን ውበት ማምጣት ብቻ ሳይሆን ኮሌጁን የሚገልጽ ልዩ ልዩ አስተማሪ ይዘት እና ቅርጽ እንዲኖረው ይደረጋልም ተብሏል፡፡ እኛም እንደሁል ጊዜው ብርቱ እጆች እና በጎ ተግባሮች ይቀጥሉ እያልን ቀጣይ በሌሎች ተመሳሳይ ቅኝቶች እስከምንመለስ ቸር ቆዩን፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ሁሉን አቀፍ ተቋማዊ የልማት ገጽታዎቻችን እንደ ቀጠሉ ናቸው!!
ኮሌጁ በዚህ በጀት ዓመት እጅግ በርካታ የስራ ስኬቶችን ያስመዘገበበት ጊዜ ሲሆን በርካታዎቹ ስራዎች ተጠናቀዋል፤ የተወሰኑት ጥቂት ጊዜን ይሻሉ አንዳንዶቹ ደግሞ እቅድ ተይዞላቸዋል፡፡
ተቋሙን ምቹ የስራ ከባቢ እና ለእይታ ሳቢ ለማድረግ እየተከወኑ ካሉ ዘረፈ ብዙ ትጋቶች መካከል ትልቁን ሚና የሚጋሩት የኮንስትራክሽን ዘርፍ አሰልጣኞች ናቸው፡፡ ስልጠና ዘርፉ በተለያዩ አሰልጣኞች ታቅደው እየተተገበሩ ያሉ በርካታ ፕሮጀክቶችን የያዘ ሲሆን በዚህ ምልከታችን በሁለት አሰልጣኞች እየተሰራ ያለን የውስጥ ለውስጥ መንገድ እና የአደባባይ ስራ በአጭር እንቃኛለን፡፡
በሁለት በኩል መተላለፊያ የሚሆኑ እና በቴራዞን ንጣፍ ለመስራት እቅድ የተያዘላቸውን የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ጨምሮ በልዩ ልዩ አበባዎችና ሳሮች እንዲያሸበርቁ ታልሞ እየተሰራ የሚገኝን መለስተኛ አደባባይ ለመስራት ሲታትሩ ሁለት የዘርፉን አሰልጣኞች በካሜራችን ዐይን ተመልክተናል፡፡
600 ካሬ ሜትር ገደማ በሚሸፍን ቦታ ላይ የመንገድ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን እየሰሩ ያሉ 2 አሰልጣኞች መርጋ አብዲሳ እና ገረመ ፍሪሳ ናቸው፡፡ አሰልጣኞቹ በኮሌጁ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን በመመልከት እነሱም የራሳቸውን አሻራ ለማኖር በማስብ ለመስራት መነሳታቸውን ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በግዢ ዳይሬክቶሬት ቢሮ አካባቢ የሚገኝ ሲሆን ከዚህ በፊት የነበረው ገጽታ ምቾትን የሚነሳ ነበር፡፡ ይህ ፕሮጀክት አሁን ላይ 80 ከመቶው መጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ አሰልጣኞቹ የገለፁ ሲሆን ከ20 ቀናት ባልበለጡ ጊዜያት ለማጠናቀቅ ማቀዳቸውን ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የአካባቢውን ውበት ማምጣት ብቻ ሳይሆን ኮሌጁን የሚገልጽ ልዩ ልዩ አስተማሪ ይዘት እና ቅርጽ እንዲኖረው ይደረጋልም ተብሏል፡፡ እኛም እንደሁል ጊዜው ብርቱ እጆች እና በጎ ተግባሮች ይቀጥሉ እያልን ቀጣይ በሌሎች ተመሳሳይ ቅኝቶች እስከምንመለስ ቸር ቆዩን፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍4❤1