አርብ:- መጋቢት 13 ቀን 2016 ዓ.ም
ለሬጅስትራር ጽ/ቤት ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ!!
ለኮሌጁ ሬጅስትራር ጽ/ቤት ባለሙያዎች በደንበኛ አያያዝ ዙሪያ ዛሬ መጋቢት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ስልጠና ተሰጠ፡፡
የደንበኞችን ፍላጎት መሰረት ያደረገ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ለጽ/ቤቱ ባለሙያዎች የተሰጠው ስልጠና በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ያሉ ፈታኝ ነገሮችን የሚያሳይ እና ማሻሻያ ስልቶችን የሚጠቁም ነው፡፡
ስልጠናውን ያዘጋጀው በስልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን ቢሮ ስር የጥናት፣ ምርምርና ፐብሊኬሽን የስራ ክፍል ሲሆን ሬጅስትራር ጽ/ቤት ከሰልጣኝ ቅብላ እስከ ስልጠና ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ስጦታ ድረስ ባለው ጌዜ ከደንበኞች ጋር ሰፊ እና ቀጥተኛ ግንኙነት ስላለው ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በመጠቀም እና የደንበኞችን ፍላጎት ያማከለ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማስቻል ታቅዶ መዘጋጀቱን ከስራ ክፍሉ አስተባባሪ ምስራቅ ደለሳ ማረጋገጥ ችለናል፡፡
አስተባባሪዋ አክለውም የጥናት፣ ምርምርና ፐብሊኬሽን የስራ ክፍል ተግባራዊ ጥናት እና ምርምር በማድረግ ክፍተቶች እንዲሞሉ ማድረግ ሲሆን ይህ ስልጠና እንዲሰጥ የተደረገውም በጥናቱ ግኝት መሰረት መስተካከል ካለባቸው ትግበራዎች አንዱ ስለሆነ ነው ብለዋል፡፡ ስልጠናው የተሰጠው ደግሞ በሄኖክ አብርሃም ነው፡፡
የኮሌጁ ደንበኞች የመጀመሪዎቹ ሰልጣኞች ናቸው፤ ሁለተኛዎቹም ሰልጣኞች ናቸው፤ ሶስተኛ እና አራተኛም እነሱ ስለሆነም በሁሉም የስራ እንቅስቃሴ ሰልጣኝ ተኮር ስራዎችን መስራት የሁል ጊዜ ተቀዳሚ ትኩረታችን ነው፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ለሬጅስትራር ጽ/ቤት ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ!!
ለኮሌጁ ሬጅስትራር ጽ/ቤት ባለሙያዎች በደንበኛ አያያዝ ዙሪያ ዛሬ መጋቢት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ስልጠና ተሰጠ፡፡
የደንበኞችን ፍላጎት መሰረት ያደረገ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ለጽ/ቤቱ ባለሙያዎች የተሰጠው ስልጠና በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ያሉ ፈታኝ ነገሮችን የሚያሳይ እና ማሻሻያ ስልቶችን የሚጠቁም ነው፡፡
ስልጠናውን ያዘጋጀው በስልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን ቢሮ ስር የጥናት፣ ምርምርና ፐብሊኬሽን የስራ ክፍል ሲሆን ሬጅስትራር ጽ/ቤት ከሰልጣኝ ቅብላ እስከ ስልጠና ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ስጦታ ድረስ ባለው ጌዜ ከደንበኞች ጋር ሰፊ እና ቀጥተኛ ግንኙነት ስላለው ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በመጠቀም እና የደንበኞችን ፍላጎት ያማከለ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማስቻል ታቅዶ መዘጋጀቱን ከስራ ክፍሉ አስተባባሪ ምስራቅ ደለሳ ማረጋገጥ ችለናል፡፡
አስተባባሪዋ አክለውም የጥናት፣ ምርምርና ፐብሊኬሽን የስራ ክፍል ተግባራዊ ጥናት እና ምርምር በማድረግ ክፍተቶች እንዲሞሉ ማድረግ ሲሆን ይህ ስልጠና እንዲሰጥ የተደረገውም በጥናቱ ግኝት መሰረት መስተካከል ካለባቸው ትግበራዎች አንዱ ስለሆነ ነው ብለዋል፡፡ ስልጠናው የተሰጠው ደግሞ በሄኖክ አብርሃም ነው፡፡
የኮሌጁ ደንበኞች የመጀመሪዎቹ ሰልጣኞች ናቸው፤ ሁለተኛዎቹም ሰልጣኞች ናቸው፤ ሶስተኛ እና አራተኛም እነሱ ስለሆነም በሁሉም የስራ እንቅስቃሴ ሰልጣኝ ተኮር ስራዎችን መስራት የሁል ጊዜ ተቀዳሚ ትኩረታችን ነው፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍16❤3
ማክሰኞ:- መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለኮሌጁ ሰልጣኞች በሙሉ
የኮሌጁ የስነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት በስነምግባር ምንነትና አስፈላጊነት፤ በሰልጣኞች የስነምግባር ክበብ ምንነትና ጥቅም እንዲሁም ብልሹ አሰራር ከተማሪዎች የስልጠና አሰጣጥ አንጻር ያለውን ትርጉም በተመለከተ ለ2 ቀናት ስልጠና አዘጋጅተናል፡፡
በመሆኑም ከመጋቢት 18 – 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 7፡30 ---- 11፡00 ሰዓት ለ2 ተከታታይ ቀናት አስተዳደር ህንፃ 4ኛው ፎቅ ላይ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ስልጠናው ስለሚሰጥ በዕለቱ እና በሰዓቱ እንድትገኙ እናሳውቃለን ፡፡
የኮሌጁ የስነምግባርና ጸረሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት
ማስታወቂያ
ለኮሌጁ ሰልጣኞች በሙሉ
የኮሌጁ የስነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት በስነምግባር ምንነትና አስፈላጊነት፤ በሰልጣኞች የስነምግባር ክበብ ምንነትና ጥቅም እንዲሁም ብልሹ አሰራር ከተማሪዎች የስልጠና አሰጣጥ አንጻር ያለውን ትርጉም በተመለከተ ለ2 ቀናት ስልጠና አዘጋጅተናል፡፡
በመሆኑም ከመጋቢት 18 – 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 7፡30 ---- 11፡00 ሰዓት ለ2 ተከታታይ ቀናት አስተዳደር ህንፃ 4ኛው ፎቅ ላይ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ስልጠናው ስለሚሰጥ በዕለቱ እና በሰዓቱ እንድትገኙ እናሳውቃለን ፡፡
የኮሌጁ የስነምግባርና ጸረሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት
👍1
ማክሰኞ:- መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም
በሰልጣኞች መካከል ሲደረግ የቆየው የእግር ኳስ ዋንጫ ጨዋታ በኮንስራክሽን ቴክኖሎጂ ዲፓርትመንት አሸናፊነት ተጠናቀቀ!!
በኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ /ፊኒሽንግ/ እና ኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ /ICT/ ዲፓርትመንቶች መካከል በተደረገ የሰልጣኞች የእግር ኳስ ፍፃሜ ጨዋታ የኮንስትራክሽን ዘርፉ ሰልጣኞች ዋንጫውን አሸነፉ፡፡
ከየካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከተለያዩ ዲፓርትመንቶች የተውጣጡ 14 ቡድኖች ሲጫወቱ ቆይተው ለፍፃሜ የደረሱት ሁለቱ ቡድኖች ዛሬ መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም ከፍተኛ ፉክክር በታየበት አጓጊ ውድድር ተጫውተው ድል ለኮንስትራክሽን ሰልጣኞች ቀርባለች፡፡
ጨዋታው ምንም እንኳን 3 እኩል ሜዳ ላይ ቢጠናቀቅም መጨረሻ ላይ በተሰጠው የፍፁም ቅጣት ምት የኮንስትራክሽን /ፊኒሽንግ/ ዲፓርትመንት ግብ ጠባቂ አንድ ጎል በመከላከሉ በፍፁም ቅጣት ምቱ 5ለ4 በሆነ ትልቅ ትንቅንቅ ጨዋታው ተጠናቋል፡፡
በውድድሩ አሸናፊ ለሆኑት የዲፓርንመንቱ ሰልጣኞች የዋንጫ እና የገንዘብ ሸልማት የተበረከተላቸው ሲሆን ሽልማቱም በኮሌጁ ዋና ዲን በአቶ መለሰ ይግዛው አማካኝነት ተሰጥቷቸዋል፡፡
የእግር ኳስ ውድድሩ የተዘጋጀው በኮሌጁ ሰልጣኝ መማክርት አማካኝነት እንደሆነ እና ዓላማውም በሰልጣኞች መካከል የመተባበር እና የውድድር መንፈስን ለማሳደግ ታቅዶ እንደተዘጋጀ የመማክርቱ ም/ሰብሳቢ ሰልጣኝ ኤልያስ ሙልጌታ ነግሮናል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
በሰልጣኞች መካከል ሲደረግ የቆየው የእግር ኳስ ዋንጫ ጨዋታ በኮንስራክሽን ቴክኖሎጂ ዲፓርትመንት አሸናፊነት ተጠናቀቀ!!
በኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ /ፊኒሽንግ/ እና ኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ /ICT/ ዲፓርትመንቶች መካከል በተደረገ የሰልጣኞች የእግር ኳስ ፍፃሜ ጨዋታ የኮንስትራክሽን ዘርፉ ሰልጣኞች ዋንጫውን አሸነፉ፡፡
ከየካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከተለያዩ ዲፓርትመንቶች የተውጣጡ 14 ቡድኖች ሲጫወቱ ቆይተው ለፍፃሜ የደረሱት ሁለቱ ቡድኖች ዛሬ መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም ከፍተኛ ፉክክር በታየበት አጓጊ ውድድር ተጫውተው ድል ለኮንስትራክሽን ሰልጣኞች ቀርባለች፡፡
ጨዋታው ምንም እንኳን 3 እኩል ሜዳ ላይ ቢጠናቀቅም መጨረሻ ላይ በተሰጠው የፍፁም ቅጣት ምት የኮንስትራክሽን /ፊኒሽንግ/ ዲፓርትመንት ግብ ጠባቂ አንድ ጎል በመከላከሉ በፍፁም ቅጣት ምቱ 5ለ4 በሆነ ትልቅ ትንቅንቅ ጨዋታው ተጠናቋል፡፡
በውድድሩ አሸናፊ ለሆኑት የዲፓርንመንቱ ሰልጣኞች የዋንጫ እና የገንዘብ ሸልማት የተበረከተላቸው ሲሆን ሽልማቱም በኮሌጁ ዋና ዲን በአቶ መለሰ ይግዛው አማካኝነት ተሰጥቷቸዋል፡፡
የእግር ኳስ ውድድሩ የተዘጋጀው በኮሌጁ ሰልጣኝ መማክርት አማካኝነት እንደሆነ እና ዓላማውም በሰልጣኞች መካከል የመተባበር እና የውድድር መንፈስን ለማሳደግ ታቅዶ እንደተዘጋጀ የመማክርቱ ም/ሰብሳቢ ሰልጣኝ ኤልያስ ሙልጌታ ነግሮናል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍16😢4🏆1
ረቡዕ:- መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም
ለ14ኛው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት በቂ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ!!
ዘንድሮ ለ14ኛ ጊዜ ለሚከበረው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት በተለያዩ ዘርፎች ተወዳድሮ አሸናፊ ለመሆን የሚያስችል በቂ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ፡፡
4 የማምረቻ፣ 5 የምርት እና 1 የአገር በቀል ቴክኖሎጂዎችን በማምረት እንዲሁም አሰልጣኞች በ14 ሙያዎች፣ ሰልጣኞች በ9 ዘርፎች እና ኢንተርፕራይዞች ደግሞ 5 በሚሆኑ የሙያ መስኮች የክህሎት ውድድር ለማድረግ እቅድ መያዙን ከቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን አቶ ደሜ መርሻ ሰምተናል፡፡
ምክትል ዲኑ አክለውም የዘንድሮው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች፣ የፋሽን ሾው ትርኢቶች፣ የICT ዘርፍ ፈጠራዎችና መሰል ስራዎች የበዓሉ ዝግጅት አካል ናቸው፡፡ ብለዋል፡፡
እንደ ተቋም 7 የሚሆኑ ችግር ፈቺ ተግባራዊ የጥናት እና ምርምር ስራዎች እየተጋጁ ሲሆን ቀጣይ መጋቢት 27 ቀን 20 16 ዓ.ም ደግሞ በኮሌጅ ደረጃ የክህሎት ውድድር እንደሚጀመር ታውቋል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ለ14ኛው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት በቂ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ!!
ዘንድሮ ለ14ኛ ጊዜ ለሚከበረው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት በተለያዩ ዘርፎች ተወዳድሮ አሸናፊ ለመሆን የሚያስችል በቂ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ፡፡
4 የማምረቻ፣ 5 የምርት እና 1 የአገር በቀል ቴክኖሎጂዎችን በማምረት እንዲሁም አሰልጣኞች በ14 ሙያዎች፣ ሰልጣኞች በ9 ዘርፎች እና ኢንተርፕራይዞች ደግሞ 5 በሚሆኑ የሙያ መስኮች የክህሎት ውድድር ለማድረግ እቅድ መያዙን ከቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን አቶ ደሜ መርሻ ሰምተናል፡፡
ምክትል ዲኑ አክለውም የዘንድሮው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች፣ የፋሽን ሾው ትርኢቶች፣ የICT ዘርፍ ፈጠራዎችና መሰል ስራዎች የበዓሉ ዝግጅት አካል ናቸው፡፡ ብለዋል፡፡
እንደ ተቋም 7 የሚሆኑ ችግር ፈቺ ተግባራዊ የጥናት እና ምርምር ስራዎች እየተጋጁ ሲሆን ቀጣይ መጋቢት 27 ቀን 20 16 ዓ.ም ደግሞ በኮሌጅ ደረጃ የክህሎት ውድድር እንደሚጀመር ታውቋል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍9
ረቡዕ:- መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም
የኮሌጁ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የንብረት አያያዜን ከማኑዋል ወደ ዲጅታል ላሸጋግር ነው አለ!!
ዳይሬክቶሬቱ ይህንን ያሳወቀው እንደ ከተማ አስተዳደር የለማውን ዘመናዊ የንበረት አስተዳደር ሶፍትዌር አጠቃቀም ለሚመለከታቸው የዳይሬክቶሬቱ እና የመንግስት ህንፃ አስተዳደር እና አገልግሎት ጽ/ቤት ባለሙያዎች ስልጠናዎችን እየሰጠ ባለበት ጊዜ ነው፡፡
በዚህ ስልጠና ላይ 16 ባለሙያዎች እየተሳተፉ የሚገኝ ሲሆን ከንብረት ጋር የተያያዙ ጽንሰ ሀሳባዊ ገለፃ ከመሰጠቱ ባሻገር መሰረታዊ የኮምፒውተር አጠቃቀም እና አጠቃላይ በለማው ሶፍትዊር ዙሪያ ተግባራዊ የክህሎት ስልጠና በኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ /ICT/ ዲፓርትመንት አሰልጣኞች እየተሰጠ ይገኛል፡፡
የተቋሙን ንብረት በቀላሉ ለመቆጣጠር፣ አሰራሩን ለማዘመን እና የንብረት አጠቃቀምን ፍትሐዊነት ለማምጣት ያስችል ዘንድ ተግባራዊ ለማድረግ የታቀደው ዲጅታላይዜሽን ስርዓት ስልጠናው እንደተጠናቀቀ ወደ ስራ ይገባል ያሉን የኮሌጁ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ጨመዳ ናቸው፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም ስርዓቱ የንብረት ብክነትን እና የተንዛዛ አሰራርን ያስቀራል ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን እና የከተማ አስተዳደሩ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ለዚህ ተግባር የለማው ሶፍትዌር በሁሉም የመንግስት ተቋማት ይተገበር ዘንድ ከዘርፉ ለተውጣጡ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና እንደሰጠ መዘገባችን አይዘነጋም፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
የኮሌጁ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የንብረት አያያዜን ከማኑዋል ወደ ዲጅታል ላሸጋግር ነው አለ!!
ዳይሬክቶሬቱ ይህንን ያሳወቀው እንደ ከተማ አስተዳደር የለማውን ዘመናዊ የንበረት አስተዳደር ሶፍትዌር አጠቃቀም ለሚመለከታቸው የዳይሬክቶሬቱ እና የመንግስት ህንፃ አስተዳደር እና አገልግሎት ጽ/ቤት ባለሙያዎች ስልጠናዎችን እየሰጠ ባለበት ጊዜ ነው፡፡
በዚህ ስልጠና ላይ 16 ባለሙያዎች እየተሳተፉ የሚገኝ ሲሆን ከንብረት ጋር የተያያዙ ጽንሰ ሀሳባዊ ገለፃ ከመሰጠቱ ባሻገር መሰረታዊ የኮምፒውተር አጠቃቀም እና አጠቃላይ በለማው ሶፍትዊር ዙሪያ ተግባራዊ የክህሎት ስልጠና በኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ /ICT/ ዲፓርትመንት አሰልጣኞች እየተሰጠ ይገኛል፡፡
የተቋሙን ንብረት በቀላሉ ለመቆጣጠር፣ አሰራሩን ለማዘመን እና የንብረት አጠቃቀምን ፍትሐዊነት ለማምጣት ያስችል ዘንድ ተግባራዊ ለማድረግ የታቀደው ዲጅታላይዜሽን ስርዓት ስልጠናው እንደተጠናቀቀ ወደ ስራ ይገባል ያሉን የኮሌጁ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ጨመዳ ናቸው፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም ስርዓቱ የንብረት ብክነትን እና የተንዛዛ አሰራርን ያስቀራል ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን እና የከተማ አስተዳደሩ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ለዚህ ተግባር የለማው ሶፍትዌር በሁሉም የመንግስት ተቋማት ይተገበር ዘንድ ከዘርፉ ለተውጣጡ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና እንደሰጠ መዘገባችን አይዘነጋም፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍7❤3