ማክሰኞ፡- የካቲት 26 ቀን 2016 ዓ.ም
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8ን ምክኒያት በማድረግ የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ሴት ሰልጣኞች የታብሌት ሽልማት ተበረከተላቸው!!
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8ን ምክኒያት በማድረግ ከሁሉም ዲፓርትመንቶች የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ 41 ሴት የኮሌጃችን ሰልጣኞች ዛሬ የካቲት 26 ቀን 2016 ዓ.ም የታብሌት ሽልማት ተበረከተላቸው፡፡
በኢትዮጵያ ለ48ኛ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ113 ጊዜ የሚከበረው ማርች 8 የሴቶች ቀን በኮሌጃችን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የመጡ ባለሙያዎች፣ የኮሌጁ ዲኖች፣ ሰራተኞች እና ሰልጣኞች ተገኝተዋል፡፡
መርሃ ግብሩ በአደባባይ ፌስቲቫል እና አዳራሽ ውስጥ በተደረገ አውደ ጥናት የተካሄደ ሲሆን መድረኩን ያዘጋጀው የኮሌጁ ስርዓተ ፆታ ተወካዮች ከሰልጣኝ መማክርት አባላት ጋር በመተባበር ነው ተብሏል፡፡
አደዋ ለጥቁር ህዝቦች የነፃነት ጮራን የፈነጠቀ ሲሆን ማርች 8 ደግሞ የሴቶች እኩልነትን ለማረጋገጥ የተደረገ ታሪካዊ ቀን ነው፡፡ ስለሆነም ዛሬ እያከበርን ያለነው ሁለቱ በዓላት የፍትህ ጥያቄዎችን ለማስመለስ የተደረጉ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ በዓላት ናቸው ያሉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ናቸው፡፡
በሌላ በኩል ሴት እህት፣ ሴት እናት፣ ሴት ልጅ እና ሴት ሚስት በመሆን የዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ኃላፊነት የምትሸከም ብትሆንም በተለያዩ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ፣ ባህላዊ እና ፖለቲካዊ ጫናዎች ሲደርስባቸው ቆይቷል፡፡ ስለሆነም አሁን ላይ ማርች 8ን ስናከብር ሴቶች እንደማንኛውም ሰብአዊ ዜጋ መብታቸው እንዲከበርና እንክብካቤን እንዲደረግላቸው ሁላችንም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል በማለት የተናገሩት ደግሞ የኮሌጁ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ አድማሱ በቀለ ናቸው፡፡
ማርች 8 እንደ ጎርጎሮሳዊያን የዘመን ቀመር 1908 ላይ በአሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ ነዋሪ የሆኑ 15,000 ሴቶች የተሻሻለ የሥራ ሰዓት እንዲኖር፣ የደመወዝ ክፍያ እኩልነት እንዲፈጠር እና የመምረጥ መብታቸው እንዲከበር ለጥያቄ አደባባይ የወጡበት ቀን ሲሆን በ1975 ዓ.ም ደግሞ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሴቶች ቀንን በዓለም አቀፍ ደረጃ በይፋ እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8ን ምክኒያት በማድረግ የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ሴት ሰልጣኞች የታብሌት ሽልማት ተበረከተላቸው!!
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8ን ምክኒያት በማድረግ ከሁሉም ዲፓርትመንቶች የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ 41 ሴት የኮሌጃችን ሰልጣኞች ዛሬ የካቲት 26 ቀን 2016 ዓ.ም የታብሌት ሽልማት ተበረከተላቸው፡፡
በኢትዮጵያ ለ48ኛ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ113 ጊዜ የሚከበረው ማርች 8 የሴቶች ቀን በኮሌጃችን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የመጡ ባለሙያዎች፣ የኮሌጁ ዲኖች፣ ሰራተኞች እና ሰልጣኞች ተገኝተዋል፡፡
መርሃ ግብሩ በአደባባይ ፌስቲቫል እና አዳራሽ ውስጥ በተደረገ አውደ ጥናት የተካሄደ ሲሆን መድረኩን ያዘጋጀው የኮሌጁ ስርዓተ ፆታ ተወካዮች ከሰልጣኝ መማክርት አባላት ጋር በመተባበር ነው ተብሏል፡፡
አደዋ ለጥቁር ህዝቦች የነፃነት ጮራን የፈነጠቀ ሲሆን ማርች 8 ደግሞ የሴቶች እኩልነትን ለማረጋገጥ የተደረገ ታሪካዊ ቀን ነው፡፡ ስለሆነም ዛሬ እያከበርን ያለነው ሁለቱ በዓላት የፍትህ ጥያቄዎችን ለማስመለስ የተደረጉ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ በዓላት ናቸው ያሉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ናቸው፡፡
በሌላ በኩል ሴት እህት፣ ሴት እናት፣ ሴት ልጅ እና ሴት ሚስት በመሆን የዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ኃላፊነት የምትሸከም ብትሆንም በተለያዩ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ፣ ባህላዊ እና ፖለቲካዊ ጫናዎች ሲደርስባቸው ቆይቷል፡፡ ስለሆነም አሁን ላይ ማርች 8ን ስናከብር ሴቶች እንደማንኛውም ሰብአዊ ዜጋ መብታቸው እንዲከበርና እንክብካቤን እንዲደረግላቸው ሁላችንም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል በማለት የተናገሩት ደግሞ የኮሌጁ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ አድማሱ በቀለ ናቸው፡፡
ማርች 8 እንደ ጎርጎሮሳዊያን የዘመን ቀመር 1908 ላይ በአሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ ነዋሪ የሆኑ 15,000 ሴቶች የተሻሻለ የሥራ ሰዓት እንዲኖር፣ የደመወዝ ክፍያ እኩልነት እንዲፈጠር እና የመምረጥ መብታቸው እንዲከበር ለጥያቄ አደባባይ የወጡበት ቀን ሲሆን በ1975 ዓ.ም ደግሞ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሴቶች ቀንን በዓለም አቀፍ ደረጃ በይፋ እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍13
አርብ፡- የካቲት 29 ቀን 2016 ዓ.ም
ዛሬ ማርች 8 ነው!!
ዛሬ ማርች 8 የሴቶች ቀን በኢትዮጵያ ለ48ኛ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ113 ጊዜ የሚከበር ሲሆን ማርች /መጋቢት/ 8 እንደ ጎርጎሮሳዊያን የዘመን ቀመር 1908 ላይ ኗሪነታቸው በአሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ የሆኑና በተለይ ደግሞ በጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎች ሰራተኞች የነበሩ 15,000 ሴቶች በአደባባይ ወጥተው የሥራ ሰዓት እንዲሻሻል /እንዲያጥር/፣ የደመወዝ ክፍያ እኩልነት እንዲፈጠር እና የመምረጥ መብታቸው እንዲከበር ለጥያቄ የወጡበት ታሪካዊ ቀን ነው፡፡ ከዚያም ከአንድ ዓመት በኋላ የአሜሪካ ሶሻሊስት ፓርቱ የመጀመሪያውን ብሔራዊ የሴቶች ቀን አወጀ። በ1975 ዓ.ም ደግሞ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሴቶች ቀንን ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ በይፋ እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
ኮሌጃችንም የሴቶችን ቀን ምክኒያት በማድረግ ሰሞኑን በርካታ ማህበራዊ አገልግሎቶችን በትጋት እየተውጣ ይገኛል፡፡ ካከናውናቸው ተጓዳኝ ተግባራት መካከል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በአቃቂ ቀሊቲ ላስገነባው የሴቶች ተሀዲሶና ክህሎት ማሰልጠኛ ማዕከል ለቤተ መጽሕፍት አገልግሎት 116 ሸልፎች፣ ጠረንጴዛዎች እና ወንበሮች እንዲሁም ለሳኒተሪ እና ለቢውልዲንግ ኤሌክትሪካል ኢንስታሌሽን የተግባር ስልጠና መስጫ ወርክሾፖች አጠቃላይ የሌይአውት ስራ በማከናወን ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ስራ ሰርቷል፡፡ በዚህም የውድ ወርክ፣ የሜታል ማኑፋክቸሪንግ፣ የኤሌክትሪክ ኤሌክትሮኒክ እና የኮንስትራክሽን ዲፓርትመንቶች አሰልጣኞች የአንበሳውን ድርሻ ተወጥተዋል።
ከዚህ ባሻገር በዚሁ ሳምንት 41 ለሚሆኑ የኮሌጁ ሴት ሰልጣኞች የታብሌት ስጦታ ያበረከተውም ይህንኑ ቀን ታሳቢ በማድረግ መሆኑ አይዘነጋም፡፡
ምናልባት ማርች 8 የሴቶች ቀንን ስናከበር የወንዶችስ ቀን አይከበርም ወይ የሚል ጥያቄ ከተነሳ መልሱ ዓለም አቀፍ የወንዶች ቀን የሚከበረው ኖቬምበር (ኅዳር) 19 ሲሆን ከ1990ዎቹ ጀምሮ ከ80 በላይ በሚሆኑ ሀገራት ይከበራል ይሁን እንጂ እስከ አሁን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዕውቅና አልተቸረውም፡፡
በመጨረሻም ለኮሌጃችን ሴት ሰራተኞች እና ሰልጣኞች ለማርች 8 እንኳን አደረሳችሁ እያልን መልካም የስኬት ጊዜ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ዛሬ ማርች 8 ነው!!
ዛሬ ማርች 8 የሴቶች ቀን በኢትዮጵያ ለ48ኛ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ113 ጊዜ የሚከበር ሲሆን ማርች /መጋቢት/ 8 እንደ ጎርጎሮሳዊያን የዘመን ቀመር 1908 ላይ ኗሪነታቸው በአሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ የሆኑና በተለይ ደግሞ በጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎች ሰራተኞች የነበሩ 15,000 ሴቶች በአደባባይ ወጥተው የሥራ ሰዓት እንዲሻሻል /እንዲያጥር/፣ የደመወዝ ክፍያ እኩልነት እንዲፈጠር እና የመምረጥ መብታቸው እንዲከበር ለጥያቄ የወጡበት ታሪካዊ ቀን ነው፡፡ ከዚያም ከአንድ ዓመት በኋላ የአሜሪካ ሶሻሊስት ፓርቱ የመጀመሪያውን ብሔራዊ የሴቶች ቀን አወጀ። በ1975 ዓ.ም ደግሞ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሴቶች ቀንን ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ በይፋ እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
ኮሌጃችንም የሴቶችን ቀን ምክኒያት በማድረግ ሰሞኑን በርካታ ማህበራዊ አገልግሎቶችን በትጋት እየተውጣ ይገኛል፡፡ ካከናውናቸው ተጓዳኝ ተግባራት መካከል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በአቃቂ ቀሊቲ ላስገነባው የሴቶች ተሀዲሶና ክህሎት ማሰልጠኛ ማዕከል ለቤተ መጽሕፍት አገልግሎት 116 ሸልፎች፣ ጠረንጴዛዎች እና ወንበሮች እንዲሁም ለሳኒተሪ እና ለቢውልዲንግ ኤሌክትሪካል ኢንስታሌሽን የተግባር ስልጠና መስጫ ወርክሾፖች አጠቃላይ የሌይአውት ስራ በማከናወን ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ስራ ሰርቷል፡፡ በዚህም የውድ ወርክ፣ የሜታል ማኑፋክቸሪንግ፣ የኤሌክትሪክ ኤሌክትሮኒክ እና የኮንስትራክሽን ዲፓርትመንቶች አሰልጣኞች የአንበሳውን ድርሻ ተወጥተዋል።
ከዚህ ባሻገር በዚሁ ሳምንት 41 ለሚሆኑ የኮሌጁ ሴት ሰልጣኞች የታብሌት ስጦታ ያበረከተውም ይህንኑ ቀን ታሳቢ በማድረግ መሆኑ አይዘነጋም፡፡
ምናልባት ማርች 8 የሴቶች ቀንን ስናከበር የወንዶችስ ቀን አይከበርም ወይ የሚል ጥያቄ ከተነሳ መልሱ ዓለም አቀፍ የወንዶች ቀን የሚከበረው ኖቬምበር (ኅዳር) 19 ሲሆን ከ1990ዎቹ ጀምሮ ከ80 በላይ በሚሆኑ ሀገራት ይከበራል ይሁን እንጂ እስከ አሁን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዕውቅና አልተቸረውም፡፡
በመጨረሻም ለኮሌጃችን ሴት ሰራተኞች እና ሰልጣኞች ለማርች 8 እንኳን አደረሳችሁ እያልን መልካም የስኬት ጊዜ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
❤3👍2🏆2