General Wingate Polytechnic college-Official channel
9.95K subscribers
3.37K photos
43 videos
204 files
198 links
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን።

የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።
Download Telegram
ጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰልጣኝ የነበረው የቤካም ሌንጂሶ የመታሰብያ የሻማ ማብራት ፕሮግራም የኮሌጁ አመራሮች፣አሰልጣኞች፣ አስተዳደር ሰራተኞች እና ሰልጣኞች እንዲሁም የቀድሞ ጓደኞቹ በተገኙበት ተካሄደ።
😢65👍8🙏53
ረቡዕ:- የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም

የኮሌጁ ዲኖች እና የተለያዩ ባለሙያዎች የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኙ!!

የኮሌጁ ዲኖች እና የተለያዩ ባለሙያዎች ዛሬ የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ተገኝተው ጉብኝት አደረጉ፡፡

በኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው የተመራ ልዑክ ኢንስቲትዩቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ዘርፍ የሰራቸውን እና እየሰራቸው ያሉ አስደናቂ ተግባራትን ተመልክቷል፡፡ በጉብኝቱ ተቋሙ በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርና፣ በፋናንስ አገልግሎት፣ በአየር ንብረት፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በሰላምና ደህንነት፣ በሮቦቲክስ፣ በተፈጥሮ ቋንቋ ቅንብር እና መሰል ዘርፎች ላይ ያከናውናቸውን ስራዎች ማየት ተችሏል፡፡

ኮሌጁ የዲጂታል ሲስተምን ተጠቅሞ ከትውልዱ ፍላጎት እና ከቴክኖሎጂው ዕድገት ጋር የተቀናጀ ስልጠና ለመስጠት ያስችለው ዘንድ ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የትብብር ሰነድ እያዘጋጀ ሲሆን ይህም በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመሆን የሰነቀውን ራዕይ ለማሳካት አንዱ አጋዥ መንገድ እንደሚሆነው ተገልጿል፡፡

ቀጣይ ከኢንስቲትዩቱ ጋር በሚደረገው ስምምነት ኮሌጁ በዲጅታላይዜሽን ላይ እየሰራ ያለውን ዘርፈ ብዙ ትግበራ የበለጠ ለማስፋት እና ለማዘመን አቅም ይፈጥርለታልም ተብሏል፡፡

"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍163👎3
ሐሙስ:- የካቲት 14 ቀን 2016 ዓ.ም

የኮሌጁ ሆቴልና ሆስፒታሊቲ ማሰልጠኛ አዲሱ ህንፃን ስራ ለማስጀመር ርክክብ ተደረገ!!

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሆቴልና ሆስፒታሊቲ ማሰልጠኛ አዲሱን ህንፃ ስራ ለማስጀመር ከየካቲት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ርክክብ ተደረገ፡፡

የሆቴል እና ሆስፒሊት ዲፓርትመንትን ስልጠና አንድ ምዕራፍ የሚያሻግር ነው የተባለለት አዲስ ህንፃ ባለ አራት ወለል ሲሆን ለሆቴል አገልግሎት የሚያገለግሉ ግብዓት እንዲሟላለት ተደርጓል።

በቅርቡ ስራ እንደሚጀምር እቅድ የተያዘለት የሆቴል እና ሆስፒታሊቲ ስልጠና ክፍል ማሰልጠኛ ህንፃ ዲፓርትመንቱ ለተግባር ልምምድ ወደ ተለያዩ ሆቴሎች የሚያደርገውን ደጅ ጥናት የሚያስቀር ወይም የሚቀንስ ሲሆን ለኮሌጁ ማህበረሰብ እና ለውጭ አገልግሎት ፈላጊዎች ደግሞ የሆቴል አገልግሎት የሚያገኙበት ነው።

ህንፃው በውስጡ መሠረታዊ የሆቴል አገልግሎትን የሚሰጡ ክፍሎች የተሟሉለት ሲሆን ሆቴሉ ስራ ሲጀምር ከስልጠና ባሻገር የኮሌጁን የውስጥ ገቢ በማሳደግ ረገድ ትልቅ ተስፋ ተጥሎበታል።

"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍17🏆32
Forwarded from fikir
👍1
Forwarded from AB 🌍 K-Raj
ኢንስቲትዩቱ ከቴክኒክና ሙያ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጋር በቅርበት እንዲሰራ ጥያቄ ቀረበ፡፡

ከጄነራል ዊንጌት ፓሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ የተውጣጡ አመራሮችና ሰራተኞች ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ መስራት በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ውይይት አደረጉ፡፡

በውይይቱ ወቅት በኢንስቲትዩቱ ስለበለፀጉ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የቴክኖሎጂ ውጤቶችና የስራ እንቅስቃሴ ዙሪያ በኢንስቲትዩቱ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ዘውዴ ማብራሪያ ቀርቧል፡፡

ኢንስቲትዩቱ ከቴክኒክና ሙያ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጋር በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂ ልማት እና ተያያዥ መስኮች በጋራ መስራት በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል፡፡

በተጨሪም ኢንስቲትዩቱ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች የሚያቋቁማቸውን የኤ.አይ ክበባት በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎች ብሎም በኮሌጆች ደረጃ ማስፋፋት ስለሚቻልባቸው መንገዶች ሀሳብ ቀርቧል፡፡

የውይይቱ ተካፋይ አካላት በኢንስቲትዩቱ የተመለከቱት የቴክኖሎጂ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆኑን በመግለፅ ሊበረታታ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
👍7👎3
Forwarded from fikir
👎12👍8
ማክሰኞ፡- የካቲት 19 ቀን 2016 ዓ.ም

የEASTRIP ፕሮጀክት ሁለት ዓመት ተጨማሪ ቆይታ እንዲኖረው ተወሰነ!!

በኮሌጁ የEASTRIP ፕሮጀክት ትግበራ ሁለት ዓመት ተጨማሪ የጊዜ ቆይታ እና የገንዘብ ጭማሪ እንዲኖረው ተወሰነ፡፡

የጊዜ እና የበጀት ጭማሪው ብስራት ይፋ የሆነው በሀገር አቀፍ ደረጃ የEASTRIP ፕሮጀክት ከሚተገበርባቸው ኮሌጆች የተውጣጡ የፕሮጀክት ጽ/ቤት ባለሙያዎች፣ የኮሌጅ ኃላፊዎች እና የወርልድ ባንክ ተወካዮች ዛሬ የካቲት 19 ቀን 2016 ዓ.ም በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባደረጉት የስራ ግምገማ ላይ ነው፡፡ ይህም የበጀት እና የጊዜ ቆይታ ጭማሪ ስራዎችን በጥራት እና በተቀላጠፈ መንገድ ለማጠናቀቅ እድል ይፈጥራል ተብሏል፡፡

በዕለቱ የምስራቅ አፍሪካ እና የኢትዮጵያ EASTRIP ፕሮጀክት ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ በዓለም ባንክ የፕሮጀክቱ ተጠሪዎች፣ በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የዘርፉ ተወካዮች፣ እንደ ሀገር ፕሮጀክቱ የሚተገበርባቸው ኮሌጆች ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ተገኝተዋል፡፡

ዛሬ በተዘጋጀው መድረክ በየኮሌጆቹ ያለው የፕሮጀክት አፈፃፀም ግምገማ ውይይት፣ በፕሮጀክቱ የቀጣይ ጊዜ እቅድ ዝግጅት እንዲሁም በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በፕሮጀክቱ የተጀመረው የኮንስትራክሽን ስራ ሂደት ምልከታ ተደርጓል፡፡

የEASTRIP ፕሮጀክት በኢነርጂ ዘርፍ የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን በ5 ዓመት የፕሮጀክት ትግበራ ቆይታ በምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማዕከል ለማድረግ ከዓለም ባንክ 14.85 ሚሊዮን ዶላር ይዞ በመምጣት በርካታ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡

"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍152🙏1