ሰኞ፡- ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም
ኮሌጁ ከትራንዚሽን ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ጋር አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ!!
ኮሌጁ የተለያዩ የሞባይል ዓይነቶች እና የሞባይል አክሰሰሪዎችን እያመረተ ከሚገኘው ትራንዚሽን ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ ባለፈው ሳምንት ተፈራረመ፡፡
ትራንዚሽን ማኑፋክቸሪንግ እንደ TECNO, itel and Infinix ያሉ ሞባይሎችን እያመረተ የሚገኝ ዓለም አቀፍ ድርጅት ሲሆን በኮሌጁ ለሚገኘው የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት የስልጠና ዘርፍን ውጤታማ ለማድረግ ታቅዶ የተተገበረ ነው፡፡ በዚህ ስምምነት የኮሌጁ አሰልጣኞች እና ሰልጣኞች ተግባራዊ ስልጠና ለማግኘት እና ለተመራቂ ሰልጣኞች የስራ እድል ለመፍጠር ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሏል፡፡
ከድርጅቱ የመጡት የስራ ኃላፊዎች ከስምምነቱ ባሻገር በኮሌጁ ውስጥ በአዲስ ግብዓት የተደራጀውን የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት ወርክሾችን ጎብኝተዋል፡፡ ስምምነቱን የተፈራረሙት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው እና የድርጅቱ የሰው ሃብት ማናጀር ወ/ሮ ዓለምፀሐይ ንጉሴ ናቸው፡፡
ዲፓርትመንቱ በምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማዕከል እንዲሆን በዓለም ባንክ በኩል በርካታ መዋዕለ ነዋይ ተበርክቶለት ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ በተለያየ ጊዜ መዘገባችን ይታወሳል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ኮሌጁ ከትራንዚሽን ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ጋር አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ!!
ኮሌጁ የተለያዩ የሞባይል ዓይነቶች እና የሞባይል አክሰሰሪዎችን እያመረተ ከሚገኘው ትራንዚሽን ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ ባለፈው ሳምንት ተፈራረመ፡፡
ትራንዚሽን ማኑፋክቸሪንግ እንደ TECNO, itel and Infinix ያሉ ሞባይሎችን እያመረተ የሚገኝ ዓለም አቀፍ ድርጅት ሲሆን በኮሌጁ ለሚገኘው የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት የስልጠና ዘርፍን ውጤታማ ለማድረግ ታቅዶ የተተገበረ ነው፡፡ በዚህ ስምምነት የኮሌጁ አሰልጣኞች እና ሰልጣኞች ተግባራዊ ስልጠና ለማግኘት እና ለተመራቂ ሰልጣኞች የስራ እድል ለመፍጠር ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሏል፡፡
ከድርጅቱ የመጡት የስራ ኃላፊዎች ከስምምነቱ ባሻገር በኮሌጁ ውስጥ በአዲስ ግብዓት የተደራጀውን የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት ወርክሾችን ጎብኝተዋል፡፡ ስምምነቱን የተፈራረሙት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው እና የድርጅቱ የሰው ሃብት ማናጀር ወ/ሮ ዓለምፀሐይ ንጉሴ ናቸው፡፡
ዲፓርትመንቱ በምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማዕከል እንዲሆን በዓለም ባንክ በኩል በርካታ መዋዕለ ነዋይ ተበርክቶለት ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ በተለያየ ጊዜ መዘገባችን ይታወሳል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍24❤1
ረቡዕ፡- ህዳር 5 ቀን 2016 ዓ.ም
የቴክኒክና ሙያ የመግቢያ ነጥብ ይፋ ተደረገ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም ወደ ቲክኒክና ሙያ መግቢያ ነጥብ ይፋ አድርጓል።
ሚኒስቴሩ የመግቢያ ነጥቡን ይፋ ያደረገው ዛሬ ረቡዕ ኅዳር 5 ቀን 2016 ዓ.ም ሲሆን መግለጫውን የሰጡት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ናቸው። በዚህም የተፈጥሮ ሳይንስ ለደረጃ 5 የመቁረጫ ነጥብ ወንድ ከ218፣ ሴት 199 በላይ፣ የታዳጊ ክልል (የአርብቶ አደር አካባቢዎች) ወንድ ከ192፣ ሴት 187 በላይ፣ በተፈጥሮ ሳይንስ አካል ጉዳተኞች 147ና ከዚያ በላይ (ሁሉንም ክልሎች ታሳቢ ያደረገ ነው) ብለዋል።
ደረጃ 3 እና 4 ወንድ ከ173፣ ሴት 163 በላይ፣ ታዳጊ ክልሎች ወንድ ከ157፣ ሴት 156 በላይ፣ አካል ጉዳተኞች 130ና ከዚያ በላይ ነው ተብሏል።
ተፈጥሮ ሳይንስ ደረጃ 1 እና 2 ወንድ 172፣ ሴት 162ና ከዚያ በላይ፣ ታዳጊ ክልሎች ወንድ 156፣ ሴት 155ና ከዚያ በላይ ነው።
ማኅበራዊ ሳይንስ ለደረጃ 5 ወንድ 179፣ ሴት 170ና ከዚያ በላይ፣ ታዳጊ ክልሎች ወንድ 166፣ ሴት 162፣ አካል ጉዳተኞች 147ና ከዚያ በላይ ነው።
ደረጃ 3 እና 4 በማኅበራዊ ሳንይንስ ወንድ 149፣ ሴት 147፣ ታዳጊ ክልል ወንድ 138፣ ሴት 137ና ከዚያ በላይ፣ አካል ጉዳተኞች 130ና ከዚያ በላይ ሆኗል።
ደረጃ 1 እና 2 በማኅበራዊ ሳይንስ ወንድ 148፣ 146፣ ታዳጊ ክልል ወንድ 137፣ ሴት 136፣ አካል ጉዳተኞች 129ና ከዚያ በላይ መሆኑን አስረድተዋል።
ሚኒስትሯ አክለውም፣ "በ2016 ዓ.ም 844 ሺሕ 384 የሚሆኑ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ወስደዋል። ከእነዚህ ውስጥ በእኛ ምልከታ 632 ሺሕ 587 የሚሆኑት ወደ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ይመጣሉ የሚል ግምት አለን" ነው ያሉት።
የሰው ሃይል ለመቀበል የተሻለ ዝግጁነት አላቸው ያልናቸውኝ የመንግሥትና የግል የቴኪኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማትን ፈትሸናል ያሉት ሚኒስትሯ፣ እስካሁን ባለው ከ28 ሺህ በላይ የሚሆኑ አሰልጣኞች፣ ወደ 1ሺሕ 400 ገደማ የተሻለ ብቃት ያላቸው ማሰልጠኛ ኮሌጆች አሉ ብለዋል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
Credit: መረጃውን ሰማሁ ብሎ እወቁልኝ ያለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ነው።
የቴክኒክና ሙያ የመግቢያ ነጥብ ይፋ ተደረገ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም ወደ ቲክኒክና ሙያ መግቢያ ነጥብ ይፋ አድርጓል።
ሚኒስቴሩ የመግቢያ ነጥቡን ይፋ ያደረገው ዛሬ ረቡዕ ኅዳር 5 ቀን 2016 ዓ.ም ሲሆን መግለጫውን የሰጡት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ናቸው። በዚህም የተፈጥሮ ሳይንስ ለደረጃ 5 የመቁረጫ ነጥብ ወንድ ከ218፣ ሴት 199 በላይ፣ የታዳጊ ክልል (የአርብቶ አደር አካባቢዎች) ወንድ ከ192፣ ሴት 187 በላይ፣ በተፈጥሮ ሳይንስ አካል ጉዳተኞች 147ና ከዚያ በላይ (ሁሉንም ክልሎች ታሳቢ ያደረገ ነው) ብለዋል።
ደረጃ 3 እና 4 ወንድ ከ173፣ ሴት 163 በላይ፣ ታዳጊ ክልሎች ወንድ ከ157፣ ሴት 156 በላይ፣ አካል ጉዳተኞች 130ና ከዚያ በላይ ነው ተብሏል።
ተፈጥሮ ሳይንስ ደረጃ 1 እና 2 ወንድ 172፣ ሴት 162ና ከዚያ በላይ፣ ታዳጊ ክልሎች ወንድ 156፣ ሴት 155ና ከዚያ በላይ ነው።
ማኅበራዊ ሳይንስ ለደረጃ 5 ወንድ 179፣ ሴት 170ና ከዚያ በላይ፣ ታዳጊ ክልሎች ወንድ 166፣ ሴት 162፣ አካል ጉዳተኞች 147ና ከዚያ በላይ ነው።
ደረጃ 3 እና 4 በማኅበራዊ ሳንይንስ ወንድ 149፣ ሴት 147፣ ታዳጊ ክልል ወንድ 138፣ ሴት 137ና ከዚያ በላይ፣ አካል ጉዳተኞች 130ና ከዚያ በላይ ሆኗል።
ደረጃ 1 እና 2 በማኅበራዊ ሳይንስ ወንድ 148፣ 146፣ ታዳጊ ክልል ወንድ 137፣ ሴት 136፣ አካል ጉዳተኞች 129ና ከዚያ በላይ መሆኑን አስረድተዋል።
ሚኒስትሯ አክለውም፣ "በ2016 ዓ.ም 844 ሺሕ 384 የሚሆኑ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ወስደዋል። ከእነዚህ ውስጥ በእኛ ምልከታ 632 ሺሕ 587 የሚሆኑት ወደ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ይመጣሉ የሚል ግምት አለን" ነው ያሉት።
የሰው ሃይል ለመቀበል የተሻለ ዝግጁነት አላቸው ያልናቸውኝ የመንግሥትና የግል የቴኪኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማትን ፈትሸናል ያሉት ሚኒስትሯ፣ እስካሁን ባለው ከ28 ሺህ በላይ የሚሆኑ አሰልጣኞች፣ ወደ 1ሺሕ 400 ገደማ የተሻለ ብቃት ያላቸው ማሰልጠኛ ኮሌጆች አሉ ብለዋል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
Credit: መረጃውን ሰማሁ ብሎ እወቁልኝ ያለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ነው።
👍28
ሐሙስ፥- ህዳር 6 ቀን 2016 ዓ∙ም
በዚህ ዓመት በአዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊስ መሠረት እስከ ደረጃ 6 ቅበላ ይደረጋል ተባለ!!
ከባለፈው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው አዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ መሰረት ከዚህ ቀደም እስከ ደረጃ 5 ብቻ ተገድቦ የነበረው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የእድገት መሰላል እስከ ደረጃ 8 ድረስ እንዲሆን መደረጉ ይታወሳል፡፡
ይህም ፖሊሲው ደረጃ ስድስትን ከመጀመሪያ ድግሪ፣ ደረጃ ሰባትን ከማስተርስ እንዲሁም ደረጃ ስምንትን ከዶክትሬት ዲግሪ /PhD/ ጋር ትይዩ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
ስለሆነም በዚህ ዓመት የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ መግባት ቢፈልጉ በደረጃ 6 ገብተው መሰልጠን እንደሚያስችላቸው ተመላክቷል፡፡
ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በደረጃ 6 የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች እንደሚስተናገዱ የጠቆሙት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሙፈሪያት ካሚል ሲሆኑ በዚህ ዓመት በተቀመጠው መስፈርት መሰረት በክልሎች አማካኝነት የሰልጣኞች ምደባ ይካሄዳል ብለዋል፡፡
በዚህም በተያዘው የሥልጠና ዘመን 632 ሺህ በላይ ተማሪዎች የሥራ ገበያውን የሰው ሀይል ፍላጎት መሠረት ባደረገ መልኩ ከደረጃ 1-ደረጃ 5 እንደ ውጤታቸው ተመድበው እንደሚሰለጥኑም ነው ክብርት ሚኒስትሯ የገለጹት፡፡
በወጣው መቁረጫ ነጥብ መሰረትም ደረጃ አንድ እና ሁለት 110,015 ፤ በደረጃ ሦሰት እና አራት 412,557 እንዲሁም በደረጃ አምስት 110,015 እንደሚሳተፉ የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር በደረጃ ስድስት ደግሞ 2000 የሚሆኑ ሰልጣኞችን ለቀመበል ዝግጅት መደረጉን አመላክተዋል፡፡
የ2016 የስልጠና ዘመን የተዘጋጀው መቁረጫ ነጥብ የ2015 ትምህርት እና የ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12 ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ላይ ተግባራዊ ይሆናል፡፡
ከ2014 ዓ.ም በፊት ለነበሩ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ደግሞ በስልጠና ዘመኑ በነበረው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ይስተናገዳሉ፡፡
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
Credit: መረጃውን እወቁልኝ ብሎ በማኀበራዊ ትስስር ገጹ ያጋራው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ነው።
በዚህ ዓመት በአዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊስ መሠረት እስከ ደረጃ 6 ቅበላ ይደረጋል ተባለ!!
ከባለፈው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው አዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ መሰረት ከዚህ ቀደም እስከ ደረጃ 5 ብቻ ተገድቦ የነበረው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የእድገት መሰላል እስከ ደረጃ 8 ድረስ እንዲሆን መደረጉ ይታወሳል፡፡
ይህም ፖሊሲው ደረጃ ስድስትን ከመጀመሪያ ድግሪ፣ ደረጃ ሰባትን ከማስተርስ እንዲሁም ደረጃ ስምንትን ከዶክትሬት ዲግሪ /PhD/ ጋር ትይዩ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
ስለሆነም በዚህ ዓመት የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ መግባት ቢፈልጉ በደረጃ 6 ገብተው መሰልጠን እንደሚያስችላቸው ተመላክቷል፡፡
ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በደረጃ 6 የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች እንደሚስተናገዱ የጠቆሙት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሙፈሪያት ካሚል ሲሆኑ በዚህ ዓመት በተቀመጠው መስፈርት መሰረት በክልሎች አማካኝነት የሰልጣኞች ምደባ ይካሄዳል ብለዋል፡፡
በዚህም በተያዘው የሥልጠና ዘመን 632 ሺህ በላይ ተማሪዎች የሥራ ገበያውን የሰው ሀይል ፍላጎት መሠረት ባደረገ መልኩ ከደረጃ 1-ደረጃ 5 እንደ ውጤታቸው ተመድበው እንደሚሰለጥኑም ነው ክብርት ሚኒስትሯ የገለጹት፡፡
በወጣው መቁረጫ ነጥብ መሰረትም ደረጃ አንድ እና ሁለት 110,015 ፤ በደረጃ ሦሰት እና አራት 412,557 እንዲሁም በደረጃ አምስት 110,015 እንደሚሳተፉ የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር በደረጃ ስድስት ደግሞ 2000 የሚሆኑ ሰልጣኞችን ለቀመበል ዝግጅት መደረጉን አመላክተዋል፡፡
የ2016 የስልጠና ዘመን የተዘጋጀው መቁረጫ ነጥብ የ2015 ትምህርት እና የ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12 ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ላይ ተግባራዊ ይሆናል፡፡
ከ2014 ዓ.ም በፊት ለነበሩ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ደግሞ በስልጠና ዘመኑ በነበረው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ይስተናገዳሉ፡፡
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
Credit: መረጃውን እወቁልኝ ብሎ በማኀበራዊ ትስስር ገጹ ያጋራው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ነው።
👍24
ሐሙስ:-ህዳር 6 ቀን 2016 ዓ.ም
አዲስ በተቀረፀው የሰልጣኞች ስነ ምግባር መመሪያ ዙሪያ ከሰልጣኞች እና ከሰልጣኞች ጋር ቀጥታ ግንኙነት ካላቸው አካላት ጋር ውይይት ተደረገ!!
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና ቢሮ ተዘጋጅቶ በከተማ አስተዳደሩ ስር በሚገኙ 15 የመንግስት ቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ላይ በሚተገበረው የሰልጣኞች የስነ ምግባር መመሪያ ዙርያ ከሰልጣኞች እና ከሰልጣኞች ጋር ቀጥታ ግንኙነት ካላቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
በ4 ክፍሎች እና በ27 አንቀፆች የተሰነደው መመሪያ ሰልጣኞች ህግና ደንብ አክብረው እንዲማሩ፣ በተቋሙ ውስጥ ሁሉን አቀፍ አዎንታዊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው፣ ተቋማዊ ሥርዓት እንዲሰፍን፣ የስልጠና ጥራት እንዲረጋገጥ እና ምቹ የመማር ማስተማር አካባቢን ለመፍጠር ታቅዶ መዘጋጀቱ ተገልጿል፡፡
መመሪው የስነ ምግባር ግድፈት ዓይነቶች እና የእርምት እርምጃዎችን ብቻ ሳይሆን ሰልጣኞች መጠቀም ያለባቸውን ሙሉ መብት እና መወጣት ያለባቸውን ግዴታ በስፋት ይዘረዝራል፡፡
በመመሪያው ዙሪያ ከሰልጣኞች ጋር ውይይት የተደረገው ዛሬ ህዳር 6 ቀን 2016 ዓ.ም ሲሆን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ደግሞ ትናንት ህዳር 5 ቀን ነው፡፡
በኮሌጅ ደረጃ በስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን የሚመራ የሰልጣኞች ዲሲፕሊን ኮሚቴ እንደሚዋቀር ተገልጿል።
መመሪያው ረቂቅ በመሆኑ ከመፅደቁ በፊት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተወያይቶ የጋራ ለማድረግ ታስቦ የተደረገ ነው ያሉን ደግሞ የኮንስትራክሽን ስልጠና ክፍል ተጠሪ እና በመመሪያ ዝግጅቱ የጀነራል ዊንጌት ተወካይ የሆኑት አሰልጣኝ ኤፍሬም ጥላሁን ናቸው።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
አዲስ በተቀረፀው የሰልጣኞች ስነ ምግባር መመሪያ ዙሪያ ከሰልጣኞች እና ከሰልጣኞች ጋር ቀጥታ ግንኙነት ካላቸው አካላት ጋር ውይይት ተደረገ!!
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና ቢሮ ተዘጋጅቶ በከተማ አስተዳደሩ ስር በሚገኙ 15 የመንግስት ቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ላይ በሚተገበረው የሰልጣኞች የስነ ምግባር መመሪያ ዙርያ ከሰልጣኞች እና ከሰልጣኞች ጋር ቀጥታ ግንኙነት ካላቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
በ4 ክፍሎች እና በ27 አንቀፆች የተሰነደው መመሪያ ሰልጣኞች ህግና ደንብ አክብረው እንዲማሩ፣ በተቋሙ ውስጥ ሁሉን አቀፍ አዎንታዊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው፣ ተቋማዊ ሥርዓት እንዲሰፍን፣ የስልጠና ጥራት እንዲረጋገጥ እና ምቹ የመማር ማስተማር አካባቢን ለመፍጠር ታቅዶ መዘጋጀቱ ተገልጿል፡፡
መመሪው የስነ ምግባር ግድፈት ዓይነቶች እና የእርምት እርምጃዎችን ብቻ ሳይሆን ሰልጣኞች መጠቀም ያለባቸውን ሙሉ መብት እና መወጣት ያለባቸውን ግዴታ በስፋት ይዘረዝራል፡፡
በመመሪያው ዙሪያ ከሰልጣኞች ጋር ውይይት የተደረገው ዛሬ ህዳር 6 ቀን 2016 ዓ.ም ሲሆን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ደግሞ ትናንት ህዳር 5 ቀን ነው፡፡
በኮሌጅ ደረጃ በስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን የሚመራ የሰልጣኞች ዲሲፕሊን ኮሚቴ እንደሚዋቀር ተገልጿል።
መመሪያው ረቂቅ በመሆኑ ከመፅደቁ በፊት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተወያይቶ የጋራ ለማድረግ ታስቦ የተደረገ ነው ያሉን ደግሞ የኮንስትራክሽን ስልጠና ክፍል ተጠሪ እና በመመሪያ ዝግጅቱ የጀነራል ዊንጌት ተወካይ የሆኑት አሰልጣኝ ኤፍሬም ጥላሁን ናቸው።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍23❤1
ሰኞ 10/03/2016 ዓ.ም ምዝገባ ይጀመራል በምስሉ ላይ የተገለፀውን ቅደም ተከተል በመከተል በ https://www.aatvetb.edu.et/ ድህረገፅ ገብተው ይመዝገቡ
Galmeen Wixataa (10/03/2016 A.L.H) eegalma, marsariitii https://www.aatvetb.edu.et/ seenuun tartiiba suuraa irratti mul'atu hordofuun galmaa'aa.
Registration Will start Monday( Nov 20/2023), log in to the website https://www.aatvetb.edu.et/ and register by following the order shown in the image.
Galmeen Wixataa (10/03/2016 A.L.H) eegalma, marsariitii https://www.aatvetb.edu.et/ seenuun tartiiba suuraa irratti mul'atu hordofuun galmaa'aa.
Registration Will start Monday( Nov 20/2023), log in to the website https://www.aatvetb.edu.et/ and register by following the order shown in the image.
👍12