General Wingate Polytechnic college-Official channel
9.95K subscribers
3.37K photos
43 videos
204 files
198 links
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን።

የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።
Download Telegram
አግሮ ዞን ዲዛይን
Forwarded from admasu Ye Abiye Lij
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
agrizone
7😢2👍1
ቅዳሜ፦ መጋቢት 28 ቀን 2016 ዓ.ም

ማስታወቂያ

ለኮሌጁ አሰልጣኞች እና አስተዳደር ሠራተኞች በሙሉ

ሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም በወቅታዊ የፐብሊክ ሰርቪስ ስራ አተገባበር ዙሪያ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ስላለ በእለቱ ከጧቱ 2:30 ላይ አስተዳደር ህንጻ 4ኛ ፎቅ በሚገኘው አዲሱ አዳራሽ እንዲትገኙ እያሳሰብን ነገር ግን መደበኛው የስልጠና ሂደት መኖሩን እናሳውቃለን።

የኮሌጁ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
👍8
ሰኞ:- መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም

አሻራ እንነካለን፣ አሻራችንንም እናስቀምጣለን!!

የኮሌጁ የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በሰራተኞች ዲጂታል የሰዓት መቆጣጠሪያ አጠቃቀም እና አጠቃላይ የፐብሊክ ሰርቫንቱ መብት እና ግዴታዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ተደረገ፡፡

እንደ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ሰርቫንቱ መብት እና ግደታ የተደነገገባቸውን አዋጆች፣ ደንቦች እና መመሪያዎች በማጣቀስ ለተሳታፊዎች በገለፃ ያቀረቡት የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሯ መቅደስ አባይ ናቸው፡፡

በገለፃው ላይ የዲጂታል የሰዓት መቆጣጠሪያ ስርዓት /የጣት አሻራ/ አጠቃቀም ዙሪያ በስፋት ተነስቷል፡፡ እንደ ኮሌጅ ከማኑዋል ወደ ወረቀት አልባ ዲጂታል ስርዓት መሻጋገራችን ግድ ይለናል ምክኒያቱም የአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች መፈልፈያ ቋት ሆነን ለሌሎች ስናሸጋገር የእኛ የቴክሎጂ አጠቃቀማችን መዘግየት የለበትም ያሉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ናቸው፡፡ ዋና ዲኑ አክለውም ኮሌጃችንን በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፖሊ ቴክኒክ ለማድረግ የያዝነው ራዕይ እውን የሚሆነው የጊዜ አጠቃቀማችን ውጤታማ ሲሆን ነው ነገር ግን የተዘረጋው ስርዓት ከተቋሙ የስራ ባህርይ እና ከሰራተኛው የስራ ጠባይ ጋር ቅን ተዛምዶ እንዲኖረው ይደረጋል ብለዋል፡፡

ከዚህ ባሻገር የተቋሙን የውስጥ ገቢ በማሳደግ ኮሌጁ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመንና ሰራተኛውን ለመደጎም ሁሉም ዲፓርትመንቶች ባቀረቡት የምርትና የአገልግሎት ፕሮፖዛል መሰረት በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገቡ አቅጣጫ የተሰጠ ሲሆን የተወሰኑ ዘርፎች ወደ ገበያው መቀላቀላቸው ተገልጿል፡፡

በመጨረሻም የስራ ሰዓታችንን ለመከታተል የጣት አሻራ እንነካለን፣ ኮሌጃችንን የሚመጥን ስራ በመስራት ለቀጣይ ትውልድ አሻራችንን እናስቀምጣለን በሚለው ገዢ ሀሳብ ማጠቃለያ ተስጥቶ ተጠናቋል፡፡

ለኮሌጁ አሰልጣኞች ብቻ የሰዓት መከታተያያ ስርዓቱ ወደ ዲጂታል ከተቀየረ አንድ ዓመት ማስቆጠሩ ይታወሳል፡፡

"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍111👎1
ማክሰኞ:- ሚያዚያ 1 ቀን 2016 ዓ.ም

የጨረታ ማስታወቂያ

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኮሌጁ የእንሰሳት እርባታ ጣቢያ የሚገኙ የቀንድ ከብቶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ አውጥቷል፡፡

በመሆኑም ለጨረታ የቀረቡ የቀንድ ከብቶችን መግዛት የምትፈልጉ አካላት በሙሉ ጨረታው ከወጣበት ከመጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ለጨረታ የቀረቡ ወንድ ጥጆችን፣ የወተት ላሞችን እና ጊደሮችን መጫረት የምትችሉ ሲሆን የጨረታ ሰንዱን ከኮሌጁ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ማግኘት እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡

ሰፊውን ዝርዝር መረጃ የሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ዕትም አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ መመልከት የሚችሉ መሆኑንም እንገልፃለን፡፡

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
👍51😢1
ማክሰኞ:- ሚያዚያ 1 ቀን 2016 ዓ.ም

ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የኮሌጁ ሰራተኞች የማዕድ ማጋራት ስጦታ ተደረገ!!

በኮሌጁ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው 121 ሰራተኞች የበዓል መዋያ የሚሆን የዘይት እና ዱቄት ስጦታ ተደርጓል፡፡

ስጦታው ነገ የሚከበረውን የእስልምና እምነት ተከታይ የኢድ አልፈጥር በዓል እና ከሳምንታት በኋላ ለሚከተለው የክርስትና እምነት ተከታዮች የትንሳኤ በዓልን ምክኒያት በማድረግ የተበረከተ ነው፡፡

የማዕድ ማጋራት ዓላማው በኑሮ ውድነቱ ምክንያት ጫና ላይ ላሉ የስራ ባልደረቦች የመተሳሰብ እና የመረዳዳት ባህል ለማጠናከር እና የአንዱን ችግር ሌላዉ እንዲጋራ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
👍94🙏1
ማክሰኞ:- ሚያዚያ 1 ቀን 2016 ዓ.ም

"ኢድ ሙባረክ''

ለኮሌጃችን የእስልምና እምነት ተከታይ ሰራተኞች፣ ሰልጣኞች እና አጋሮቻችን በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው ዓመተ ሂጅራ የኢድ አልፈጥር ረመዳን በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የዕድገት እና የበጎነት ይሆንላችሁ ዘንድ እንመኛለን።

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
18👍11👏2