ሰኞ፡- ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም
የአዳዲስ ሰልጣኞች ምዝገባ ከተጀመረ አንድ ሳምንት አስቆጠረ!!
ኮሌጁ የ2016 ዓ.ም አዳዲስ ሰልጣኞችን በበየነ መረብ /online/ መመዝገብ የጀመረው የዛሬ ሳምንት ህዳር 10 ቀን 2016 ዓ∙ም ነው።
እስከ አሁን በተደረገው የወረቀት አልባ ኦን ላይን ምዝገባ በ2015 ዓ.ም 12ኛ ክፍልን ያጠናቀቁና ከዚያ በፊት ጨርሰው የተቀመጠውን የቅበላ መስፈርት ያሟሉ አዳዲስ ሰልጣኞች ምዝገባቸውን አከናውነዋል። በምዝገባ ሂደቱም የኔትወርክ መጨናነቅና የተመዝጋቢዎች ወረፋ እንዳይኖር ከሬጅስትራል ሰራተኞች ባሻገር በርካታ የቢሮ ሰራተኞች በምዝገባ ሂደቱ ላይ እንዲሳተፉ ተደርጓል፡፡ እስካሁንም ከ1400 በላይ አዳዲስ ሰልጣኞች ምዝገባቸውን አጠናቀዋል፡፡
ያልተመዘገባችሁ ውድ አመልካቾች ባላችሁበት ሆናችሁ በሞባይል ወይም ደግሞ በአቅራቢያችሁ ባለ ኢንተርኔት ቤት በመሄድ መመዝገብ የምትችሉ ሲሆን ሂደቱም በሚከተለው መልኩ ነው፡፡
ይኸውም፡- ብራውዘራችሁ ላይ gwptc.sims.aatvetb.edu.et የሚለውን ሰርች ማድረግ፣ በስተግራ ያለውን 3 ነጥብ መጫን፣ በመቀጠልም registration guideline የሚለውን በመጫን መመሪያውን ማንበብ፣ Application form የሚለውን መምረጥ፣ የተጠየቁትን መረጃዎች በሙሉ መሙላት። ስልክ የሚጠይቅበት ቦታ ላይ 09 ሳይሆን 9 ብሎ መጀመር፣ ከዚያም Apply የሚለውን በመጫን፣ በመጨረሻም ሲስተሙ admission ID በ 8465 SMS ይልካል።
- በ8465 SMS የተላከላችሁን አጭር የፅሑፍ መልዕክት እያሳያችሁ በኮሌጁ registrar በአካል በመገኘት ከ8ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለ አጠቃላይ ዋናው የትምህርት ማስረጃችሁን እና የማይመለስ ኮፒ እንዲሁም 2 ጉርድ ፎቶ በመያዝ ቀሪ የምዝገባ ሂደታችሁን ማጠናቀቅ ይኖርባችኋል፤ ተብላችኋል፡፡
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
የአዳዲስ ሰልጣኞች ምዝገባ ከተጀመረ አንድ ሳምንት አስቆጠረ!!
ኮሌጁ የ2016 ዓ.ም አዳዲስ ሰልጣኞችን በበየነ መረብ /online/ መመዝገብ የጀመረው የዛሬ ሳምንት ህዳር 10 ቀን 2016 ዓ∙ም ነው።
እስከ አሁን በተደረገው የወረቀት አልባ ኦን ላይን ምዝገባ በ2015 ዓ.ም 12ኛ ክፍልን ያጠናቀቁና ከዚያ በፊት ጨርሰው የተቀመጠውን የቅበላ መስፈርት ያሟሉ አዳዲስ ሰልጣኞች ምዝገባቸውን አከናውነዋል። በምዝገባ ሂደቱም የኔትወርክ መጨናነቅና የተመዝጋቢዎች ወረፋ እንዳይኖር ከሬጅስትራል ሰራተኞች ባሻገር በርካታ የቢሮ ሰራተኞች በምዝገባ ሂደቱ ላይ እንዲሳተፉ ተደርጓል፡፡ እስካሁንም ከ1400 በላይ አዳዲስ ሰልጣኞች ምዝገባቸውን አጠናቀዋል፡፡
ያልተመዘገባችሁ ውድ አመልካቾች ባላችሁበት ሆናችሁ በሞባይል ወይም ደግሞ በአቅራቢያችሁ ባለ ኢንተርኔት ቤት በመሄድ መመዝገብ የምትችሉ ሲሆን ሂደቱም በሚከተለው መልኩ ነው፡፡
ይኸውም፡- ብራውዘራችሁ ላይ gwptc.sims.aatvetb.edu.et የሚለውን ሰርች ማድረግ፣ በስተግራ ያለውን 3 ነጥብ መጫን፣ በመቀጠልም registration guideline የሚለውን በመጫን መመሪያውን ማንበብ፣ Application form የሚለውን መምረጥ፣ የተጠየቁትን መረጃዎች በሙሉ መሙላት። ስልክ የሚጠይቅበት ቦታ ላይ 09 ሳይሆን 9 ብሎ መጀመር፣ ከዚያም Apply የሚለውን በመጫን፣ በመጨረሻም ሲስተሙ admission ID በ 8465 SMS ይልካል።
- በ8465 SMS የተላከላችሁን አጭር የፅሑፍ መልዕክት እያሳያችሁ በኮሌጁ registrar በአካል በመገኘት ከ8ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለ አጠቃላይ ዋናው የትምህርት ማስረጃችሁን እና የማይመለስ ኮፒ እንዲሁም 2 ጉርድ ፎቶ በመያዝ ቀሪ የምዝገባ ሂደታችሁን ማጠናቀቅ ይኖርባችኋል፤ ተብላችኋል፡፡
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍23😢3
ረቡዕ፡- ህዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም
ሰዓቱ እየቆጠረ ነው!!
ኮሌጁ አዳዲስ ሰልጣኞችን መመዝገብ ከጀመረ እንሆ ሁለተኛ ሳምንት ተቆጠረ፡፡ በዚህ ምዝገባ ላይ ኮሌጁ ካለው የስልጠና ግብዓት መጠን እና እንዲቀበል ከተጣለበት ኮታ አንፃር አሁን ላይ 50 ፐርሰንት ያህሉ ምዝገባቸውን አጠናቋል፡፡
ውድ ምዝገባችሁን ያጠናቀቃችሁ አዳዲስ ሰልጣኞች!!
ኮሌጃችን በISO 9001:2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርቲፋይድ የሆነ ብቸኛ ተቋም መሆኑ፣ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመሆን አቅዶ እየተጋ መገኘቱ፣ በኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዘርፍ የልህቀት ማዕከል እንዲሆን ብዙ ስራዎች እየተከወኑ መገኘቱ እና የተቋሙን አጠቃላይ ስነ ምህዳር ውብ እና ማራኪ ለማድረግ ሰፊ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አይታችሁ እኛን መርጣችሁ በመምጣታችሁ እናመሰግናለን።
እኛን መርጣችሁ ስትመጡ በምክኒያት እንደሆነ እንረዳለን፣ አስር ጊዜ ብቻ ሳይሆን ከሃምሳ ጊዜ በላይ ለክታችሁ እኛ ጋር ቆርጣችሁ እንደመጣችሁ እናምናለን፡፡ የነገውን ትውልድ የመጠነ እና ዓለም የደረሰበትን የስልጠና ስማርት ቴክኖሎጂ ግብዓት ለመጠቀም ለሁሉም ዲፓርትመንቶች ኢንተራክቲቭ ቦርድ የተገጠመላቸው የሙያ ዘርፎችን መርጣችሁ በመመዝገባችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ የእያንዳንዱ ዲፓርትመንት በከፍተኛ መዋለ ንዋይ የተገዙ ዘመኑን የዋጁ አዳዲስ ግብዓትን ከብቁ አሰልጣኞች ጋር አሟልቶ ይጠብቃችኋል፡፡
ውድ እስከ አሁን ምዝገባ ያላደረጋችሁ ደንበኞቻችን!!
ለምዝገባ እንደርሳለን በማለት የተዘናጋችሁ ወይም ጀነራል ዊንጌት ልመዝገብ አልመዝገብ በማለት ያመነታችሁ ቤተሰቦቻችን ሰዓቱ እየቆጠረ ነው፡፡ ዓላማችን እናንተን ብቁ ባለሙያ ማድረግ ስለሆነ ቦታ ሳይሞላ እና የምዝገባ ጊዜ ሳይጠናቀቅ በፈለጉት የሙያ ዘርፍ እና በሚመችዎት የስልጠና መርሃ ግብር ማለትም በቀን፣ በማታ፣ እና በቅዳሜ እና እሁድ ተመዝግበው እንዲሰለጥኑ እንመክራለን፡፡ የሚከተለውን ማስፈንጠርያ ተጭነው ይመዝገቡ=- http://gwptc.sims.aatvetb.edu.et
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ሰዓቱ እየቆጠረ ነው!!
ኮሌጁ አዳዲስ ሰልጣኞችን መመዝገብ ከጀመረ እንሆ ሁለተኛ ሳምንት ተቆጠረ፡፡ በዚህ ምዝገባ ላይ ኮሌጁ ካለው የስልጠና ግብዓት መጠን እና እንዲቀበል ከተጣለበት ኮታ አንፃር አሁን ላይ 50 ፐርሰንት ያህሉ ምዝገባቸውን አጠናቋል፡፡
ውድ ምዝገባችሁን ያጠናቀቃችሁ አዳዲስ ሰልጣኞች!!
ኮሌጃችን በISO 9001:2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርቲፋይድ የሆነ ብቸኛ ተቋም መሆኑ፣ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመሆን አቅዶ እየተጋ መገኘቱ፣ በኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዘርፍ የልህቀት ማዕከል እንዲሆን ብዙ ስራዎች እየተከወኑ መገኘቱ እና የተቋሙን አጠቃላይ ስነ ምህዳር ውብ እና ማራኪ ለማድረግ ሰፊ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አይታችሁ እኛን መርጣችሁ በመምጣታችሁ እናመሰግናለን።
እኛን መርጣችሁ ስትመጡ በምክኒያት እንደሆነ እንረዳለን፣ አስር ጊዜ ብቻ ሳይሆን ከሃምሳ ጊዜ በላይ ለክታችሁ እኛ ጋር ቆርጣችሁ እንደመጣችሁ እናምናለን፡፡ የነገውን ትውልድ የመጠነ እና ዓለም የደረሰበትን የስልጠና ስማርት ቴክኖሎጂ ግብዓት ለመጠቀም ለሁሉም ዲፓርትመንቶች ኢንተራክቲቭ ቦርድ የተገጠመላቸው የሙያ ዘርፎችን መርጣችሁ በመመዝገባችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ የእያንዳንዱ ዲፓርትመንት በከፍተኛ መዋለ ንዋይ የተገዙ ዘመኑን የዋጁ አዳዲስ ግብዓትን ከብቁ አሰልጣኞች ጋር አሟልቶ ይጠብቃችኋል፡፡
ውድ እስከ አሁን ምዝገባ ያላደረጋችሁ ደንበኞቻችን!!
ለምዝገባ እንደርሳለን በማለት የተዘናጋችሁ ወይም ጀነራል ዊንጌት ልመዝገብ አልመዝገብ በማለት ያመነታችሁ ቤተሰቦቻችን ሰዓቱ እየቆጠረ ነው፡፡ ዓላማችን እናንተን ብቁ ባለሙያ ማድረግ ስለሆነ ቦታ ሳይሞላ እና የምዝገባ ጊዜ ሳይጠናቀቅ በፈለጉት የሙያ ዘርፍ እና በሚመችዎት የስልጠና መርሃ ግብር ማለትም በቀን፣ በማታ፣ እና በቅዳሜ እና እሁድ ተመዝግበው እንዲሰለጥኑ እንመክራለን፡፡ የሚከተለውን ማስፈንጠርያ ተጭነው ይመዝገቡ=- http://gwptc.sims.aatvetb.edu.et
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍18👎1😢1
ረቡዕ፦ ህዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም
የስልጠና ማስታወቂያ
ኮሌጃችን ከመደበኛው የስልጠና ፕሮግራም ባሻገር ለአጫጭር ስልጠና ፈላጊዎች በአዲስ መልኩ አማራጭ ይዞ መጥቷል።
ይኸውም በ10 የስልጠና ዘርፎች ስር በሚገኙ 53 ሙያዎች አጫጭር ስልጠናዎችን ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል።
ስለሆነም በአጭር ቀናት ሰልጥነው ረጅሙን የህይወት ጉዞ የሚሰሩበት ሙያ ይቅሰሙ።
በዚህ ስልጠና ለመማር ፍቃደኝነት ብቻ እንጂ የመግቢያ ነጥብ፣ የትምህርት ደረጃ እና መሰል መስፈርቶች አያግድዎትም።
ሁል ጊዜ ምዝገባ፣ ሁል ጊዜ ስልጠና አለ።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
የስልጠና ማስታወቂያ
ኮሌጃችን ከመደበኛው የስልጠና ፕሮግራም ባሻገር ለአጫጭር ስልጠና ፈላጊዎች በአዲስ መልኩ አማራጭ ይዞ መጥቷል።
ይኸውም በ10 የስልጠና ዘርፎች ስር በሚገኙ 53 ሙያዎች አጫጭር ስልጠናዎችን ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል።
ስለሆነም በአጭር ቀናት ሰልጥነው ረጅሙን የህይወት ጉዞ የሚሰሩበት ሙያ ይቅሰሙ።
በዚህ ስልጠና ለመማር ፍቃደኝነት ብቻ እንጂ የመግቢያ ነጥብ፣ የትምህርት ደረጃ እና መሰል መስፈርቶች አያግድዎትም።
ሁል ጊዜ ምዝገባ፣ ሁል ጊዜ ስልጠና አለ።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
👍27
ሐሙስ:- ህዳር 20 ቀን 2016 ዓ.ም
ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠና ተሰጠ!!
በኮሌጅ የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ም/ዲን ቢሮ በኩል ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ከህዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የ3 ቀናት ስልጠና ተሰጠ፡፡
ከአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 9 ወረዳዎች ለተውጣጡ 140 የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የቢዝነስ አመራር ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ይዘቱም ስለንግድ ፈጠራ አመራር ክሂሎት፣ በሚሰጡት አገልግሎት ወይም በሚያቀርቡት ምርት ላይ የሚጠበቅባቸው የውድድር ብቃት፣ ስለ ኢንተርፕርነር፣ ስለ ቴክኖሎጂ ፅንሰ ሀሳብ እና መሰል ጉዳዮች ላይ በጥልቀት ቀርቧል።
የስልጠና ፍላጎት ጥያቄ የመጣው ከራሳቸው ከአንቀሳቃሾቹ መሆኑም ተገልጿል፡፡
የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ም/ዲን ቢሮ በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አገልግሎት ዘርፍ የጥቃቅን እና አነስተኛ ተቋማትን ችግር ለይቶ እና ፍላጎታቸውን መሰረት አድርጎ በአራቱ የድጋፍ አግባቦች ማለትም የቴክኒካል ክህሎት፣ የስራ ፈጣሪነት ክህሎት፣ የምርጥ ቴክኖሎጂ አጠቃቀም እና የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ /ካይዘን/ አቅም ግንባታ አማካኝነት እግዛ ያደርጋል፡፡
አሁን ላይ 510 የሚሆኑ ነባር እና አዲስ ኢንተርፕራይዞች በኮለጁ ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገላቸው ይገኛሉ።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠና ተሰጠ!!
በኮሌጅ የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ም/ዲን ቢሮ በኩል ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ከህዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የ3 ቀናት ስልጠና ተሰጠ፡፡
ከአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 9 ወረዳዎች ለተውጣጡ 140 የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የቢዝነስ አመራር ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ይዘቱም ስለንግድ ፈጠራ አመራር ክሂሎት፣ በሚሰጡት አገልግሎት ወይም በሚያቀርቡት ምርት ላይ የሚጠበቅባቸው የውድድር ብቃት፣ ስለ ኢንተርፕርነር፣ ስለ ቴክኖሎጂ ፅንሰ ሀሳብ እና መሰል ጉዳዮች ላይ በጥልቀት ቀርቧል።
የስልጠና ፍላጎት ጥያቄ የመጣው ከራሳቸው ከአንቀሳቃሾቹ መሆኑም ተገልጿል፡፡
የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ም/ዲን ቢሮ በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አገልግሎት ዘርፍ የጥቃቅን እና አነስተኛ ተቋማትን ችግር ለይቶ እና ፍላጎታቸውን መሰረት አድርጎ በአራቱ የድጋፍ አግባቦች ማለትም የቴክኒካል ክህሎት፣ የስራ ፈጣሪነት ክህሎት፣ የምርጥ ቴክኖሎጂ አጠቃቀም እና የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ /ካይዘን/ አቅም ግንባታ አማካኝነት እግዛ ያደርጋል፡፡
አሁን ላይ 510 የሚሆኑ ነባር እና አዲስ ኢንተርፕራይዞች በኮለጁ ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገላቸው ይገኛሉ።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍20
ቅዳሜ:- ህዳር 22 ቀን 2016 ዓ∙ም
2ሺ የሚደርሱ አዳዲስ ሰልጣኞች በ2 ሳምንት ተመዘገቡ!!
ኮሌጁ የ2016 ዓ.ም አዳዲስ ሰልጣኞችን ከህዳር 10 ቀን 2016 ዓ∙ም ጀምሮ በበየነ መረብ /online/ እና በሀርድ ኮፒ ለ2 ሳምንታት የመዘገበ ሲሆን በዚህም 2 ሺ የሚደርሱ አዳዲስ ሰልጣኞችን መመዝገቡ ታውቋል።
ኮሌጁ አሁን ላይ ባለው ዘርፈ ብዙ ፋሲሊቲዎችን ማሟላቱ እና ለስልጠና ጥራቱ ትኩረት መስጠቱ ተመራጭነቱን ይበልጥ ስላሰፋው ከፍተኛ ተመዝጋቢ ካላቸው የመዲናችን ቴክኒክና ሙያ ተቋማት ውስጥ የመጀመሪያውን ረድፍ ይዟል።
ውድ ተመዝጋቢዎች! በመሉ እምነት እኛን ተማምናችሁ መርጣችሁን ስለመጣችሁ እናመሰግናለን።
የአሁኑ ቅዳሜና እሁድ በበየነ መረብ መመዝገቢያ ሰንደቁ ላይ ምዝገባ ለማከናወን ሞክራችሁ ሲስተሙ እንዳስቸገራችሁ የገለፃችሁልን ብዙዎች ናችሁ። እውነታችሁን ነው የቀረቡ መረጃዎችን አስተካክለን የተጨማሪ ዙር ምዝገባ ሰኞ ህዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በዲጂታል ስርዓቱ ስለምናቀጥል በትዕግስት እንዲትጠባበቁን እንገልፃለን።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ምዝገባችሁን ያካሄዳችሁ አዳዲስ ሰልጣኞች የስልጠና ገለፃ /Training orentation/ ስላለ ሰኞ ህዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከጧቱ 2:30 በኮሌጁ እንድትገኙ እናሳውቃለን።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
2ሺ የሚደርሱ አዳዲስ ሰልጣኞች በ2 ሳምንት ተመዘገቡ!!
ኮሌጁ የ2016 ዓ.ም አዳዲስ ሰልጣኞችን ከህዳር 10 ቀን 2016 ዓ∙ም ጀምሮ በበየነ መረብ /online/ እና በሀርድ ኮፒ ለ2 ሳምንታት የመዘገበ ሲሆን በዚህም 2 ሺ የሚደርሱ አዳዲስ ሰልጣኞችን መመዝገቡ ታውቋል።
ኮሌጁ አሁን ላይ ባለው ዘርፈ ብዙ ፋሲሊቲዎችን ማሟላቱ እና ለስልጠና ጥራቱ ትኩረት መስጠቱ ተመራጭነቱን ይበልጥ ስላሰፋው ከፍተኛ ተመዝጋቢ ካላቸው የመዲናችን ቴክኒክና ሙያ ተቋማት ውስጥ የመጀመሪያውን ረድፍ ይዟል።
ውድ ተመዝጋቢዎች! በመሉ እምነት እኛን ተማምናችሁ መርጣችሁን ስለመጣችሁ እናመሰግናለን።
የአሁኑ ቅዳሜና እሁድ በበየነ መረብ መመዝገቢያ ሰንደቁ ላይ ምዝገባ ለማከናወን ሞክራችሁ ሲስተሙ እንዳስቸገራችሁ የገለፃችሁልን ብዙዎች ናችሁ። እውነታችሁን ነው የቀረቡ መረጃዎችን አስተካክለን የተጨማሪ ዙር ምዝገባ ሰኞ ህዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በዲጂታል ስርዓቱ ስለምናቀጥል በትዕግስት እንዲትጠባበቁን እንገልፃለን።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ምዝገባችሁን ያካሄዳችሁ አዳዲስ ሰልጣኞች የስልጠና ገለፃ /Training orentation/ ስላለ ሰኞ ህዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከጧቱ 2:30 በኮሌጁ እንድትገኙ እናሳውቃለን።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍37
ጀነራል_ዊንጌት_ፖለተኮ_በ2016_አመልክተው_ሙያ_የተደለደሉ.xlsx
119.3 KB
በ 2016 ዓ.ም በኮሌጁ ለመሰልጠን በቀን በማታ እና በዊኬንድ ለመሰልጠን የተመዘገባችሁ ሰልጣኞች የተመደባቹባቸውን ሙያዎች የሚከተለውን ኤክሴል ከፍታቹ ተመለከቱ።
👍40
ለonline registration ይሄንን ደረሰኝ ተጠቀሙ
👍9
ሰኞ፡- ህዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም
ለአዲስ ተመዝጋቢ ሰልጣኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ!!
በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2016 ዓ.ም ስልጠና ለመከታተል ላመለከቱ አዳዲስ ሰልጣኞች የግንዛቤ መስጫ መድረክ ዛሬ ህዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም ተካሄደ፡፡
በዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ በበጀት ዓመቱ በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠናቸውን ለመከታተል ያመለከቱ አዳዲስ ሰልጣኞች በዕለቱ ተገኝተዋል፡፡
በወቅቱ የኮሌጁ ዲኖች እና የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች በቦታው ተገኝተው የስልጠናውን ሂደት በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በዚህ የስልጠና ሂደት ገለፃ ላይ የሁሉም ስልጠና ክፍል ተጠሪዎች ተገኝተው ስለ ዲፓርትመንታቸው ምንነት፣ በዲፓርትመንቱ ስር ስለሚሰጡ የስልጠና መስኮች፣ እያንዳንዳቸው የስልጠና መስኮች በገበያው ላይ ያለው የስራ ፍላጎት፣ ስልጠናው የሚፈጀው የጊዜ ቆይታ እና መዳረሻቸው የት እንደሆነ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
አንዳንድ ዲፓርትመንቶች ደግሞ በሰልጣኞች የተሰሩ ምርቶችን መድረክ ላይ በማሳየት አዲስ ተመዝጋቢ ሰልጣኞች የስልጠና ክፍሉን እንዲቀላቀሉ የማስተዋወቅ እና የመቀስቀስ ስራ አከናውነዋል፡፡
አሁን ላይ አዳዲስ ሰልጣኞች ሌላ አማራጭ ፈልገው ዲፓርትመንት መቀየር ቢሹ መስተናገድ እንደሚችሉ የተገለፀ ሲሆን ነገር ግን Accounting & finance, Automotive elecetric & electronics, Automotive mechanics, Biulding electrical installation /BEI/, Fashion Designing, Hard ware & Networking Service, Marketing & Sales management, Secretarial & office administration እና web design & data base administration ባሉ 9 የስልጠና መስኮች ላይ ከስልጠና ግብዓት እና ከአሰልጣኝ መጠን አንፃር ከበቂ በላይ ስልተመዘገበባቸው ለመደበኛው የቀን ተማሪዎች አማራጭ ለመቀየር የማይስተናገድባቸው እንደሆኑ ተገልጿል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ለአዲስ ተመዝጋቢ ሰልጣኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ!!
በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2016 ዓ.ም ስልጠና ለመከታተል ላመለከቱ አዳዲስ ሰልጣኞች የግንዛቤ መስጫ መድረክ ዛሬ ህዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም ተካሄደ፡፡
በዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ በበጀት ዓመቱ በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠናቸውን ለመከታተል ያመለከቱ አዳዲስ ሰልጣኞች በዕለቱ ተገኝተዋል፡፡
በወቅቱ የኮሌጁ ዲኖች እና የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች በቦታው ተገኝተው የስልጠናውን ሂደት በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በዚህ የስልጠና ሂደት ገለፃ ላይ የሁሉም ስልጠና ክፍል ተጠሪዎች ተገኝተው ስለ ዲፓርትመንታቸው ምንነት፣ በዲፓርትመንቱ ስር ስለሚሰጡ የስልጠና መስኮች፣ እያንዳንዳቸው የስልጠና መስኮች በገበያው ላይ ያለው የስራ ፍላጎት፣ ስልጠናው የሚፈጀው የጊዜ ቆይታ እና መዳረሻቸው የት እንደሆነ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
አንዳንድ ዲፓርትመንቶች ደግሞ በሰልጣኞች የተሰሩ ምርቶችን መድረክ ላይ በማሳየት አዲስ ተመዝጋቢ ሰልጣኞች የስልጠና ክፍሉን እንዲቀላቀሉ የማስተዋወቅ እና የመቀስቀስ ስራ አከናውነዋል፡፡
አሁን ላይ አዳዲስ ሰልጣኞች ሌላ አማራጭ ፈልገው ዲፓርትመንት መቀየር ቢሹ መስተናገድ እንደሚችሉ የተገለፀ ሲሆን ነገር ግን Accounting & finance, Automotive elecetric & electronics, Automotive mechanics, Biulding electrical installation /BEI/, Fashion Designing, Hard ware & Networking Service, Marketing & Sales management, Secretarial & office administration እና web design & data base administration ባሉ 9 የስልጠና መስኮች ላይ ከስልጠና ግብዓት እና ከአሰልጣኝ መጠን አንፃር ከበቂ በላይ ስልተመዘገበባቸው ለመደበኛው የቀን ተማሪዎች አማራጭ ለመቀየር የማይስተናገድባቸው እንደሆኑ ተገልጿል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍29😢3