Waliya Entertainment
296 subscribers
1.57K photos
15 videos
758 links
ሙዚቃ እና ሙዚቃ ብቻ!!!

Follow us on social medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
Download Telegram
የመሃሙድ አህመድ የስንብት ፕሮግራም አርቲስቱን ከማስከበር ይልቅ ለገንዘብ የተሰራ ነው ሲሉ የተለያዩ አድናቂዎቹ ተናገሩ።

የመሃሙድ አህመድ የስንብት ፕሮግራም በቅርቡ በሚሊኒየም አዳራሽ በ ጆርካ ኢቨንት እና በዳኒ ዴቪስ አማካኝነት መዘጋጀቱ ይታወቃል። ምንም እንኳን አርቲስቱን ለማክበር የተዘጋጀ ፕሮግራም ቢሆንም ነገር ግን በቦታው ላይ የተገኙት አድናቂዎቹ በጣም የወረደ ዝግጅት እንደሆነ ከድምፅ ጥራት ጀምሮ በሰአቱ አለመጀመር እንዲሁም ከተጋበዙት ትላልቅ ድምፃዊያኖቹ ውስጥ የመሃሙድ ስራን የተጫወተው አንድ ሙዚቀኛ ብቻ መሆኑ እንዲሁም የ vip ትኬት የገዙት ሰዎች ልዩ ምግብ እና መጠጥ እንደሚዘጋጅላቸው ቢተዋወቅም ነገር ግን በጣም ውድ የሆኑ መጠጦችን በገንዘባቸው እንዲገዙ ዝቅ ያሉ መጠጦች እንደ ቢራ አይነቶቹ ጭራሽ እንዳይኖሩ መደረጋቸው ታዳሚዎች የተጭበረበሩ እንደመሰላቸው አዘጋጆቹ ለመሃሙድ አህመድ የማይረሳ ምሽትን ከመፍጠር ይልቅ ለራሳቸው ገንዘብ ማካበትን እንደፈለጉ ያስታውቃሉ ሲሉ የፕሮግራሙ ታዳሚዎች ቅሬታቸውን ገልፀዋል።

የፕሮግራሙ አዘጋጆች ከኢትዬፒካሊንክ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስም ለዝግጅቱ ከ42 ሚሊየን ብር በላይ ከራሳቸው ማውጣታቸውን የገለፁ ሲሆን የተለያዩ ችግሮች ቢያጋጥሟቸውም ችግሮችን በተገቢ ሁኔታ በመፍታት ሁሌም የሚኮሩበትን ዝግጅት በብቃት ማዘጋጀታቸውን ገልፀዋል።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #Mehamud_ahmed #jorkaevent
ከዚህ አንፃር ለመርሃ ግብሩ መሳካት ከውጥን ጀምሮ ተግባራዊ እስኪሆን ድረስ የደከሙት በጠቅላላ ምስጋና እንደሚገባቸው ተናግረዋል።

ያም ሆኖ ግን  ከታለመለት አላማ አንፃር ሲታይ ትልቅ ክፍተት የነበረበት ከመሆኑ ባለፈ በታሰበው ልክ መሬት ላይ ወርዷል ማለት እንደሚያዳግት የጣዕም ልኬት አዘጋጆች አንስተዋል።

ክፍተቱ የሚጀምረው መርሃ ግብሩ "የስንብት" የሚለውን ቃል መጠሪያ ከማድረጉ እንደሆነ አንስተዋል። መጠሪያው ትልቅ ክፍተት የሚፈጥር እና ከሥነ ልቦና አንፃር ሲታይ አሉታዊ ተፅዕኖው እንደሚያጋድል አዘጋጆቹ ገልፀዋል።

ከዚያ ይልቅ ማክበር እንደመሆኑ መጠን ስያሜው ያንን ተንተርሶ ሊሰጥ ይገባው እንደነበር በማንሳት መድረኩ ግቡን መቷል የሚል አመኔታ እንደሌላቸው ተናግረዋል። በጣዕም ልኬት አዘጋጆች ዕይታ በሙዚቃ ድግሱ ላይ የታዩ ክፍተቶች እንደሚከተለው ተቀምጠዋል።

👉« የመድረኩ ይዘት የተቃኘበት መንገድ ትልቅ ስህተት ነበረው፤ይህንን ያለ ይሉኝታ ማስቀመጥ ይገባል።» ብለዋል

👉ከሰዓት አከባበር ጋር በተገናኘ ትልቅ ክፍተት መፈጠሩን ተከትሎ በርካቶች ዝግጅቱን አቋርጠው ለመውጣት ከመገደዳቸው ባለፈ ጥቂት ታዳሚያን ብቻ መሀሙድ ሥራውን ሲያቀርብ መመልከታቸው  ቀዳሚው ክፍተት እንደነበር ተጠቅሷል።

👉«መሀሙድን ለማክበር የተገኙት ድምፃውያን የራሳቸውን የቀደሙ ሥራዎች እና በየምሽት ክበቡ የሚቀርቡ ሙዚቃዎችን ደግመው ማቅረባቸው ከመድረኩ አላማ ጋር የሚጋጭ ነበር። በተጨማሪም የመድረኩ ዝግጅት ላይ ምን አይነት ሥራ ይቅረብ በሚለው ዙሪያ ምንም ግንዛቤ አልነበራቸውም።»

« ከዚያ ይልቅ በእለቱ ተዋጣላቸውም አልተዋጣላቸውም ከሁሉም ድምፃውያን አንደበት የመሀሙድን ስራ ልናደምጥ ይገባ ነበር» ሲሉ አዘጋጆቹ ገልፀዋል።

👉 «መሀሙድ በወቅቱ ከነበረበት የጤና እክል አንፃር አዘጋጆቹ ብቻ ሳይሆኑ ሙዚቀኞችም ጭምር  እንዲዘፍን ፈፅሞ ማድረግ አልነበረባቸውም።»
ከእዚያ ይልቅ በመድረኩ የክብር ሥፍራ ላይ ሆኖ ቢከታተል መልካም እንደነበር አንስተዋል።

👉 የዝግጅቱ "እጥር ምጥን" ማለት አለመቻሉ ክፍተት መፍጠሩን ያነሱት የጣዕም ልኬቶች መርሃ ግብሩ ሚሊኒየም አዳራሽ የግድ እንዲሆን ከማድረግ ይልቅ ሌላ ስፍራ በመምረጥ የሙያ ምስክርነት፣ ዘጋቢ ፊልሞች፣ ስጦታዎችና ሌሎችም ጉዳዮች በተናበበ መልኩ ማድረግ ይቻል ነበር ሲሉ አንስተዋል። የምሽት ክለብ የመሰለ መርሃ ግብር መሆኑን ተከትሎ አዘጋጆቹ ሳይቀሩ ለመቆጣጠር ተቸግረው እንደነበር ገልፀዋል።

👉«ፕሮግራሙ ኮንሰርት የሚሰሩ ሰዎች እጅ ላይ መውደቁ ክፍተት ፈጥሯል ያሉት አዘጋጆቹ ኮንሰርት መሆኑ እና ገንዘብ ላይ ማተኮሩ የቀረቡት ድምፃውያን ከመሀሙድ አርቋቸዋል። » ሲሉ ሁኔታውን የገለፁ ሲሆን የመሀሙድን ስራ በተደጋጋሚ የተጫወቱ እንዲሁም የመሀሙድ ሙዚቃ ዘመን ተጋሪ ሆነው የሰሩ ባለሙያዎች ቢመረጡ መልካም ነበር ሲሉ ሃሳባቸውን ሰንዝረዋል።

ከእዚህ እና ከሌሎች ክፍተቶች እንፃር ዝግጅቱ ሀሳቡ እና መነሻው ትልቅ ተግባር ግን  አጨራረሱ  ዝቅተኛ እንደሆነ አንስተዋል።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #mehamud_ahmed