የማ (የማን) ...?!
በብርቱካን ሚደቅሳ
#Ethiopia | ለራሴ በሚገባኝ መልኩ ፈጣሪን የጠየኩት (ያልጎመጎምኩለት ) አንድ ነገር ነበር፤ ያልተሠሙትን ቃላት፣ ያልተቀመሩትን ዜማዎች ያልተሳሉትን ሥእሎች ያልተባሉትን ነገሮች ለጦብያ ልጆች አሳይላት ብዬ፡፡ አረገላት መሰለኝ ሰሞኑን……..
የጋሞ ዞኗ ቦንኬ ወረዳ የጋሽ አሰፋ ሠፈር እንደ ሆነችው ጬንቻ ተራራማ ነች አሉ፡፡ ይህን የሰማሁት ባለፈው ቅዳሜ የደጋ ሰው አልበም ድምጻዊ የማ እና ፕሮዲውሰሩ ኢዩኤልን ለማክበር በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በተዘጋጀው ውይይት ላይ በተገኘሁበት ወቅት ነው፡፡
ቦንኬ እና ማህበረሰቧ ለሙዚቃው ንሸጣ የተገኘበት ስፍራ ነው፡፡ጋሞን ሙሉ በሙሉ አውቃለሁ ብዬ ስለምኩራራ ቦንኬን ለመጀመሪያ ጊዜ የዛን ዕለት በመስማቴ ተቁነጠነጥኩ፡፡ እዛው ሆኜ አንዳንድ ማጣራቶች አረኩ፡፡ ለካ በምርጫ ቃላት ቦንኬ የምትጠራው በጎረቤቷ ወረዳ ገረሴ ነው፡፡ ሁለቱ ተዋህደው አንድ የፓርላማ መቀመጫ፡፡
ታዲያ እነ የማ ደጋነትን ለሙዚቃቸው መጠሪያ ከቦንኬ ብቻ ወስደው የጣፉት ነገር አይደለም፡ ፡የሙዚቃው እና የግጥሙ መንፈስ ከድምጻዊዋ ጋር ይዋሀድ ዘንድ ባሌ ተራራ ወጥተዋል፡፡ለእኔ ለማይሟ ለማብራራት ከባድ የሆነ የሙዚቃ ጥበባ (ግስ ነው) ተጠቅመው የደጋን ጉም እና ውርጭ የሚዘውረውን የንፋስ ድምፅ በሙዚቃው ውስጥ በስሱ እንዲሰማ አድርገዋል (የኢዩኤል ስራ ነው)፡፡ አይገርምም? ነገሩ የገባኝ የደጋ ሠውን እንደገና ቅዳሜ ማታ ስሰማው ነው፡፡
የራያ ራዩማን ነገር ካነሳሁ አውርቼ አላበቃም፤ በፍቅር ዘፈን አዘቦም ቆቦም የማ (የማን) እንደሆነ ጠይቆ ሁሉም የኛ ብሎ መመለስ እንዴት መታደል ነው?! ትርጉም የእኔ! የጎበዙን ገጣሚ ሀሳብ ወደፊት የምንሰመው ይሆናል፡፡
Telegram: https://www.t.me/waliyaentmt
በብርቱካን ሚደቅሳ
#Ethiopia | ለራሴ በሚገባኝ መልኩ ፈጣሪን የጠየኩት (ያልጎመጎምኩለት ) አንድ ነገር ነበር፤ ያልተሠሙትን ቃላት፣ ያልተቀመሩትን ዜማዎች ያልተሳሉትን ሥእሎች ያልተባሉትን ነገሮች ለጦብያ ልጆች አሳይላት ብዬ፡፡ አረገላት መሰለኝ ሰሞኑን……..
የጋሞ ዞኗ ቦንኬ ወረዳ የጋሽ አሰፋ ሠፈር እንደ ሆነችው ጬንቻ ተራራማ ነች አሉ፡፡ ይህን የሰማሁት ባለፈው ቅዳሜ የደጋ ሰው አልበም ድምጻዊ የማ እና ፕሮዲውሰሩ ኢዩኤልን ለማክበር በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በተዘጋጀው ውይይት ላይ በተገኘሁበት ወቅት ነው፡፡
ቦንኬ እና ማህበረሰቧ ለሙዚቃው ንሸጣ የተገኘበት ስፍራ ነው፡፡ጋሞን ሙሉ በሙሉ አውቃለሁ ብዬ ስለምኩራራ ቦንኬን ለመጀመሪያ ጊዜ የዛን ዕለት በመስማቴ ተቁነጠነጥኩ፡፡ እዛው ሆኜ አንዳንድ ማጣራቶች አረኩ፡፡ ለካ በምርጫ ቃላት ቦንኬ የምትጠራው በጎረቤቷ ወረዳ ገረሴ ነው፡፡ ሁለቱ ተዋህደው አንድ የፓርላማ መቀመጫ፡፡
ታዲያ እነ የማ ደጋነትን ለሙዚቃቸው መጠሪያ ከቦንኬ ብቻ ወስደው የጣፉት ነገር አይደለም፡ ፡የሙዚቃው እና የግጥሙ መንፈስ ከድምጻዊዋ ጋር ይዋሀድ ዘንድ ባሌ ተራራ ወጥተዋል፡፡ለእኔ ለማይሟ ለማብራራት ከባድ የሆነ የሙዚቃ ጥበባ (ግስ ነው) ተጠቅመው የደጋን ጉም እና ውርጭ የሚዘውረውን የንፋስ ድምፅ በሙዚቃው ውስጥ በስሱ እንዲሰማ አድርገዋል (የኢዩኤል ስራ ነው)፡፡ አይገርምም? ነገሩ የገባኝ የደጋ ሠውን እንደገና ቅዳሜ ማታ ስሰማው ነው፡፡
የራያ ራዩማን ነገር ካነሳሁ አውርቼ አላበቃም፤ በፍቅር ዘፈን አዘቦም ቆቦም የማ (የማን) እንደሆነ ጠይቆ ሁሉም የኛ ብሎ መመለስ እንዴት መታደል ነው?! ትርጉም የእኔ! የጎበዙን ገጣሚ ሀሳብ ወደፊት የምንሰመው ይሆናል፡፡
Telegram: https://www.t.me/waliyaentmt
👍1👏1
"የዘመን ቃናዎች - ፩" ነገ ይመረቃል
#Ethiopia | ከተቀነቀኑ ዘመናትን ያስቆጠሩ፣ ከአድማጩ ጆሮ ርቀው የኖሩና በስፋት ያልተደመጡ ተወዳጅ ሙዚቃዎችን ከእነነባር ቃና እና ወዘናቸው በአዲስ መልኩ በማዘጋጀት ለትውልድ ለማሻገር ታስቦ የተዘጋጀውና በወጣቱ ድምጻዊ ዳዊት ጽጌ ዳግም የተቀነቀኑ ሦስት ተወዳጅ ሙዚቃዎችን ያካተተው 'የዘመን ቃናዎች - ፩" የሙዚቃ ቪዲዮዎች
ሀሙስ፣ ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም
ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ላይ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሽ በደማቅ ሥነ ስርዓት ይመረቃል።
በአንጋፋዎቹ የአገራችን ድምጻውያን አሰፋአባተ፣ ጥላሁን ገሠሠ እና እሳቱ ተሰማ ከዘመናት በፊት የተቀነቀኑ እና በወጣቱ ድምጻዊ ዳዊት ጽጌ እንደገና ተዚመው በታላቁ የሙዚቃ ሰው አበጋዙ ክብረወርቅ ሺዎታ አቀናባሪነትና በበርካታ ባለሙያዎች ተሳትፎ የተዘጋጁ ሦስት ዘመን አይሽሬ ሙዚቃዎችን ባካተተው ''የዘመን ቃናዎች - ፩" የሙዚቃ ቪዲዮ ምረቃ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የኪነ ጥበብ ቤተሰቦች ይገኛሉ፡፡
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music
#Ethiopia | ከተቀነቀኑ ዘመናትን ያስቆጠሩ፣ ከአድማጩ ጆሮ ርቀው የኖሩና በስፋት ያልተደመጡ ተወዳጅ ሙዚቃዎችን ከእነነባር ቃና እና ወዘናቸው በአዲስ መልኩ በማዘጋጀት ለትውልድ ለማሻገር ታስቦ የተዘጋጀውና በወጣቱ ድምጻዊ ዳዊት ጽጌ ዳግም የተቀነቀኑ ሦስት ተወዳጅ ሙዚቃዎችን ያካተተው 'የዘመን ቃናዎች - ፩" የሙዚቃ ቪዲዮዎች
ሀሙስ፣ ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም
ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ላይ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሽ በደማቅ ሥነ ስርዓት ይመረቃል።
በአንጋፋዎቹ የአገራችን ድምጻውያን አሰፋአባተ፣ ጥላሁን ገሠሠ እና እሳቱ ተሰማ ከዘመናት በፊት የተቀነቀኑ እና በወጣቱ ድምጻዊ ዳዊት ጽጌ እንደገና ተዚመው በታላቁ የሙዚቃ ሰው አበጋዙ ክብረወርቅ ሺዎታ አቀናባሪነትና በበርካታ ባለሙያዎች ተሳትፎ የተዘጋጁ ሦስት ዘመን አይሽሬ ሙዚቃዎችን ባካተተው ''የዘመን ቃናዎች - ፩" የሙዚቃ ቪዲዮ ምረቃ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የኪነ ጥበብ ቤተሰቦች ይገኛሉ፡፡
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music
👍2
“ክብር ለጥበብ” የእውቅና አሰጣጥ መርሃ - ግብር አየተካሄደ ይገኛል
*
3ኛው “ክብር ለጥበብ” የእውቅና አሰጣጥ መርሃ-ግብር በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እየተካሄደ ይገኛል።
የኪነ-ጥበብ፣ ስነ-ጥበብ እና ዕደ-ጥበብ ዘርፍ ባለሙያዎች ለኢትዮጵያ ላበረከቱት አስተዋጽኦ የሚሰጥ አገር አቀፍ የእውቅና መርሃ-ግብር እንደሆነ የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚንስቴር አስታውቋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በአዋጅ ከተቋቋመበት እና ከተሰጠው ተግባርና ሀላፊነት ውስጥ አንዱ እና ዋነኛው የኪነ-ጥበብ፣ የስ-ጥበብ እና የእደ-ጥበብ ዘርፉን ተልእኮ ለማስፈጸም እንደሆነ በሥነ-ስርዓቱ ተጠቅሷል።
ተልእኮውን በማሰፈጸምና በማበረታት በጥበብ ዘርፉ ላይ የሚሰሩ ሙያተኞችን ማበረታት እና እውቅና መስጠት አንዱ የተልእኮ አካል በመሆኑ መርሃ -ግብሩ መዘጋጀቱ ተገልጿል።
በ2013ዓ.ም የተካሄደው የመጀመሪያው የእውቅናና ሽልማት መርሃ-ግብር በውድድር መልክ ሲካሄድ እንደነበር ይታወሳል። ከ2ኛው ክብር ለጥበብ የእውቅና መርሃ ግብር ጀምሮ ዝግጅቱ የውድድር ሳይሆን በሀገራችን የጥበብ ዘርፍ ላይ የራሳቸውን አሻራ ያበረከቱ እና አሁንም እያበረከቱ ለሚገኙ ባለሙያዎች እውቅና ለመስጠት ያለመ መርሃ ግብር እንደሆነ ታውቋል።
በእውቅና መርሃግብሩ በቴአትር፣ በፋሽን፣ በሙዚቃ፣ ዲጄን ጨምሮ በ12 ዘርፎች ለ50 ሙያተኞች እውቅና እንደሚሰጣቸው ይጠበቃል።
በሽልማት መርሃ ግብሩ ወጣት እና አንጋፋ የጥበብ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
Follow us on
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
*
3ኛው “ክብር ለጥበብ” የእውቅና አሰጣጥ መርሃ-ግብር በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እየተካሄደ ይገኛል።
የኪነ-ጥበብ፣ ስነ-ጥበብ እና ዕደ-ጥበብ ዘርፍ ባለሙያዎች ለኢትዮጵያ ላበረከቱት አስተዋጽኦ የሚሰጥ አገር አቀፍ የእውቅና መርሃ-ግብር እንደሆነ የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚንስቴር አስታውቋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በአዋጅ ከተቋቋመበት እና ከተሰጠው ተግባርና ሀላፊነት ውስጥ አንዱ እና ዋነኛው የኪነ-ጥበብ፣ የስ-ጥበብ እና የእደ-ጥበብ ዘርፉን ተልእኮ ለማስፈጸም እንደሆነ በሥነ-ስርዓቱ ተጠቅሷል።
ተልእኮውን በማሰፈጸምና በማበረታት በጥበብ ዘርፉ ላይ የሚሰሩ ሙያተኞችን ማበረታት እና እውቅና መስጠት አንዱ የተልእኮ አካል በመሆኑ መርሃ -ግብሩ መዘጋጀቱ ተገልጿል።
በ2013ዓ.ም የተካሄደው የመጀመሪያው የእውቅናና ሽልማት መርሃ-ግብር በውድድር መልክ ሲካሄድ እንደነበር ይታወሳል። ከ2ኛው ክብር ለጥበብ የእውቅና መርሃ ግብር ጀምሮ ዝግጅቱ የውድድር ሳይሆን በሀገራችን የጥበብ ዘርፍ ላይ የራሳቸውን አሻራ ያበረከቱ እና አሁንም እያበረከቱ ለሚገኙ ባለሙያዎች እውቅና ለመስጠት ያለመ መርሃ ግብር እንደሆነ ታውቋል።
በእውቅና መርሃግብሩ በቴአትር፣ በፋሽን፣ በሙዚቃ፣ ዲጄን ጨምሮ በ12 ዘርፎች ለ50 ሙያተኞች እውቅና እንደሚሰጣቸው ይጠበቃል።
በሽልማት መርሃ ግብሩ ወጣት እና አንጋፋ የጥበብ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
Follow us on
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
የማስተዋል እያዩ "እንዚራ" አልበም መቼ ይለቀቃል? ⏳
"እጅግ የማከብራቹ ውድ አድናቂዎቼ እና መላው የሙዚቃ አድማጮቼ በቅድሚያ ላሳያችሁኝ ውዴታ እና አክብሮት ከልቤ አመሰግናለው።
እነሆ "እንዚራ" የተሰኘውን የመጀመሪያ አልበሜን ወደ እናንተ ለማድረስ አሰናድተን የጨረስን ሲሆን የካቲት 1 ቀን 2016 ዓ.ም በኤላ ቲቪ አማካኝነትም በተለያዩ አማራጮች ይለቀቃል እናተም አንደወትሮው አድምጣችሁ አስተያየታችሁን እንደምታደርሱኝ ባለሙሉ ተስፋ ነኝ።" - ማስተዋል እያዩ
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music
"እጅግ የማከብራቹ ውድ አድናቂዎቼ እና መላው የሙዚቃ አድማጮቼ በቅድሚያ ላሳያችሁኝ ውዴታ እና አክብሮት ከልቤ አመሰግናለው።
እነሆ "እንዚራ" የተሰኘውን የመጀመሪያ አልበሜን ወደ እናንተ ለማድረስ አሰናድተን የጨረስን ሲሆን የካቲት 1 ቀን 2016 ዓ.ም በኤላ ቲቪ አማካኝነትም በተለያዩ አማራጮች ይለቀቃል እናተም አንደወትሮው አድምጣችሁ አስተያየታችሁን እንደምታደርሱኝ ባለሙሉ ተስፋ ነኝ።" - ማስተዋል እያዩ
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music
👍1🔥1
የዘመን ቃናዎች ቁጥር 1
*
የዘመን ቃናዎች ቁጥር 1 የሙዚቃ ቅጂዎች ማስተዋወቂያ ተካሂዷል።
ለዛቸው ከፍ ያለ፣ በትናንት ትዝታ ውስጥ ያሉ፣ ተወዳጅና ለጆሮ የሚስማሙ፤ ነገር ግን በጊዜ ዑደት የተረሱ፣ በደንብ ያልተደመጡ 3 ዜማዎች በነበራቸው ቃና የአሁኑን ዘመን የዋጁ እንዲሆኑ በግጥም ተስተካክለው በድምፃዊ ዳዊት ፅጌ አማካኝነት ለአድማጮች ቀርበዋል።
የሙዚቃ ዝግጅቱ በተለያዩ ምክንያቶች 2 ዓመት እንደፈጀ ተነግሯል።
ሙዚቃውን አንጋፋው የሙዚቃ አቀናባሪ አበጋዝ ክብረወርቅ ሽወታ ያቀናበረው ሲሆን፤ ከድምፃዊ ዳዊት ፅጌ ጋር በጋራ ፕሮዲዩስ አድርገውታል።
ሙዚቃዎቹ በ1950፣ 60 እና 70ዎቹ የተሰሩ ሲሆኑ፤ ሁሉም ከባንድ ጋር በመድረክ የተቀዱ ናቸው።
ሥራው አድካሚ ቢሆንም ትናንትን የዘከርንበት፣ እኔም ሕልሜን የኖርኩበት ነው ያለው ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ፤ ሁለተኛ አልበሙም በቅርቡ ለአድማጭ ጆሮ እንደሚደርስ ተናግሯል።
የሙዚቃ አቀናባሪው አበጋዝ ክብረወርቅ ሽወታም የአስቴርና የጋሽ ጥላሁንን የቆዩ ዜማዎች በድጋሚ ሰርተናል፤ ይህንንም በዛ ልክ ሰርተነዋል ብሏል።
በሙዚቃ አጃቢነት፥ መስፍን ሽፈራው፣ መስፍን ሙላት እና ሜላት ቀለመወርቅ ተሳትፈዋል።
የዜማ ደራሲ አየለ ማሞ፣ የድምፃዊ እሳቱ ተሰማ፣ የድምፃዊ አሰፋ አባተ እና የድምፃዊ ጥላሁን ገሰሰ ቤተሰቦች ዜማዎቹ እንዲሰሩ ስለፈቀዱም ምስጋና ቀርቦላቸዋል።
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music
*
የዘመን ቃናዎች ቁጥር 1 የሙዚቃ ቅጂዎች ማስተዋወቂያ ተካሂዷል።
ለዛቸው ከፍ ያለ፣ በትናንት ትዝታ ውስጥ ያሉ፣ ተወዳጅና ለጆሮ የሚስማሙ፤ ነገር ግን በጊዜ ዑደት የተረሱ፣ በደንብ ያልተደመጡ 3 ዜማዎች በነበራቸው ቃና የአሁኑን ዘመን የዋጁ እንዲሆኑ በግጥም ተስተካክለው በድምፃዊ ዳዊት ፅጌ አማካኝነት ለአድማጮች ቀርበዋል።
የሙዚቃ ዝግጅቱ በተለያዩ ምክንያቶች 2 ዓመት እንደፈጀ ተነግሯል።
ሙዚቃውን አንጋፋው የሙዚቃ አቀናባሪ አበጋዝ ክብረወርቅ ሽወታ ያቀናበረው ሲሆን፤ ከድምፃዊ ዳዊት ፅጌ ጋር በጋራ ፕሮዲዩስ አድርገውታል።
ሙዚቃዎቹ በ1950፣ 60 እና 70ዎቹ የተሰሩ ሲሆኑ፤ ሁሉም ከባንድ ጋር በመድረክ የተቀዱ ናቸው።
ሥራው አድካሚ ቢሆንም ትናንትን የዘከርንበት፣ እኔም ሕልሜን የኖርኩበት ነው ያለው ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ፤ ሁለተኛ አልበሙም በቅርቡ ለአድማጭ ጆሮ እንደሚደርስ ተናግሯል።
የሙዚቃ አቀናባሪው አበጋዝ ክብረወርቅ ሽወታም የአስቴርና የጋሽ ጥላሁንን የቆዩ ዜማዎች በድጋሚ ሰርተናል፤ ይህንንም በዛ ልክ ሰርተነዋል ብሏል።
በሙዚቃ አጃቢነት፥ መስፍን ሽፈራው፣ መስፍን ሙላት እና ሜላት ቀለመወርቅ ተሳትፈዋል።
የዜማ ደራሲ አየለ ማሞ፣ የድምፃዊ እሳቱ ተሰማ፣ የድምፃዊ አሰፋ አባተ እና የድምፃዊ ጥላሁን ገሰሰ ቤተሰቦች ዜማዎቹ እንዲሰሩ ስለፈቀዱም ምስጋና ቀርቦላቸዋል።
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music
❤1
አርቲስት ጌታቸው ኃ/ማርያም "ወጣቱ ትውልድ በትውልድ ቅብብሎሽ የወረሰውን ሀገር ወዳድነት እና አንድነት ማስቀጠል አለበት" ሲል በባሕል ማዕከል በነበረውው የኪነ-ጥበብ ምሽት ላይ ተናገረ።
***
አርቲስት ጌታቸው በባሕል ማዕከል በነበረውው የኪነ-ጥበብ ምሽት የክብር እንግዳ ሆኖ በቀረበበት መድረክ ባስተላለፈው መልዕክት ወጣቱ ትውልድ በትውልድ ቅብብሎሽ የተረከባትን ሀገሩን መውደድ እና አንድነቱንም አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ገልጿል።
ኢትዮጵያን ለማስቀጠል ጠንካራ የስራ ባህል እና ምክናታዊነት ብሎም ችግሮችን ወደ እድል እየቀየሩ የመፍትሔ አካል መሆን ከወጣቱ ትውልድ የሚጠበቅ ሀላፊነት ስለመሆኑም አርቲስት ጌታቸው በስፋት አውስቷል።
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music
***
አርቲስት ጌታቸው በባሕል ማዕከል በነበረውው የኪነ-ጥበብ ምሽት የክብር እንግዳ ሆኖ በቀረበበት መድረክ ባስተላለፈው መልዕክት ወጣቱ ትውልድ በትውልድ ቅብብሎሽ የተረከባትን ሀገሩን መውደድ እና አንድነቱንም አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ገልጿል።
ኢትዮጵያን ለማስቀጠል ጠንካራ የስራ ባህል እና ምክናታዊነት ብሎም ችግሮችን ወደ እድል እየቀየሩ የመፍትሔ አካል መሆን ከወጣቱ ትውልድ የሚጠበቅ ሀላፊነት ስለመሆኑም አርቲስት ጌታቸው በስፋት አውስቷል።
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music
👍1
የክብር ዶክተር ጋሽ ሙላቱ አስታጥቄ ከአድናቂዎቹ ጋር ራት የሚበላበት ምሽት ሊካሄድ ነው።
በሀገራችን በጃዝ ሙዚቃው ዘርፍ የጃዝ አባት በመባል የሚታወቀውና በሙያው ከ50 አመታት በላይ የሰራው የክብር ዶክተር ሙላቱ አስታጥቄ የካቲት 9/2016 ዓ/ም በግዮን ሆቴል በሚገኘው በአፍሪካ ጃዝ መንደር ከአድናቂዎቹ ጋር ተገናኝቶ ራት ይበላል ፊርማውንም ያስቀምጣል።
በዝግጅቱ ላይ ተጋባዥ እንግዶች እና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችም እንደሚገኙ የታዋቂ ኤቨንት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሳሙኤል አበራ ተናግረዋል።
ታዋቂ ኤቨንት ከእዚህ በፊት የተለያዩ ኤቨንቶችን በማዘጋጀት የሚታወቅ ሲሆን ይሄን ዝነኞችን ከአድናቂዎቻቸው ጋር የማገናኘቱን ስራ ሲያከናውን ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
ከእዚህ በፊት አርቲስት ሰላም ተስፋዬን በሸራተን አዲስ ሆቴል ከአድናቂዎቿ ጋር በማገናኘት ራት የመብላትና የፎቶ ግራፍ መነሳት መርሀ ግብር ማካሄዱ የሚታወስ ነው።
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music
በሀገራችን በጃዝ ሙዚቃው ዘርፍ የጃዝ አባት በመባል የሚታወቀውና በሙያው ከ50 አመታት በላይ የሰራው የክብር ዶክተር ሙላቱ አስታጥቄ የካቲት 9/2016 ዓ/ም በግዮን ሆቴል በሚገኘው በአፍሪካ ጃዝ መንደር ከአድናቂዎቹ ጋር ተገናኝቶ ራት ይበላል ፊርማውንም ያስቀምጣል።
በዝግጅቱ ላይ ተጋባዥ እንግዶች እና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችም እንደሚገኙ የታዋቂ ኤቨንት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሳሙኤል አበራ ተናግረዋል።
ታዋቂ ኤቨንት ከእዚህ በፊት የተለያዩ ኤቨንቶችን በማዘጋጀት የሚታወቅ ሲሆን ይሄን ዝነኞችን ከአድናቂዎቻቸው ጋር የማገናኘቱን ስራ ሲያከናውን ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
ከእዚህ በፊት አርቲስት ሰላም ተስፋዬን በሸራተን አዲስ ሆቴል ከአድናቂዎቿ ጋር በማገናኘት ራት የመብላትና የፎቶ ግራፍ መነሳት መርሀ ግብር ማካሄዱ የሚታወስ ነው።
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music
👍1
👤 Dawit tsige | ዳዊት ፅጌ
🎵 Yezemen Kana | የዘመን ቃና
━━━━━━━━━━━━━━
➠ RELEASED: 2024
➠ GENRE: #Ethiopian
➠ TYPE: #Album
➠ TRACKS: 3
➠ FORMATS: #Mp3
➠ CHANNEL: @Waliyaentmt
━━━━━━━━━━━━
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Dawit_tsige #Album #Ethio_albums #Waliya_Entertainemnt
🎵 Yezemen Kana | የዘመን ቃና
━━━━━━━━━━━━━━
➠ RELEASED: 2024
➠ GENRE: #Ethiopian
➠ TYPE: #Album
➠ TRACKS: 3
➠ FORMATS: #Mp3
➠ CHANNEL: @Waliyaentmt
━━━━━━━━━━━━
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
#Dawit_tsige #Album #Ethio_albums #Waliya_Entertainemnt
👍1
የሰርፀ ፍሬስብሃት መልዕክት
#Ethiopia | ስለ ዳዊት ጽጌ የተዋጣለት ድምፃዊነት ዛሬ ምን ዐዲስ ነገር መናገር ይቻላል? ኹሉ የመሠከረለት ዜማ የሚኩል እና ሸምኖ የሚቋጭ አዚያሚ ነው። በሙያም በግብረ ገብም ማንነቱን ያስመሠከረ የዘመን አርአያ ነው።
ወደ ኋለኛው የኢትዮጵያ ሙዚቃ ዘመን መለስ ብሎ፥ "ወትረ ኅልው" (classic) የምንላቸውን ዜማዎች ተጫውቶ አዳመጥኳቸው። እጅግ በሚገርም ብቃት እና ዘመን አሻጋሪ በኾነ መንፈስ ውብ አድርጎ ነው ያዜማቸው። የተመረጡት ሙዚቃዎችም በተሠጡት ጋዜጣዊ መግለጫዎች ላይ እንደተወሳው፣ ከዘወትር ድምጫችን የራቁ እና በቀላሉ የማናገኛቸው ሥራዎች ናቸው።
አበጋዙ ክብረወርቅ ሺዎታ፥ በተለመደ የሙያ አክብሮት እና ጥንቃቄው፣ የቀደሙ አቀናባሪዎችን አሻራ እንዳይለቅ አድርጎ በዘመን Expression የተጌጠ Adaptation እና Re-Arrangement የተዋሐዱበት ፕሮዳክሽን አስደምጦናል። የጥላሁን ገሠሠን፣ የማሕሙድ አሕመድን፣ የዓለማየሁ እሸቴን፣ የምኒልክ ወስናቸውን፣ የአስቴር ዐወቀን፣ የተፈራ ካሣን (በግርማ ተፈራ) ሥራዎች፤ በልዩ ጥራት እና ከፍታ (ራሳቸውን ድምፃውያኑን ባሳመነ ብቃት) ፕሮዲውስ ማድረጉ ይታወቃልና፣ እንዲህ ያለውን ፕሮዳክሽን እንዴት re-arrange ሊያደርገው እንደሚችል መገመት አይሳነንም ።
የሙዚቃ መሣሪያዎቹ formation እና የሙዚቀኞቹ የየግል ብቃት ብዙ የሚያስጽፍ፣ ምሁራን ሙዚቀኞችን ያገናኘ አስደናቂ መሰባሰብ ነው። እንደ አንድ ኦርኬስትራ ወይም ባንድ አብረው ብናያቸው ኹሌም የምመኛቸውን ሙዚቀኞች ይህ ፕሮዳክሽን ማገናኘት ችሏልና በጣም ደስ ይላል።
እያንዳንዱ ሥራ የራሱ ፈተና ስላለው፥ ይሄኛውም ለሙዚቀኞቹ ፈተና ይኖረዋል። ግን የተሳካለት ስሜት ሰጪ ፕሮዳክሽን መሠራቱን መመስከር ይቻላል።
#Ethiopia | ስለ ዳዊት ጽጌ የተዋጣለት ድምፃዊነት ዛሬ ምን ዐዲስ ነገር መናገር ይቻላል? ኹሉ የመሠከረለት ዜማ የሚኩል እና ሸምኖ የሚቋጭ አዚያሚ ነው። በሙያም በግብረ ገብም ማንነቱን ያስመሠከረ የዘመን አርአያ ነው።
ወደ ኋለኛው የኢትዮጵያ ሙዚቃ ዘመን መለስ ብሎ፥ "ወትረ ኅልው" (classic) የምንላቸውን ዜማዎች ተጫውቶ አዳመጥኳቸው። እጅግ በሚገርም ብቃት እና ዘመን አሻጋሪ በኾነ መንፈስ ውብ አድርጎ ነው ያዜማቸው። የተመረጡት ሙዚቃዎችም በተሠጡት ጋዜጣዊ መግለጫዎች ላይ እንደተወሳው፣ ከዘወትር ድምጫችን የራቁ እና በቀላሉ የማናገኛቸው ሥራዎች ናቸው።
አበጋዙ ክብረወርቅ ሺዎታ፥ በተለመደ የሙያ አክብሮት እና ጥንቃቄው፣ የቀደሙ አቀናባሪዎችን አሻራ እንዳይለቅ አድርጎ በዘመን Expression የተጌጠ Adaptation እና Re-Arrangement የተዋሐዱበት ፕሮዳክሽን አስደምጦናል። የጥላሁን ገሠሠን፣ የማሕሙድ አሕመድን፣ የዓለማየሁ እሸቴን፣ የምኒልክ ወስናቸውን፣ የአስቴር ዐወቀን፣ የተፈራ ካሣን (በግርማ ተፈራ) ሥራዎች፤ በልዩ ጥራት እና ከፍታ (ራሳቸውን ድምፃውያኑን ባሳመነ ብቃት) ፕሮዲውስ ማድረጉ ይታወቃልና፣ እንዲህ ያለውን ፕሮዳክሽን እንዴት re-arrange ሊያደርገው እንደሚችል መገመት አይሳነንም ።
የሙዚቃ መሣሪያዎቹ formation እና የሙዚቀኞቹ የየግል ብቃት ብዙ የሚያስጽፍ፣ ምሁራን ሙዚቀኞችን ያገናኘ አስደናቂ መሰባሰብ ነው። እንደ አንድ ኦርኬስትራ ወይም ባንድ አብረው ብናያቸው ኹሌም የምመኛቸውን ሙዚቀኞች ይህ ፕሮዳክሽን ማገናኘት ችሏልና በጣም ደስ ይላል።
እያንዳንዱ ሥራ የራሱ ፈተና ስላለው፥ ይሄኛውም ለሙዚቀኞቹ ፈተና ይኖረዋል። ግን የተሳካለት ስሜት ሰጪ ፕሮዳክሽን መሠራቱን መመስከር ይቻላል።