Waliya Entertainment
296 subscribers
1.57K photos
15 videos
758 links
ሙዚቃ እና ሙዚቃ ብቻ!!!

Follow us on social medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
Download Telegram
በቀደምት ጀግኖች አያቶቻችን ታላቅ ተጋድሎ እና መስዋዕትነት እንዲሁም በታላቁ ታሪክ የማይረሳው ንጉሳችን ዳግማዊ አጤ ምንሊክ እና በእቴጌ ጣይቱ ብጡል ብልህ አመራር እና አስተባባሪነት ለተቀዳጀነው አንፀባራቂው የ፻፳ ወ፱ኛው የአድዋ ድል በዓል እንኳን አደረሳችሁ የሚል መልዕክቴን ሳስተላልፍ በታላቅ ብሔራዊ ኩራት ነው::

ይህ በታሪክ ተመዝግቦ በየአመቱ የምንዘክረው አድዋ ላይ የተቀዳጀነው ድል የኢትዮጵያን ነፃነት ያስከበረ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ የቅኝ ግዛት ቀንበር ተጭኗቸው ሲሰቃዩ ለነበሩ አፍሪካዊያን ወንድም እና እህቶቻችን እንዲሁም በመላው አለም በጭቆና ውስጥ የነበሩትን ጥቁር ህዝቦች ቀና ብለው እንዲሄዱ እና ነፃ እንዲወጡ በወቅቱ ታላቅ መነቃቃትን የፈጠረ ገናና የጥቁር ህዝቦች ድል ነው።

የዘንድሮውን የ፻፳ ወ፱ ኛው የአድዋ ድል በአል ስናከብር ሀገራችን ኢትዮጵያ ላለፉት ቀላል ለማይባሉ አመታት አንድነቷን አስጠብቃ ወደ ፊት እንዳትራመድ ሰቅዞ የያዛትን ተከታታይ የብሔር ፖለቲካ አዙሪት እንደ ሀገር እና እንደ ህዝብ ያስከፈለንን እና እያስከፈለን ያለውን ዋጋ ግምት ውስጥ በማስገባት ካለንበት ውስብስብ እና እጅግ ኋላቀር የዘር ፖለቲካ ለመውጣት ከመቼውም ጊዜ በላቀ አንድነታችንን አስተባብረን የህልውናችን መሰረት የሆነችው እናት ሀገራችንን ለማዳን በንቃት መቆም ይጠበቅብናል።

<<ምንሊክ ጥቁር ሰው!>>

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ቴዎድሮስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #teddy_afro #adwa
ተወዳጁ የባህል ሙዚቀኛ አስቻለው ፈጠነ በኦንላይን ገበያ መጣ!!

ታሪክና ባህል በተሸከሙ ሙዚቃቹ ስምና በልዩ ልዩ ታሪካዊ ፎቶዎች የታተሙ ደረጃቸውን የጠበቁ ቲሸርቶችን በኦንላይን ገበያ አቀረበ።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #aschalewu_fetene
እንኳን ለ129ኛው የዓድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መልካም የድል በዓል እንዲሆን ከልብ እንመኛለን።

ዓድዋ
👉የነፃነት_አርማ
👉የጥቁር_ሕዝቦች_ድል
👉የአንድነት_ተምሳሌት
👉አድዋ ኢትዮጵያዊነት።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #adwa
አንጋፋው ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ በልዩ ስጦታ በወዳጅ ዘመዶቹ ተሸለመ

#Ethiopia | የትዝታው ንጉስ ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ ለሀገራችን የሙዚቃ ዘርፍ ላደረገው አስተዋፅዖ ያላቸውን አድናቆት ለመግለጽ በመኖሪያ ቤቱ በመገኘት ከወዳጅ እና ቤተሰቦቹ ከልብ የመነጨ አድናቆትን አግኝቷል።

በፕሮግራሙ ላይ ለታዋቂው ድምፃዊ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ለበርካታ አመታት ላበረከቱት ትሩፋት ያላቸውን ጥልቅ አክብሮት እና ምስጋና የሚገልጽ የወርቅ ሃብል ተበርክቶለታል።

ድምፃዊዉ ዘመን እና ጊዜ የማይሽራቸውን ስራዎችን በመስራትየሚታወቀው ማህሙድ አህመድ የሀገሪቱን የባህልና የሙዚቃ ገጽታ ለዓለም በማስተዋወቅ በኩል ትልቅ ሚና ተጫውቷል።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #mehamu_ahmed
ድምፃዊት ቬሮኒካ አዳነ አዲስ ነገር ይዛ እየመጣች ትገኛለች…

ድምፃዊት ቬሮኒካ አዳነ የበኩር አልበምዋን "መጠርያዬ" የተሰኘ የሙዚቃ አልበም ይዛ መምጣትዋን አይዘነጋም፡፡

ሁል -ጊዜ አዳዲስ ጉዳዮችን ይዛ ብቅ የምትለው ወጣቷ ድምፃዊት ከሰሞኑ የሚለቀቁ ቪድዮች እንደ ሚኖሩም ገልፃለች፡፡ በራስዋ የማህበራዊ ትስስር ገፅ ላይ እንዲህ ስትል ለአድናቂዎቿ የሙዚቃ አድማጮች በሙሉ አድርሳለች፡፡

…"አንድ አንዴ ፈጣሪን ማመስገኛ ቃል አጣለሁ ተመስገን…በጣም የማከብረው ድርጅት ጋር የBrand Ambassader የመሆን ስምምነት ላይ ደርሰናል፡፡ እሱ ብቻ ሳይሆን ነገ የምለቀውን ቪድዮ ሙሉ በሙሉ ገዝተውታል፡፡ የኔ ደስታ የሚያስደስታችሁ ቤተሰቦቼ እንኳን ደስ አላችሁ፡፡
ለማንኛውም የነገው አዲስ ነገር በMarch 8 በveronica Adane Youtube Channel የሚለቀው በውስጡ ያለው 12 ቪድዮ ነው ብዙ ደክመውበታል እንደ ምትወዱት አልጠራጠርም" ስትል ገልፃለች፡፡

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #veronica_adane
ድምጻዊ አስቻለው በእሥራኤል 🇮🇱

በተለየ የአዚያዚያም ስልቱ ፤
በሀገረሰባዊ የአከዋወን ብቃቱ፤ የምናውቀው ‼️
በ "እናትዋ ጎንደር " የሙዚቃ አፍቃሪውን ልብ ከፍቶ የገባው፤
በ "አስቻለ" አልበሙ ብቃቱን አስመስክሮ "አሞራው ካሞራ" ን የመረቀን ፤
ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ‼️

የመጀመሪያ ኮንሰርቱን በእሥራኤል 🇮🇱 ሊያቀርብ ነው‼️

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #aschalewu_fetene
"ኪነ ጥበብን በኃላፊነት ተጠቅመን የተሻለ አብሮነት፣ ፍቅርና መከባበር እንዲኖር እንሰራን "- የሙዚቃ ባለሙያዎች

የሙዚቃ ባለሙያው ካሙዙ ካሳ እንደተናገረው፣ ኢትዮጵያ እዚህ የደረሰችው በአብሮነት በመሆኑ ነገንም ለመቀጠል አብሮነት እንደሚያስፈልግ ገልጻል፡፡ ስለአብሮነት ሁሌም መነገር፣መነሳት ማስታወስ አስፈላጊ ነው ያለው የሙዚቃ ባለሞያ ካሙዙ፣ለኢትዮጵያዊያን አብሮነት አዲስ አይደለም በአብሮነት የኖረ ህዝብ ነው ብሏል፡፡

በአብሮነት ችግርን መቅረፍ ጠላትን፣ ኑሮን ማሸነፍ፣ ድል መንሳት እንደሚቻል ገልጾ፣ በኪነ ጥበብ ፍቅር፣አንድነትና ጀግንነትን መግለጽ እንደሚቻል ተናግሯል።

ቀደም ሲል በነበሩ አባቶች፣ወጣት ድምጻዊያን ብዙ ተሰርቷል፣ወደፊትም ይሰራል። ኪነ ጥበብ በኃላፊነት ሰዎች ያላዩበትን መንገድ ማሳየት ፍቅርን ፣አብሮነትን መስበክ፣ሰዎችን ለመልካም ነገር ማነሳሳት መሆኑን አስረድቷል፡፡

ወጣቱ ትውልድ አብሮነት ከሌለ ምንም ነገር መሆን እንደማይችል ማወቅ እንዳለበትና መከፋፈሉ፣ መለያየቱ የማይጠቅም ነገር መሆኑን ሊረዳ ይገባል። መከፋፈልን ትተን በአንድነት፣ በመተሳሰብና ይቅር በመባባል የተሻለች ሀገር ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ አለብን ብሏል፡፡

ድምጻዊት ሃይማኖት ግርማ በበኩሏ፣ህዝባችን ከንግግር በላይ በተግባር አብሮ ይኖር ነበር፣ ወደፊትም ይኖራል፡፡ በሥራም በማንኛውም ጉዳይ የሆነ አካባቢ ሲኬድ ኢትዮጵያ ውስጥ ሁሉም ጋር ጥሩ ነገር አለ። በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያለው አብሮነት የሚያስደስት ነው ብላለች፡፡

ሙዚቃ ትልቁ ሥራው ፍቅር፣አብሮነትን፣መልካም ነገርን፣የሰዎች መቀራረብን መስበክ መሆኑን በመግለጽ፣ወደፊትም በሰዎች መካከል አብሮነትን የሚያጸኑ ሥራዎችን እንደሚያስቀጥሉ ተናግራለች፡፡

@waliyaentmt
@waliyaentmt
@waliyaentmt
ተወዳጇ ድምጻዊት ትዕግስት አፈወርቅ በሞት ባጣነው ወንድሟ ተወዳጁ ድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ስም 100 ሺህ ብር የለገሰች ሲሆን አንዲሁም በየአመቱ የድምጻዊውን ሙት አመት በማስመልከት 100 ሺህ ብር ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብታለች፡፡

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #madingo #tigist
የድምጻዊ አንዷለም ጎሳ ሚስት ቀነኒ አዱኛ በድገንት ሂወቷ አለፈ።

የተወዳጁ ኦሮሚኛ ሙዚቃ አቀንቃኝ አንዱአለም ጎሳ ሚስት የሆነችው ቀነኒ እስካሁን ባልታወቀ ምክንያት ህይወቷን እንዳጣች መረጃ ቢገኝም ስለአሟሟቷ ፖሊስ በማጣራት ላይ ይገኛል።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #Andualem_gossa
አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ድምፃዊ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ፣ መሰንቆና ዋሽንት ተጫዋች፣ ክራርና በገና ደርዳሪ፣ የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ መምህር የሆኑት አለማየሁ ፋንታ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ከ1960 ዓ.ም ጀምሮ በያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ውስጥ ከማስተማርም በዘለለ ትምህርት ቤቱ ሲከፈት የባህል ሙዚቃ ትምህርትን ለተማሪዎች እንዲሆን አድርገው ካሪኩለም በማዘጋጀት ከፍተኛ ሚናን ተጫውተዋል።

ውልደትና እድገታቸው በአሁኑ የዋግምራ ዞን ሰቆጣ አካባቢ ሲሆን፣ በልጅነታቸው በድቁና ማዕረግ ቤተክርስቲያንን አገልግለዋል፡፡

ሙዚቃን የጀመሩት በሀገር ፍቅር ቴአትር ሲሆን ከ1950 ዓ.ም ጀምሮ ለአስር ዓመታት ያህል በክፍሉ ሰርተዋል፡፡ የኢትዮጵያን የባህል ሙዚቃ በመወከል በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በአሜሪካና በእስያ በርካታ ሀገራትንም ተዟዙረዋል።

በእንግሊዝ፣ ስዊድን፣ ኖርዌይ፣ ጀርመን፣ ኦስትሪያና ሌሎችም በርካታ የአውሮፓ ሃገራት የባህል ሙዚቃ አምባሳደርነት ማዕረግን ያገኙ ሲሆን፣ ከዚህም በተጨማሪ በ1968 ዓ.ም ከዳካር የኔግሮ አርትስ ፌስቲቫል ሽልማት ከዩኔስኮ ለሙዚቃ ስራዎቻቸው እውቅና ፣ ከኮርያ ስፕሪንግ ፍሬንድ ሺፕ አርት ፌስቲቫል ዲፕሎማና የክብር ሜዳሊያና መሰል በርካታ ሽልማቶችንም አግኝተዋል::

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ስርዓተ ቀብራቸው በነገው ዕለት ፒያሳ በሚገኘው በገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ በ9 ሰዓት እንደሚፈፀምም ታውቋል።

Follow us on
Telegram - https://t.me/waliyaent