Waliya Entertainment
296 subscribers
1.57K photos
15 videos
758 links
ሙዚቃ እና ሙዚቃ ብቻ!!!

Follow us on social medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
Download Telegram
ተወዳጁ ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ በዱባዩ ኮንሰርት ምንም ክፍያ እንዳልተከፈለው አሳወቀ።

ትላልቅ ኮንሰርቶችን በዱባይ በማዘጋጀት የሚታወቀው G-power የተሰኘው ኩባንያ "የመስቀል ወፍ" የተሰኘ በኢትዬጲያ የሙዚቃ ታሪክ ስመጥር የሆኑትን አስቴር አወቀን እና ጎሳዬ ተስፋዬን በመጋበዝ ትልቅ ዝግጅት እንዳዘጋጀ የሚታወቅ ነው። ሆኖም ግን ተወዳጁ ሙዚቀኛ ጎሳዬ ተስፋዬ ምንም አይነት ክፍያ እንዳልተከፈለው ወይም ስምምነት ላይ እንዳልደረሱ ነገር ግን አድናቂዎችን በማክበር ብቻ በቦታው ላይ ያለምንም ክፍያ እንደተገኘ አስታውቋል።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #Gossaye_tesfaye #Aster_aweke
🎂መልካም ልደት ለ አርቲስት ኤሊያስ የማነ (ኪዊ)🎂

በ90 ዎቹ ገነው ከነበሩ ሙዚቃዎች መሀል "ይበቃል" የተሰኘ በብዙዎቹ ዘንድ ተወዳጅ የነበረውን ሙዚቃን እና "አንቺ ስትሳሚ" የተሰኘ አልበምን በሙዚቃ ሊቅ ኤልያስ መልካ አቀናባሪነት ያደረሰን ሲሆን በህትመት ላይ ባጋጠመ መጠነኛ እክል ምክንያት አልበሙ ከገበያ ላይ እንደተሰበሰበ የምናስታውሰው ነው። ወደፊት በድጋሚ ገበያ ላይ ለማዋልም እየተሰራ እንደሆነ ከአንዳንድ ምንጮች መረዳትም ችለናል።

ኤልያስ ኪዊ መኖሪያውን ከሃገር ውጪ በተለያዩ ሀገራት ያደረገ ሲሆን በአሁኑ ሰአት በአውስትራሊያ እየኖረ ይገኛል ከአንድ አመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት በዝክረ ኤልያስ መልካ 3 ላይ ተገኝቶ ከኤልያስ ጋር የነበራቸውን ትውስታ በሰፊው አካፍሎን እንደነበር የሚታወስ ነው።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #kiwi
ከ100 በላይ ሰዎች ራፐሩ ዲዲ ወሲባዊ ጥቃት ፈፅሞብናል ሲሉ አዲስ ክስ መሠረቱ።

ወሲባዊ ጥቃት በማድረስ፣ በመድፈር እና የወሲባዊ ብዝበዛ በመፈጸም በሚሉ ወንጀሎች ነው ታዋቂው ሙዚቀኛ ላይ አዲስ ክስ የሚመሠረተው።

የቴክሳስ ግዛቱ ጠበቃ ቶኒ በዝቢ እንደሚሉት ከከሳሾቹ መካከል አንዳንዶች ገና የዘጠኝ ዓመት ሕፃን ሳሉ ነው ወንጀሉ የተፈፀመባቸው።

ዲዲ በተሰኘ የመድረክ ስሙ የሚታወቀውን ራፐር የሚወክሉት ጠበቃ ኤሪካ ዎልፍ ደንበኛቸው ክሱን “እንደማይቀበል” ገልፀው “ሐሰተኛ እና ስም አጥፊ ናቸው” ብለዋል።

ማክሰኞ ዕለት ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ጠበቃ በዝቢ “ሁሉንም ማስረጃ አሰባስበን ሌሎች በድርጊቱ የተሳተፉ ሰዎችን ለሕግ እናቀርባለን” ብለዋል።

የዲዲ ጠበቃ ለቢቢሲ በላኩት መግለጫ ደንበኛቸው “ችሎት ፊት ሲቀርብ እውነቱን በማፍረጥረጥ ንፁህ ስሙን ለማደስ” እንደቸኮለ አመልክተዋል።

እስር ላይ የሚገኘው ዲዲ በቅርብ ጊዜያት በርካታ ክሶች እየቀረቡበት ይገኛሉ።

ባለፈው ሳምንት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋለው ዲዲ በማጭበርበር እና በወሲባዊ ጥቃት ላይ በመሰማራት ነው የተጠረጠረው። ዋስትና ጠይቆ የተከለከለው ራፐር የፌዴራል ማረሚያ ቤት ይገኛል። ራፐሩ ውድቅ የተደረገበት ዋስትና ድጋሚ እንዲታይ ይግባኝ ጠይቋል።

ዲዲ የቀረቡበትን ሁሉንም ክሶች አልፈፀምኩም በማለት ያስተባብላል።

አሁን ከ120 በላይ ክሶች የተመሠረቱበት ሲሆን፣ ጠበቃው እንደሚሉት ከ100ዎቹ ከሳሾች መካከል ግማሾቹ ሴቶች ቀሪዎቹ ደግሞ ወንዶች ናቸው።

አክለውም 25 ከሳሾች ድርጊቱ በተፈፀመባቸው ወቅት ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች ነበር። ዲዲ ሕፃናት ላይ ወሲባዊ ጥቃት በመፈጸም ሲከሰስ ይህ የመጀመሪያው ነው።

@waliyaentmt
@waliyaentmt
@waliyaentmt
🎂መልካም ልደት ለ መሳይ ተፈራ🎂

ባለፈው አመት ውስጥ ከተለቀቁት ድንቅ አልበሞች ውስጥ አንዱ የሆነውን "የልቤን" የተሰኘውን ያበረከተልን ድምፃዊ መሳይ ተፈራ ዛሬ የተወለደበት ቀን ነው።

መልካም ልደት ከዋልያ ኢንተርቴይመንት🎂🎂

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #Messay_tefera #yelben
የሮያሊቲ ክፍያ የሚጀመርበት ፕሮጀክት ይፋ ሆነ።

የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረቶች የሚጠናከሩበትና ሥራ የሚጀምሩበት ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል።

ፕሮጀክቱ በሰላም ኢትዮጵያ እና በሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በዩኔስኮ የገንዘብ ድጋፍ የተቀረፀ ሲሆን፤ የሚተገበረው በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን እና በኢትዮጵያ የሙዚቃ ዘርፎች ማህበራት ህብረት ትብብር ነው።

ፕሮጀክቱ የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች በባለሙያዎችና በሕግ አስከባሪዎች እንዲሁም በመንግሥት አካላትና በሞያ ማህበራት ዘንድ ስላላቸው ተጠቃሚነት ግንዛቤ የሚፈጥር ነው።

መብቶቹን የማክበር ባህልንም የሚያሳድግ እንደሆነ ዛሬ በተካሄደው የፕሮጀክቱ የማስተዋወቂያ መድረክ ተገልጿል።

ፕሮጀክቱ የሕግ ማዕቀፎች ዝግጅትና የኮፒ ራይት ምዝገባን፤ እንዲሁም ባለሙያዎች የፈጠራ ስራቸውን በተሻለ ሁኔታ እንዲጠብቁ የሚያስችሉ የተለያዩ ስልጠናዎችን መስጠትን ያካትታል።

ለሚቀጥሉት 18 ወራት የሚተገበረው ፕሮጀክቱ በዘርፉ እና በዘርፉ ተዋንያን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣል ተብሏል።

የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች ማጠናከር ፕሮጀክቱ በተለይ የስነ ስዕል፣ ቅርፃቅርፅ፣ ፊልም፣ ቲያትር፣ ሙዚቃና ውዝዋዜ እና መሰል የኪነጥበብ ዘርፎችን በከፍተኛ ሁኔታ ይደግፋል ተብሎ ይጠበቃል።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #royality
ተወዳጁ የሙዚቃ አቀናባሪ ኤልያስ መልካ ካረፈ ድፍን 5 አመት ሞላው።

በአብዛኞቹ የሙዚቃ አፍቃሪዎች ዘንድ የምንጊዜም ምርጥ አቀናባሪ ፣ ገጣሚ እንዲሁም ዜማ ደራሲ ሲሉ የሚያደንቁት ኤልያስ መልካ ካረፈ ዛሬ 5 አመት መሙላቱን አስመልክቶ የኤልያስ መልካ አድናቂዎቹ በጴጥሮስ ጳውሎስ ተገኝተው ሙት አመቱን እያስታወሱ ይገኛሉ።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #Eliasmelka
“ የልጆቼን ትምህርት ቤት መክፈል አቅቶኛል” የሙዚቃ ቪዲዮ ዳይሬክተር ስንታየሁ ሲሳይ

የሙዚቃ ዳይሬክተር ስንታየሁ ቁጥራቸው የበዙ ዘመን ተሻጋሪ የሙዚቃ ክሊፖችን ሰርቷል።
📌 የሄለን በርሄ - ልቤ እና እስኪ ልየው፣
📌 የዳን አድማሱ - ከፍቶሽ እንዳላይ ፣
📌 ደሜ ሉላ ሉላ እና ዱምባ ዱምባ
📌 ሙዳ ሼዳ እና ሳሮን ተፈሪ - ሚሶ ነጋያ ፣
📌 የጥበቡ ወርቅዬ - ሊጋባ ፣
📌 የመስፍን በቀል - ደመላሽ ፣
📌 ፍቅርአዲስ ነቃጥበብ ፣
📌 ኃይልዬ ታደሰ - ድሬ ድሬ፣
📌 የላፎንቴኖችን ባቡሬ ፣
📌 ነፃነት መለሰ - ደጉ ባላገሩ እና የታለ ልጁ የታለ፣
📌 ንጉሡ ታምራት - Ijaan Nalaaltee ,
📌 ሸዊት መዝገቦ - ፀማዕኻኒ
📌 ኤዴን ገብረ ሥላሴ - ሰው ዋኖ
📌 ገረመው አሰፋ - አለ ወይ
📌 ትንሳኤ ጎበና - ሰማይ
📌 ወንድሙ ጅራ - ከራስ ጋር
📌 ዘለቀ ገሠሠ - ሀገሬ እና ሌሎች በርካታ ክሊፖችን ወዘተ🙏 ሰርቷል

“..ለገንዘብ ሰርቼ አላውቅም ፤ ዘመን የሚሻገር ስራ ነው መስራት የምወደው ፣ ያላመንኩበትን ሥራ መስራት አልወድም” የሚለው ስንታየሁ ዛሬ ላይ ዋጋ እንዲከፍል እንዳደረገው ገልጿል ። ልጆቹን ለማሳደግ መኪናውን እስከመሸጥ መድረሱን ተናግሯል ።

ስንታየሁ በአሁን ሰዓት የልጆቹን ትምህርት ቤት መክፈል አቅቶት ልጆቹ ትምህርታቸውን ሊያቆሙ እንደሆነ ጭምር በEBS ቅዳሜ ከሰዓት ፕሮግራም ላይ ቀርቦ የእንባ ሳግ እየተናነቀው ተናግሯል።

አንጋፋውን የጥበብ ባለሞያ፤
ስንታየሁ ሲሳይ ወልደ ፃዲቅን ለማገዝ
1000351511285 - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
5141003450005 - ዳሽን ባንክ
73749093 - አቢሲኒያ ባንክ

https://gofund.me/5cd8a047

@waliyaentmt
@waliyaentmt
@waliyaentmt
ዜና ዕረፍት

የድምፃዊ ሚካኤል በላይነህ አባት አቶ በላይነህ ሐይሉ ከዚህ አለም ድካም አረፉ፡ በመሆኑም የቀብሩ ስነሥርአት ነገ ረቡዕ በ9.00 ሠዓት በየካ ሚካኤል ስለሚፈፀም የአርቲስቱ አድናቂዎችና የሥራ ባልደረቦች በሠዓቱ እንድትገኙ ይሁን። ነፍስ ይማር

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #micheal_balayneh
ድምፃዊ ሙሉዓለም ታከለ በዘንድሮ ዓመት የበኩር አልበሙን ለሙዚቃ አፍቃሪያን እንደሚያበቃ ገለፀ

በተለያዩ ነጠላ ዜማዎች ከሙዚቃ አፍቃሪያን ጋር የተዋወቀው ወጣቱ ድምፃዊ ሙሉዓለም ታከለ ‹‹ባለክራሩ›› በተሰኘው ፊልም ላይ በክራር ብቻ ያቀነቀናቸውን የሙዚቃ ስራዎች ስብስብ በአዲስ መልክ መስራቱን አሳውቋል፡፡

በክራር የሙዚቃ መሳሪያ ብቻ ታጅቦ ያቀነቀናቸው የቀደሙ ስራዎችን ጨምሮ ለፊልሙ የተዘጋጀ አንድ ሙዚቃን ጨምሮ በድምሩ አምስት ስራዎች እንደሆኑ ታውቋል፤ ድምፃዊው ከእዚህ ቀደም ‹ህዳር› በተሰኘው ፊልም ላይ ባቀነቀነው የማጀቢያ ሙዚቃ አማካይነት በጉማ አዋርድ ላይ ተሸልሞ እንደነበር ይታወሳል፡፡

ድምፃዊው ስለ አዲስ አልበሙ ለተነሳለት ጥያቄ በሰጠው ምላሽ ቢቻል በእዚህ ዓመት አጋማሽ፤ ካልሆነ በ2017ዓ.ም መጨረሻ ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ የማጠናቀቅ ሀሳብ እንዳለው አስታውሷል፡፡

የአልበም ስራው ከተጀመረ ሁለት ዓመታት ሊያስቆጥር ተቃርቧል ያለው ድምጻዊው በስራው ላይ ተሳትፎ ስላደረጉ ባለሙያዎች ባይገልፅም ብዙ ፈተናዎችን አልፎ ቢሆን ለሙዚቃ ወዳጆች የማድረስ ሃሳብ እንዳለው ገልጿል፡፡

Follow us
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #mulualem_getachew
የሳምንቱ ምርጥ ሙዚቃዎች በዩቲዩብ በብዛት ተመልካች ያገኙ 10 የሳምንቱ ሙዚቃዎች

የሶና ታከለ "ወረ ቦሌ" ነጠላ ዜማ በዚህ ሳምንት ከፍተኛ ደማጭነት በማግኘት የደረጃ ሰንጠረዡን አለቀቀም። ከአንድ ወር በላይ በርካታ ተመልካች በማግኘት የሚደርስበት ሙዚቃ አልተገኘም። በዚህ ሳምንት ብቻ 900ሺ+ ተመልካች አግኝቷል።

1ኛ🟡 ሶና ታከለ (ወረ ቦሌ) 🎶 906,944 እይታ
2ኛ🟡 ኤደን ገ/ሥላሴ (ይኹን) 🎶 404,553 እይታ
3ኛ🟢 ሳሌሚያ (አለም ብሬ) 🎶 380,287 እይታ
4ኛ🟡 አብዱ ኪያር (ቡቡዬ) 🎶 300,293 እይታ
5ኛ🔴 አብዱ ኪያር (ገለመሌ) 🎶 294,316 እይታ
6ኛ🟢 አንዱዓለም ጎሳ (ቢሊሌ) 🎶 270,154 እይታ
7ኛ🟡 ሰላማዊት ዮሐንስ (ሰንቢደ) 🎶 224,447 እይታ
8ኛ🟢 ማህሌት ወንድሙ (እሺ አትለኝም ወይ) 🎶 208,652 እይታ
9ኛ🟢 ቬሮኒካ አዳነ (እናነይ) 🎶 203,825 እይታ
10ኛ🔴 አንዱዓለም ጎሳ (ፎቴ) 🎶 192,383 እይታ

🟢 ደረጃ ያሻሻሉ
🔴 ደረጃ የቀነሱ
🟡 ባሉበት ደረጃ የቆዩ

🎶 በሳምንቱ ውስጥ በኢትዮጵያዊያን በዩቲዩብ በብዛት የታዩ ሙዚቃዎችን በትክክለኛ ዳታ ላይ ተመርኩዞ የቀረበ ምርጥ አስር ሙዚቃ ሰንጠረዥ ነው።

ጥቅምት 03/2017 ዓ.ም

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music
የኤልያስ መልካ አድናቂዎች ዛሬ በሙዳይ የበጎ አድራጎት ድርጅት የኤልያስ 5ተኛ ሙት አመቱን በማስመልከት አከበሩ።

በብዙዎች ዘንድ የሙዚቃ ፈጣሪ ተብሎ አድናቆትን የተቸረው ኤልያስ መልካ 5ተኛ ሙት አመቱን መሙላቱን አስመልክቶ ዛሬ የኤልያስ መልካ አድናቂዎች በሙዳይ የበጎ አድራጎት ድርጅት አክብረዋል።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #elias_melka
❣️ የሶል ንግሥት አስቴር አወቀ
የ2024 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ በሙዚቃ ዘርፍ ተሸላሚ ሆናለች 🇺🇸

#Ethiopia | የኢትዮጵያን ሙዚቃ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ አድማጮች ጋር እንዲደርስ በማስቻል ፈር-ቀዳጅ በመሆንሽ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ልባዊ ደስታውን በመግለፅ እንኳን ደስ አለሽ ይላል ።

በአፍሪካ የሙዚቃ ኢንደስትሪ ለፈጠርሽው ከፍተኛ ተፅእኖና በዓለም አቀፍ ደረጃ ወጣቱን ትውለድ በማነቃቃት ያደረግሽው አርዓያነት ይህንን እውቅና እንድታገኚ አድርጓል።

እ. ኤ.አ ጥቅምት 13 ቀን 2024 በሚደረገው የ2024 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ይህ እውቅናና ሽልማት ተበርክቶልሻል።

የ2024 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ስነ ስርአት ሜሪላንድ በሚገኘውና ኢትዮጵያዊያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩት ሜትሮ ፖይንትስ ሆቴል ዛሬ፣ እሁድ ኦክቶበር 13/2024 ምሽት በደማቅ ዝግጅት እተካሄደ ነው።

በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የተመሰረተውና ለትርፍ ያልተቋቋመው ኖቫ ኮኔክሽን ያዘጋጀው የ2024 አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ የዘንድሮ የክብር የሽልማት ሥነ ስርዓት እየተከናወነ ነው።

ይህ አመታዊ የእውቅና ሽልማት ስነ ስርአት በአሜሪካና በአፍሪካ በሙያቸው ታላቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን ለማክበር የተዘጋጀ ነው።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music #aster_aweke
ከአራት ዓመታት በላይ ጊዜን የወሰደው የወጣቱ ድምፃዊ እዮብ በላይ አልበም በዚህ አመት ለአድማጭ ይደርሳል ተባለ::

ድምፃዊ እዮብ በላይ ከአራት ዓመት በላይ ስለወሰደበት አልበሙ አንዳንድ መረጃዎች የተናገረ ሲሆን ከአንድ ዓመት በፊት ሰርቶ ለሙዚቃ አፍቃሪያን ባደረሰው እና ተወዳጅነትን ባተረፈው ‹ማለዳ› በተሰኘው ነጠላ ዜማው የሚታወቀው ወጣቱ ድምፃዊ እዮብ በላይ በአዲስ ስራም መጥቷል፡፡

ድምፃዊው ዓርብ ጥቅምት 1/2017 ‹አጀቤ› የተሰኘውን ሁለተኛ ስራውን ለሙዚቃ አፍቃሪያን ያደረሰ ሲሆን ምህረትዓብ ደስታ በግጥምና ዜማ ተሳትፎ አድርጎበታል፡፡

ከእዚህ በተጨማሪ ሚካኤል ሀይሉ(ሚኪ ጃኖ) በቅንብር እና ሚክሲንግ እንዲሁም ሰለሞን ሃ/ማርያም በማስተሪንግ ተሳትፎ እንዳደረጉበት ድምፃዊው ከመሰንበቻ ጋር ባደረገው ቆይታ አንስቷል፡፡

ከአራት ዓመት በላይ የሆነውን አልበሙን ወደ ሙዚቃ ወዳጆች ሊያደርስ መሆኑንም ድምፃዊው ተናግሯል። የ ይህን የበኩር የሆነ አልበሙን እስከ ዘንድሮ ዓመት መጨረሻ ሰርቶ ላይ ለማጠናቀቅ አቅዶ በሂደት ላይ መሆኑን አሳውቋል፡፡

ከአልበሙ አስቀድሞ ተጨማሪ አንድ ነጠላ ዜማ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል ያለው ድምፃዊ እዮብ በላይ ስራው ለአድማጭ ብቁ ሆኖ ሲገኝ ለመልቀቅ መታቀዱን በተጨማሪነት ገልጿል፡፡

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music