Waliya Entertainment
288 subscribers
1.57K photos
16 videos
763 links
ሙዚቃ እና ሙዚቃ ብቻ!!!

Follow us on social medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
Download Telegram
በአምላክ ቢያድግልኝ የ4ኛው የፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድርን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ድምጻዊ በአምላክ ቢያድግልኝ የ4ኛው የፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ የ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር አሸናፊ ሆኗል፡፡

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው 4ኛው የአሸናፊዎች አሸናፊ የፋና ላምሮት የድምጻውያን ውድድር ዛሬ ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡

በፍጻሜ ውድድሩም በአምላክ ቢያድግልኝ፣ ትዕግስት አስማረ፣ ሄኖክ ብርሃኑ እና ሃብታሙ ይሄነው የተዘጋጁበትን ሥራ በማቅረብ ብርቱ ፉክክር አድርገዋል፡፡

በዚህም በአምላክ ቢያድግልኝ ውድድሩን በአንደኝነት በማጠናቀቅ የ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር አሸናፊ መሆን ችሏል፡፡

እንዲሁም ፣ ሃብታሙ ይሄነው 2ኛ፣ ሄኖክ ብርሃኑ 3ኛ እና ትዕግስት አስማረ ደግሞ 4ኛ ሆነው ውድድሩን አጠናቅቀዋል፡፡

በዚህ መሰረትም 2ኛ ለወጣው ሃብታሙ ይሄነው 1ሚሊየን ብር ፣ 3ኛ ሆኖ ላጠናቀቀው ሄኖክ ብርሃኑ 500 ሺህ ብር እና 4ኛ ለወጣችው ትዕግስት አስማረ 300 ሺህ ብር ተሸልመዋል፡፡

በአጠቃላይ ለ4ኛው የፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ የፍጻሜ ውድድር የ3 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር ሽልማት ተበርክቷል፡፡

በሌላ በኩል ለግጥም እና ዜማ ደራሲ ለሆኑት ጸጋዬ ደቦጭ ደግሞ በዘርፉ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የ200 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቷል፡፡

በመላኩ ገድፍ
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music
👍1
"የሙዚቃ ስራዎቼን ለማበላለጥ አቅም አጣለሁ"!

ዝነኛው የሙዚቃ ሰው ሙላቱ አስታጥቄ

የኢትዮጵያን ሙዚቃ ተራቆበታል፥ በማሲንቆና ዋሽንት የተከሸኑ ባህላዊ ሙዚቃዎችን ማዳመጥ ያዘወትራል፥ለጥላሁን ገሰሰ እና ሙሉቀን መለሰ አድናቆቱን ይቸራል፤ አራቱንም የሀገር ቤት ቅኝቶች በፍቅር ያደምጣል።
በኮንሶ፣ በወላይታ፣ በከፋ፣ በደራሼ፣ ጋሞ፣ አኙዋክ፣ በሱርማና በሌሎችም ብሔረሰቦች ሙዚቃ ላይ የሱሩትን ሙያተኞች ደግሞ ደጋግሞ ያወድሳል።

በጥበብ ውስጥ ከአራት አሥርት ዓመታት በላይ የዘለቀው አርቲስት ሙላቱ አስታጥቄ የኢትዮጵያን ጃዝ ሙዚቃ ለማስተዋወቅ ዓለምን ዞሯል። ከታዋቂ ሰዎች ጋርም ኮንሰርቶችን ሰርቷል

በመጀመሪያው አልበም “አይፈራም ጋሜ አይፈራም”፣ “አልማዝ” እና “አክሱም” የተሰኙትን ኢትዮጵያዊ ሙዚቃዎችን ሲያካትት በሁለተኛው “ቆንጂት” እና “ከረዩ” የተሰኙትን አክሎበታል።

በዚ አጋጣሚ ነበር ኢትኖግራፈሩ ሙዚቀኛ ሙላቱ አስታጥቄ “ኢትዮ ጃዝ” የተሰኘውን የሙያ ልጁን ለመጠንሰስ የበቃው። አክብሮቱና ትህትናው ወደር አይገኝለትም። ተሞክሮውን ለማካፈል ደስ እያለው ጊዜውን ይሰጣል ።

ነጥሎ ሶስት ተመራጭ ሙዚቀኞችን እንዲጠራ ጫን ብለን ጠየቅነው። የተወዳጁ ሙዚቀኛ ጥላሁንን ገሰሰ 'ያላንቺ አልኖርም' የተባለውን ሙዚቃ ጠራ። ከሙሉቀን ጋር የሰራቸውን ዘመን ተሻጋሪ ስራዎችና በጥቅሉ ሁሉንም የሙዚቃ ቅንብሮቼን እወዳቸዋለው ሲል አከለ። የሰይፉ ዩሐንስን የከርሞ ሰውን ጨምሮ የሰራቸው በርካታ ስራዎቹ አይጠገቤነታቸው አያጠያይቅም።

Follow us on
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt
የሐረሪ ባህላዊ የሙዚቃ ኖታ : የጥናት መፅሐፍ

#Ethiopia | የሐረሪ ባህላዊ የሙዚቃ ኖታ ላይ ትኩረት ያደረገ የጥናት መፅሐፍ ተመርቋል፡፡

የጥናት መፅሐፉን ያዘጋጁት የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ እንዲሁም የሐረሪ ክልል ባህል ቅርስ እና ቱሪዝም ቢሮ ናቸው፡፡

የሐረሪ ብሔረሰብ ተዝቆ የማያልቅ ቱባ የስልተ ምት እንዲሁም የማህበራዊ ክንዋኔ ባለቤት መሆኑን የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ሰርፀ ፍሬስብሃት ተናግረዋል፡፡

መፅሐፉ ይህንን ሐብት አጥንቶ መሰነድን ዓላማ ማድረጉንም ምክትል ሃላፊው ገልጸዋል፡፡

የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ አፈ ጉባኤ አቶ ሙህየዲን አህመድ በበኩላቸው ሐረር የበርካታ የጥበብ ባለሞያዎች መፍለቂያ መሆኗን ጠቁመው የጥናት መፅሐፉ የክልሉን ባህላዊ ሙዚቃ በማስተዋወቅ ረገድ የላቀ ሚና እንደሚኖረው አመላክተዋል፡፡

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music
ታሜ እንደዋዛ 6 ዓመት ሞላው

የዛሬ 6 ዓመት በዚች ቀንና በዚች ስአት ነበር ድምፃዊ ታምራት ደስታ ከዚህ አለም በሞት የተለየን:: ድምፃዊ ታምራት ደስታ ቀኑ ረቡዕ እለት ሚያዚያ 10 ቀን 2010 ዓ.ም ነበር ። ታሜ በተወለደ በሰላሳ ዘጠኝ (39) አመቱ በህክምና ስህተት ከዚህ አለም በሞት የተለየው:: ታሜ ሃያ አንድ (21) አመታት በቆየበት ስኬታማ የሙዚቃ ታሪኩ አራት (4) ያህል አልበሞችን እና ከዘጠኝ (9) ያላነሱ ነጠላ ዜማዎችን አበርክቷል::

የምንጊዜም ምርጡ ድምጻዊ ታምራት ደስታ ከድምጻዊነቱ ባሻገር ቤተሰቡን (ልጆቹን) አክባሪ ማህበራዊ ህይወትን የሚያውቅ: ቁም ነገረኛ እና አስተዋይ ነበር::ታምራት ለብዙዎቻችን አረፈ እንጂ አልሞተም ዘመን በማይሽራቸው ተወዳጅ ስራዎቹ ሁሌም ሲታወስ ይኖራል::ነፍስህን ከደጋጎቹ ያድርግልን ታሜ።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music
👍1
መልካም ልደት ዲጄ ቤቢ🎉

በተለያዩ የመድረክ ፣ የሬዲዮ እና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች የምናውቀው እንዲሁም የአዲስ ሙዚክ የሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጅ የሆነው ዲጄ ቤቢ ዛሬ ልደቱ ነው።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music
ዝክረ ጥላሁን ገሠሠ
፨ ፨ ፨ ፨ ፨
በዛሬው ዕለት ታሪክ ሲወሳ ሚያዚያ 11 : 2001 ክቡር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየበት ቀን ነበር፡፡

በወሊሶ ከተማ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓም የተወለደው ጥላሁን ገሠሠ በ1949 በክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ ተቀጥሮ መስራት ጀመረ ፡፡
ከ1950ዎቹ የመጀመሪያ ዓመታት እስከ 1960ዎቹ አጋማሽ ድረስ በክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ አጃቢነት አያሌ ድንቅ ዘፈኖችን በመጫወት እውቅናን አትርፏል ።

ያልዘፈነበት ጉዳይ የለም የሚባልለት ጥላሁን ገሠሠ ድንበር የማይገድበው ፍቅር፣ የሀገር ክብር ገላጭ እንዲሁም መካሪ ስራዎቹ ለዚህ ተጠቃሽ እንደሆኑ ይነገራል ።

ጥላሁን በሚያዘያ ወር 1985 አንገቱ ላይ በስለት የመወጋት አደጋ ደርሶበት እንደነበር ነገር ግን ይህ በድምጻዊነት ከመቀጠል አላገደውም ።

በኢትዮጵያ የዘመናዊ የሙዚቃ ታሪክ ደማቅ ታሪክን ያሳለፈ፣ ትውልድ ተሻጋሪ፣ ተደማጭ ድንቅ የሙዚቃ ስራዎችን ያበረከተው ድምጻዊ የክቡር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ በተወለደ በ68 አመቱ በዛሬው ዕለት ማለፋን ታሪክ ይዘክራል፡፡

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music