Waliya Entertainment
288 subscribers
1.57K photos
16 videos
763 links
ሙዚቃ እና ሙዚቃ ብቻ!!!

Follow us on social medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt
Download Telegram
ድምፃዊ ልኡል ሃይሉ ከ3 ዓመታት በፊት ያሰራጨው አልበም በአዲስ ባለመብት ዳግም መለቀቁን አስታወቀ።

ዕውቁ የሙዚቃ ባለሙያ ኤልያስ መልካ በህይወት ሳለ ለሙዚቃ አፍቃሪያን ከደረሱ የመጨረሻ አልበሞች ውስጥ አንዱ የሆነው "እሳቱ ሰዓት" አልበም ዳግም እንዲሰራጭ መደረጉን ተናግሯል።

ከጉዳዩ ጋር በተገናኘ ከመሰንበቻ ጋር ቆይታ ያደረገው ወጣቱ ድምፃዊ ልዑል ሀይሉ የአልበም ስራው ከእዚህ ቀደም በአውታር መተግበሪያ አማካይነት ቢሰራጭም በሚፈለገው ልክ ተደራሽ ሆኗል ብሎ እንደማያስብ ተናግሯል።

ከእዚህ በተጨማሪ ድምፃዊው ከእዚህ አልበም ስርጭት ጋር በተገናኘ ምንም አይነት ክፍያ አለማግኘቱ ቅሬታ እንደፈጠረበት በቆይታው አንስቷል።

አልበሙ ባለቤት አልባ መሆኑን ተከትሎ ከባለ መብቱ እውቅናና ፍቃድ ውጪ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ በተለያዩ መንገዶች ሲሰራጭ ነበር ሲል ድምፃዊው ተናግሯል።

ይህንን አይነቱን ክፍተት ለማስተካከል እና ተገቢውን ጥቅምና የባለመብትነት ጉዳይ ለተገቢው አካል መስጠት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የአልበም ስራው ሊቀቅ ችሏል።

ከመጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በ"ናሆም ሬከርድስ" ባለመብትነት አልበሙ እንደተሰራጨ ያስታወቀው ድምፃው አዲሱ ስምምነት የኮንሰርት ስራዎችን ጨምሮ አልበሙ ተደራሽ የሚሆኑባቸው መንገዶች ይኖራሉ ሲል አስታውቋል።

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music
🌟 70K SUBSCRIBERS ON YOUTUBE! 🌟

Thank you for being part of this incredible journey! Your support, enthusiasm, and engagement have brought us to this amazing milestone.

Let's keep the celebration going and look forward to even more exciting content ahead! 🥳

Please Subscribe us on👇
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
👍1👏1
ለግጥምና ዜማዎቼ የሂሩት በቀለ ድምፅ የልቤን ያደርስልኛል።

ክቡር ዶ/ር አርቲስት ተስፋዬ አበበ(ፋዘር)

ከ40 በላይ ትያትሮች ተጫውተዋል። ለተዋቂ ሙዚቀኞችም የበዙ ግጥምና ዜማዎችን አበርክተዋል።

ከአራቱ ቅኝቶች የባቲ ቅኝትን ይመርጣሉ፤ የጥላሁንን ገሰሰ እዩዋት ስትናፍቀኝ እና ያም ሲያማ ሙዚቃዎችን በተለየ መንገድ ይመርጡዋቸዋል።

የአስናቀች ወርቁ እንደ እየሩሳሌም የተሰኘው ሌላው የልብ ስራቸው ነው።የአለማየሁ እሸቴ ቆየት ያሉ ሙዚቃዎችንም ደጋግመው ያዳምጡዋቸዋል።

ዘመን ከማይሽረው የራሳቸው ስራዎች አብልጠው የሚወዱትን ጠየቅናቸው ከጥቂት ዝምታ በኋላ ምላሻቸውን አስከተሉ«የሂሩት በቀለ ኢትዪጵያ ሀገሬ እንደ ህዝብ መዝሙር እየተደመጠ ወቅት የሚሻገር ስራ ነውና አስቀድመዋለሁ» አሉን።

ሌላው የግጥምና ዜማ ስራቸው መማር ያስከብራልን ቀጥለው አነሱ።
ለመሰነባበት ጥቂት ሲቀረን ከአሁን ሙዚቃዎች መርጠው የሚሰሙትን አጫወቱን ፣ የፍቅር አዲስ ነቃጥበብን መረጡ ። የትኛው ስራዋን?እሷ የነካችሁ ሁሉ ይስማማኛል ነበር ምላሻቸው !

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music
የለዛ አዋርድ የአመቱ ምርጥ አልበም የመጨረሻ እጩዎች
1, ሔዋን ገብረወልድ - ሔዋን
2, አብነት አጎናፍር - አለቀ
3, ሮፍናን - ስድስት
4, ዲበኩሉ ታፈሰ - የቱ ጋር ነህ?
5, ግርማ ተፈራ - ግን የት ሃገር?

ድምፆትን ለመስጠት 👉http://vote.leza.show

እባክዎ መልዕክቱን ያጋሩ :
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music
የለዛ አዋርድ የአመቱ ምርጥ ነጠላ ዜማ የመጨረሻ እጩዎች
1, ቴዲ አፍሮ - ናዕት
2, ዩሃና - ገላጋይ
3, ማስተዋል እያዩ - ጀግና
4, አስቻለው ፈጠነ - እናትዋ ጎንደር
5, ቬሮኒካ አዳነ - አበባዬ

ድምፆትን ለመስጠት 👉http://vote.leza.show

እባክዎ መልዕክቱን ያጋሩ :
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music
👍1
ነገ በመላ ሀገሪቱ :-

* ይወጣል
* ይለቀቃል

* ለተወዳጁ ድምፃዊ
* ለኢትዮጵያ ልጅ ቴዎድሮስ ካሳሁን ቴዲ አፍሮ መፅሀፍ ተፃፈለት

"ቴዎድሮስ እስኪነግስ" የተሰኘው በብላቴናው የሕይወት ውጣውረድ ላይ ያተኮረው መፅሐፍ ነገ ይወጣል

የሰው ልጅ በኖረበት በየትኛውም የዓለም ስፍራ ባለጸጋ ሆነ ድሃ፣ አለቃ ሆነ ምንዝር በምድር በቆየባቸው ዘመናት የፈጸመው መልካምም ሆነ መጥፎ ተግባር በትውልዶች የህይወት ገጽ ውስጥ በአንዳች መልኩ መስፈሩ አይቀሬ ነው፡፡ በዚህ የህይወት ፍሰት ውስጥ ያለፈ ሁሉም ሰው ደግሞ የኋላ ዳና፣ የዛሬ አሻራ፣ የነገም ራዕይ አለው፡፡ እነሆ የክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ገርማሞ ( Teddy Afro ) የትላንት ፣ ዛሬና ነገ መልክ፡፡

መጽሐፉን ከነገ ጀምሮ በነዚህ መደብሮች ማግኘት ይችላሉ;-

* ስታዲየም ነጃ መጽሐፍ መደብር 0910990259
* ለገሀር በጋሻው መጽሐፍ መደብር 0911656729
* ለገሀር ማድያ ያሬድ መጽሐፍ መደብር 0913094097
* ሜክሲኮ ኤልያስ አምደ መጽሐፍ መደብር
* መሳለሚያ ሆናልያት ህንፃ ቢሮ ቁጥር 156 ተኬ ማን ፕሮሞሽን 0911518012 ወይም 0921935862
* አራት ኪሎ 0901197837
* ካዛንቺስ መላ ህንጻ ጦቢያ መጽሐፍ መደብር 0913108312
* ፒያሳ አፒር ታረቀኝ መጽሐፍ መደብር 0983294565

Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://www.t.me/waliyaentmt

#Waliya_Entertainemnt #Music
👍1
Selam Ethiopia is inviting industry professionals, investors and policymakers to attend its inaugural Culture and Creative Industries (CCI) Summit: Music & Film Edition at Addis Ababa University on 8 and 9 April.

The event is aimed at exploring investment prospects and propelling the advancement of Ethiopia’s cultural and creative industries (CCIs) With a focus on music and film, this year’s edition of the summit will feature comprehensive sessions addressing market analysis, essential facets of the music and film business, insights into Ethiopia’s streaming landscape, copyright discussions and pitch sessions showcasing business solutions from some of Ethiopia’s most prominent creative professionals.

Reflecting on the significance of the event, Selam CEO said: “The Culture and Creative Industries Summit: Music & Film Edition 2024 presents an unprecedented opportunity to celebrate Ethiopia’s cultural richness and drive economic growth through our creative endeavours. 

Register here
https://shorturl.at/qtRTU
በእንግሊዝ ያሉ ቅርሶችን ለማስመለስ የተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች እንቅስቃሴ

እንደ ሙላቱ አስታጥቄ እና አቤል ተስፋዬ (ዘዊኬንድ) ያሉ ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያን በአለም መብዛታቸው ቅርሶችን ለማስመለስ እየረዳ ይገኛል ተባለ፡፡

ኢትዮጵያ በጣሊያን ቬነስ ከተማ በተካሄደው በዓለም አቀፉ የቢናሌ የባህል ኤግዚቢሽን ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳትፋለች፡፡ መድረኩ አለም አቀፍ የጥበብ ሰዎች ሥራቸውን ያቀረቡበት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ታዋቂው ገጣሚና ደራሲ ለምን ሲሳይ እና ኢትዮጵያዊው ሰዓሊ ተስፋዬ ኡርጌሳ ተሳትፈውበታል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያዊው ሰዓሊ ተስፋዬ ኡርጌሳ ስራቸውን አቅርበዋል፡፡

በወቅቱ ገጣሚ ለምን ሲሳይ እንደገለፀው የእንግሊዝ ሙዚየም ከእይታ ደብቆ በምስጢር አስቀምጧቸዋል ያላቸውን ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ጠይቋል፡፡

በዚህም ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያን በአለም ደረጃ እየበዙ መምጣታቸው ቅርሶችን በማስመልስ ሂደት ውስጥ ሰፊ ሚና እንደሚኖራቸው ገልጿል፡፡

ለአብነትም እንደ ሙላቱ አስታጥቄ፣ አቤል ተስፋዬ (ዘዊኬንድ)፣ መአዛ መንግሰቴ፣ ሩት ነጋ እና ሊያ ከበደን ጨምሮ የሌሎች በርካታ ኢትዮጵያዊያን ተፅዕኖ ፈጣሪነት የኢትዮጵያን የቅርስ ማስመለስ ጥያቄዎች ችላ እንዳይባሉ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ጠቅሷል፡፡

ቅርሶቹ በመቅደላ ጦርነት ወቅት የተወሰዱ ቅርሶች ሲሆን በተጨማሪም 11 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታቦታት እንደሚገኙበትም ዘጋርዲያን ዘግቧል፡፡

ገጣሚ ለምን አክሎም የእንግሊዝ ሙዚየም በ50 ሚሊየን ፓውንድ እድሳት ሊደረግለት እቅድ መያዙን ገልጾ ከዕቅዱ ውስጥም ቅርሶችን መመለስ ሊገኝበት እንደሚችል ተስፋውን ገልጿል፡፡

https://t.me/waliyaentmt
https://t.me/waliyaentmt