የ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጽሑፎች በPDF እና በድምጽ
2.15K subscribers
51 photos
2 videos
26 files
54 links
እዚህ ቻናል ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት የሚያንጸባርቁ ጽሑፎች ይለቀቃሉ
Download Telegram
መናፍቃን

መናፍቅ የሚለው ቃል የግዕዝ ቃል ሲሆን ,,ናፈቀ,, ተጠራጠረ አጠራጠረ ከፍሎ አመነ ማለት ነው
መናፍቅ የሚለውን ቃል ኪዳነ ወልድ ክፍሌ እንድህ ይተረጉሙታል
በግሪክ ኤፌቲክ
በእንግሊዘኛ ሄሬቲክ
በግዕዝ ደግሞ ሐራ ጥቃ =
መናፍቃን በየዘመናቱ የተለያዪ ስያሜዎች ተሰቷቸዋል
#በዘመነ ነቢያተት=ነቢያተ ( 1ኛ ነገ 13:11)
#በዘመነ ክርስቶስ
ጠላት የጠላት ልጅ (ማቴ 13:39)
#በዘመነ ሐዋርያት
ቢጸ ሐሳዊያን (የውሸት ወንድሞች)
#በዘመነ ሊቃውንት
መናፍቃን ተብለዋል::

፠መንፍቅና እንደት ተጀመረ ?
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
መናፍቅና የተጀመረው በሁለት መንገድ ነው
1ኛ/በጥንቆላ
ጥንቆላ ፈጣሪን የሚአሳዝን እጅግ አጸያፊ ተግባር ሲሆን ምንፍቅና ለመጀመሪያ የመጣውም በዚሁ ሥራ ነው
በቤተክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያው መናፍቅ Simon ሲሞን ይባላል::
በሐዋሥ 8:9 ላይ ታሪኩን እናገኘዋለን
ይህ ሰው ሐዋርያት ተአምር ሲሰሩ ሲያይ አመንኩ ብሎ ተጠመቀ
ከዚያም የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ በገንዘብ ለመግዛት የሞከረ ሰው ነበረ::
በመጨረሻም በመተቱ ምልክት እያሳየ
በብሉይ ኪዳን እንደ አብ
በሐድስ ኪዳን እንደ ወልድ
በባአለ ሃምሳ እንደ መንፈስ ቅዱስ ሆኜ የተገለጥኩ እኔ ነኝ ይል ነበር
ከዚያም የእርሱ ተከታዮች በቤተ ክርስቲያን ላይ ብዙ ጉዳት አድረሰዋል
2ኛ/በፍልስፍና
ክርስቶስ በተገለጠበት ዘመን ግሪክ በፍልስፍና የታወቀችበት ዘመን ነበር
ግሪኮች እራሳቸውን እንደጥበበኛ አድርገውም ይመለከቱ ነበር
ቅዱስ ጳውሎስም
" የግሪክ ሰዎችም ጥበብን ይሻሉ"
(1ኛቆሮ 1:22)ያላቸው ለዚህ ነው
እነዚህ ሰወች እውቀታዊ ሃይማኖት
Gnostic Religion በመፍጠር
ከመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስካሁን ድረስ ቤተ ክርስቲያንን ተዋግተዋታል
እነዚህ ሰዎች ግንስቲክ ሲባሉ አስተምህሯቸውም ግኖስቲዝም Gnosticismይባላል::
ሲያስተምሩም
ክፉና ደግ ሁለት አማልክት አሉ
ክፉው አምላክ ክፉትን ፈጠረ
ደጉ አምላክ ደግ ደጉን ፈጠረ ይሉ ነበር
የክፉውም ሆነ የደጉ ትንንሽ አማልክት ልጆች አሏቸው
ከደጉ አምላክ ልጅ አንዱ ትንሹ አምላክ ክርስቶስ ነው ለማለት ኤኑስ Aeons ይሉት ነበር
ዛሬ ያሉ መናፍቃን
ወልድን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ማሳነስ ከእነዚህ የተማሩት ነው
ይህ ብቻ አልነበረም ክርስቶስ አልተሰቀለም አልሞተም ይሉም ነበር
ይህንን Substitutions theory የምትክ ጽንሰ ሃሳብ ከእነርሱ #በሒራ ሰርጁስ የተባለ ካቶሊካዊ መነኩሴ በሰባተኛው መክዘ ለተነሳው ለእስልምና መስራች ለነቢዩ #መሐመድ አስተማራቸው
እርሳቸውም #በቁራናቼው በሱራ አል ኒሳ 4:157 ""እኛ የአላህን መልክተኛ የመሬምን ልጅ አል መሲህ ኢሳን ገደልን በማለታቸው እረግመናቸዋል አልገደሉትም አልሰቀሉትም ነገር ግን ለእርሱ የተሰቀለው ሰው በኢሳ ተመሰለ ""በማለት የዓለምን ድኅነት ከንቱ የሚአደርግ ሃሳብ አስቀመጡ
በአጠቀላይ ስለ ኃጢአት ስለ ነፍስና ሥጋ ስለ ድኅነት
የግኒስቲኮች አስተምህሮ በጣም የተወሳሰበ ነው
ይህንና የመሳሰለውን አስተምህሯቸውን በእውነተኞቹ ሐዋርያት ስም መጽሐፍ በመጻፍ ኑፋቄያቸውን በማስገባት ብዙ ደክመዋል::
ለምሳሌ
የበርናባስ ወንጌል የጴጥሮስ ወንጌል የሚባሉት ጥቂቶቹ ናቸው
ቤተ ክርስቲያን እነዚህን የኑፋቄ መጽሐፍት ከደኖቹ መጽሐፍት ለመለየት
200 ዓመት ፈጅቶባታል::
ይህ አስተምህሮ በዘመኑ በነበሩት ሁለት የአንጾኪያና የእስክንድርያ የቴኦሎጅ ትምህርት ቤቶች በመግባቱ
ከዚህ አስተምህሮ አየተጎነጪ የመጡ ብዙ መናፍቃን ናቸው
ብዙዎቹን ለመጥቀስ ባልችልም የታወቁትን ለመግለጽ ያክል
1ኛ/#አርዮስ
አርዮስ በሶስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሊቢያ የተወለደ ቄስና በአንጾኪያ የተማረ ሰው ::
ይህ ሰው ከፍልስፍናው ኑፋቄ ቀድቶት በመጣው ትምህርት ወልድን ፍጡር ያለ ሰው ነው
ክርስቶስ በባህሪ metaphysical የእግዚአብሔር ልጅ አይደለም በጸጋ የጸጋ አምላክ ነው ይል ነበር::
በመጨረሻም እርሱንም አስተምህሮውንም 325 ዓ.ም 318ቱ ሊቃውንት በኒቅያ አውግዘውታል
የእርሱን አስተምህሮ እንደገና በማደስ እነ#ቻርልስ ራስል የጀሆቫን እምነት መሠረቱ::

2ኛ/ #ንስጥሮስ
ንስጥሮስ 428-431 ዓ.ም የነበረ የቁስጥንጥንያ ዛሬ ኤስታፑል ቱርክ ሊቀ ጳጳስ ነበር
ይኽ ሰው ክርስቶስን ሁለት አካል ነው
ሰዉአዊ አካልና አምላካዊ አካል አለው የሚኖረው በተዋህዶ ሳይሆን ተደራርቦ ነው ይል ነበር::
እመቤታችንም ወላአዲተ አምላክ Theotokos አትባልም ይል ነበር
በመጨረሻም 431 ዓ.ም በኤፌሶን ተወገዘ::
3ኛ/#ሄሊቪዲየስ
ይኽ ሰው 4ኛው መቶ ዓመት የነበረ ሮማዊ ሰው ነው
ይኽ ሰው
የድንግልና ህይወት ምንም ጥቅም የለውም ያለና
ለመጀመሪያ ጊዜ የመቤታችን ድንግልና የተቀወመ ከክርስቶስ ሌላ ሌላ ልጅ አላት ብሎ ያለ መናፍቅ ሲሆን በጊዜው የነበሩት አባ ሄሮኒመስ (ጄሮም)ለዚህ አድስ ኑፋቄ መልስ በመመለስ አፉን ዘግተውታል::
4ኛ/ #ማርቲን ሉተር
ይህ ሰው አሁን ያለውን ፕሮቴስታት ኑፋቄ መስራች ነው
ይኽ ሰው 1483 ዓ.ም አይስሌበን በተባለች ስፍራ በጀርመን የተወለደ ሲሆን ጣዖት አምላኪ የነበረ ሰው ነው
ይኽ ሰው ከሐዋርያት አስተምህሮ እየራቀች የሠጣችውን የካቶሊክን እምነት በመቃወምና የሮማ ካቶሊክ አገዛዝ ያንቀጠቀጠውን ህዝብ በማሰባሰብ በመጨረሻ 95 (Ninety five theses)የተቃውሞ ነጥቦችን በዊተንበርግ በይፋ ለጠፈ::ዕምነቱም ፕሮቴስታት ተባለ፠
ይቀጥላል

ከዲያቆን ገብረክርስቶስ ካሳ
https://t.me/ethiopianorthodoxbooks