አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
#አሁን አሁን ላይ ፖሊስ ግለሰቦች የተጠረጠሩበት ወንጀል ከባድም ይሁን ቀላል፤ እጅ ከፍንጅ የተያዙም ይሁን በክትትል ተጠርጣሪውን በእስር በማቆየት በ48 ሰዓታት ውስጥ ለፍርድ ቤት በማቅረብ ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ይፈቀድልን ማለቱን ልምድ አድርገውታል።
#ጊዜ ቀጠሮ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀጽ 67 እና በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 19 ንዑስ አንቀጽ 6 ጥብቅ ጥበቃ ለተደረገለት #ተጠርጣሪዎች_በተጠረጠሩበት_ወንጀል_ዋስትና_የማግኘት_መብት ልዩ ሁኔታ (Exception) ነው።
#ይህ ልዩ ሁኔታ መሠረት የሚያደርገው ተጠርጣሪው ከእስር ውጪ ቢሆን የፖሊስን የምርመራ ሂደት ሊያደናቅፍ ይችላል ወይስ አይችልም? የሚለውን ነጥብ በመመርኮዝ ነው።
👉በፍርድ ቤት ጊዜ ቀጠሮ ላይ ቀርበው ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ከተጠየቀብዎ እነዚህን ምላሾች ይስጡ!!!
#የተጠረጠሩበትን ወንጀል ያመኑ ከሆነ🤔የተከበረው ችሎት እኔ የተጠረጠርኩበትን ወንጀል መፈጸሜን እያመንኩኝ በዚህም መነሻነት ብቻ ክስ ተመስርቶብኝ ፍርድ ሊሰጥ እንደሚቻል እየታወቀ ጭማሪ ጊዜው አላግባብ ነው፤ በሕገ መንሥት የተጠበቀልኝን የተፋጠነ ፍትሕ የማግኘት መብቴን የሚጎዳ ነው። በመሆኑም ቀን መጨመር ሳያስፈልገው በዋስትና እንድወጣ ይደረግ፤ ካልሆነ ቀጥታ ክስ እንዲመሰረት ትዕዛዝ ይሰጥልኝ።
#ምስክሮችን ቃል ስላልተቀበልን ቀን ይጨመርልኝ ከተባለ🤔የተከበረው ችሎት ፖሊስ አስቀድሞ የግል ተበዳይንና የምስክሮችን ቃል ማሰባሰብ ሲገባው እኔን አስሮ ማጣራቱ ተገቢነት የለውም፤ እኔ በዋስትና ብወጣም ምስክሮች እነማን እንደሆኑ በማላውቅበት ምናልባትም ምስክሮቹ የፀጥታ አካላት በሆኑበት ምስክሮችን ሊያስፈራራና ሊያባብል ይችላል መባሉ አላግባብ ነውና በዋስትና እንድወጣ ይፈቀድልኝ።