• ተጎጂ/ቤተሰብ ለማግኘት ከተቻለ በጥያቄው ላይ ያላቸው አስተያየት፣
• የማረሚያ ቤት ፀባይና ስነምግባር፣
• የአመልካች የቤተሰብ፣ የጤንነት (ለመታረም አስቸጋሪ ያደረገ በቦርድ የተረጋገጠ)፣ እድሜ ሁኔታ፣
• የህዝብና መንግስት ጥቅም ልዩ ሁኔታ፣
• እድሜ ልክ ፍርደኛ ከሆነ 12 አመት እስር መጨረሱን፣ ሌሎች ፍርደኞች 1/3ኛ እስር መጨረሳቸውን፣ የግዴታ ስራ ካለበት ይህን መጨረሱን፣ ናቸው፡፡
ቦርዱ የሙስና፣ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ሽብር፣ በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ፣ ሀሰተኛ ገንዘብ መስራት ማዛወር፣ አደገኛ እፅ፣ ሴቶችና ህፃናት መድፈር ወይም መጥለፍ፣ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀም ወንጀል የፈፀሙ ፍርደኞችን ጉዳይ በጥንቃቄ በልዩ ሁኔታ ካልሆነ እደሌሎች ወንጀሎች አያይም፡፡
በዚህ መልክ ታይቶ የሚፈቀድ የይቅርታ ውሳኔ ውጤትን ስንመለከት ውሳኔው በግልፅ በከፊል መሆኑ ካልተመለከተ በቀር ይቅርታው የፍርድ ቅጣቶችን በሙሉ ያስቀራል፡፡ ሆኖም ይቅርታ ከወንጀል ፍርዱ የሚመነጩ የፍትሐብሔር ሀላፊነቶችን አያስቀርም፡፡ በተጨማሪም በፍትሐብሔር የጠፋውን እንደነበር ለመመለስ እና በተበዳይ ላይ ለደረሰ ጉዳት የሚከፈል ካሳና ኪሳራ አያስቀርም፡፡ ሆኖም በተለይ ካልተገለፀ በቀር ለመንግስት ሊከፈል የሚገባ ወይም ያልተከፈለ ኪሳራ ቀሪ ይሆናል፡፡ ይቅርታው ከመሰጠቱ ቀድሞ የተፈፀሙ ቅጣቶች ደግሞ የፀኑ ይሆናሉ፡፡ ይቅርታ በተሰጠበት ወንጀል በአጥፊው ላይ የተያዘው የወንጀል ሪከርድ በወንጀለኞች መዝገብ ላይ ተመዝግቦ ይኖራል፡፡
ይቅርታ የተሰጠው በሀሰተኛ ወይም በተጭበረበረ ማስረጃ ተመስርቶ ከሆነ ይቅርታው ዋጋ አይኖረውም፡፡
በቅድመ ሁኔታ ላይ ተመስርቶ የተሰጠ ይቅርታ ቅድመ ሁኔታው ከተጣሰ ዋጋ ያጣል፡፡ በዚህም መሰረት አጥፊው ቀሪ ቅጣቱን እንዲፈፅም ለማድረግ እንዲቻል ቦርዱ ይቅርታው እንዲሰረዝ ክብርት ፕሬዚዳንት ትእዛዝ እንዲሰጡ የውሳኔ ሀሳብ ያቀርባል፣ ይህ ተቀባይነት እንዳገኘ ትእዛዙ ለአጥፊው እንዲደርሰው ይደረግና ቅሬታ ካለው ትእዛዙ በደረሰው በአስራ አምስት ቀን ለቦርዱ ማቅረብ አለበት፡፡ ቅሬታው ተቀባይነት ካጣ የይቅርታ ምስክር ወረቀቱን እንዲመልስ ይደረጋል፣ በዚህም መሰረት የመያዣ ትእዛዝ እንዲሰጥ ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጥያቄ ቀርቦ ቀሪ ቅጣቱን እንዲፈፅም ይደረጋል፡፡
በአጠቃላይ የይቅርታ አላማ ከላይ እንደተመለከትነው አጥፊዎች ከጥፋታቸው ታርመውና ተፀፅተው ህግ አክባሪና መልካም ዜጋ ሆነው መኖር እዲችሉ ለማድረግ የሚሰጥ እድል ነው፡፡ የወንጀል ቅጣታቸው የመጨረሻ የሆነ፣ አንድ ሶስተኛ እስራታቸውን የጨረሱ፣ በማረሚያ ቤት በመልካም ባህሪ የቆዩ፣ ከጥፋታቸው የተፀፀቱና በቀጣይም ህግን አክብረው ለመኖር የሚችሉ ሰዎች የሚያገኙት ሁለተኛ እድል ሲሆን ይቅርታ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ ብሎም ከወንጀል የተጠበቀ ለማድረግ ይረዳል፡፡ ይቅርታ የሚሰጣቸው ሰዎችም ይህን ተገንዘበው ህብረተሰቡን በመካስ በህግ አክባሪነትና በመልካም ስነ ምግባር መመራት ይጠበቅባቸዋል፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
• የማረሚያ ቤት ፀባይና ስነምግባር፣
• የአመልካች የቤተሰብ፣ የጤንነት (ለመታረም አስቸጋሪ ያደረገ በቦርድ የተረጋገጠ)፣ እድሜ ሁኔታ፣
• የህዝብና መንግስት ጥቅም ልዩ ሁኔታ፣
• እድሜ ልክ ፍርደኛ ከሆነ 12 አመት እስር መጨረሱን፣ ሌሎች ፍርደኞች 1/3ኛ እስር መጨረሳቸውን፣ የግዴታ ስራ ካለበት ይህን መጨረሱን፣ ናቸው፡፡
ቦርዱ የሙስና፣ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ሽብር፣ በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ፣ ሀሰተኛ ገንዘብ መስራት ማዛወር፣ አደገኛ እፅ፣ ሴቶችና ህፃናት መድፈር ወይም መጥለፍ፣ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀም ወንጀል የፈፀሙ ፍርደኞችን ጉዳይ በጥንቃቄ በልዩ ሁኔታ ካልሆነ እደሌሎች ወንጀሎች አያይም፡፡
በዚህ መልክ ታይቶ የሚፈቀድ የይቅርታ ውሳኔ ውጤትን ስንመለከት ውሳኔው በግልፅ በከፊል መሆኑ ካልተመለከተ በቀር ይቅርታው የፍርድ ቅጣቶችን በሙሉ ያስቀራል፡፡ ሆኖም ይቅርታ ከወንጀል ፍርዱ የሚመነጩ የፍትሐብሔር ሀላፊነቶችን አያስቀርም፡፡ በተጨማሪም በፍትሐብሔር የጠፋውን እንደነበር ለመመለስ እና በተበዳይ ላይ ለደረሰ ጉዳት የሚከፈል ካሳና ኪሳራ አያስቀርም፡፡ ሆኖም በተለይ ካልተገለፀ በቀር ለመንግስት ሊከፈል የሚገባ ወይም ያልተከፈለ ኪሳራ ቀሪ ይሆናል፡፡ ይቅርታው ከመሰጠቱ ቀድሞ የተፈፀሙ ቅጣቶች ደግሞ የፀኑ ይሆናሉ፡፡ ይቅርታ በተሰጠበት ወንጀል በአጥፊው ላይ የተያዘው የወንጀል ሪከርድ በወንጀለኞች መዝገብ ላይ ተመዝግቦ ይኖራል፡፡
ይቅርታ የተሰጠው በሀሰተኛ ወይም በተጭበረበረ ማስረጃ ተመስርቶ ከሆነ ይቅርታው ዋጋ አይኖረውም፡፡
በቅድመ ሁኔታ ላይ ተመስርቶ የተሰጠ ይቅርታ ቅድመ ሁኔታው ከተጣሰ ዋጋ ያጣል፡፡ በዚህም መሰረት አጥፊው ቀሪ ቅጣቱን እንዲፈፅም ለማድረግ እንዲቻል ቦርዱ ይቅርታው እንዲሰረዝ ክብርት ፕሬዚዳንት ትእዛዝ እንዲሰጡ የውሳኔ ሀሳብ ያቀርባል፣ ይህ ተቀባይነት እንዳገኘ ትእዛዙ ለአጥፊው እንዲደርሰው ይደረግና ቅሬታ ካለው ትእዛዙ በደረሰው በአስራ አምስት ቀን ለቦርዱ ማቅረብ አለበት፡፡ ቅሬታው ተቀባይነት ካጣ የይቅርታ ምስክር ወረቀቱን እንዲመልስ ይደረጋል፣ በዚህም መሰረት የመያዣ ትእዛዝ እንዲሰጥ ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጥያቄ ቀርቦ ቀሪ ቅጣቱን እንዲፈፅም ይደረጋል፡፡
በአጠቃላይ የይቅርታ አላማ ከላይ እንደተመለከትነው አጥፊዎች ከጥፋታቸው ታርመውና ተፀፅተው ህግ አክባሪና መልካም ዜጋ ሆነው መኖር እዲችሉ ለማድረግ የሚሰጥ እድል ነው፡፡ የወንጀል ቅጣታቸው የመጨረሻ የሆነ፣ አንድ ሶስተኛ እስራታቸውን የጨረሱ፣ በማረሚያ ቤት በመልካም ባህሪ የቆዩ፣ ከጥፋታቸው የተፀፀቱና በቀጣይም ህግን አክብረው ለመኖር የሚችሉ ሰዎች የሚያገኙት ሁለተኛ እድል ሲሆን ይቅርታ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ ብሎም ከወንጀል የተጠበቀ ለማድረግ ይረዳል፡፡ ይቅርታ የሚሰጣቸው ሰዎችም ይህን ተገንዘበው ህብረተሰቡን በመካስ በህግ አክባሪነትና በመልካም ስነ ምግባር መመራት ይጠበቅባቸዋል፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ሠ/መ/ቁጥር 211841 ጥቅምት 30 ቀን 2015 ዓ/ም
በአንድ ወገን ብቻ የሚደረግ ዉል መሠረዝ (Unilateral cancellation of contract) ተግባራዊ ሊሆን የሚችለዉ በፍ/ብ/ሕጉ ከቁጥር 1786 እስከ 1889 ከተደነገጉት አራት ቅድመ ሁኔታዎች አንዱ ተሟልቶ ሲገኝ ነዉ፡፡እነዚህም ቅድመ ሁኔታዎች፡-(1) የዉል ማፍረሻ የሚሆኑ የዉል ቃሎች በዉሉ ተገልጸዉ ሲገኙና ይሄዉ ሁኔታ ተፈጽሞ ሲገኝ ፤(2) ቁርጠኛ የሆነ የዉል መፈጸሚያ ጊዜ በዉሉ ከተመለከተ፣በማስጠንቀቂያዉ ላይ በተሰጠዉ ጊዜ ወይም በፍርድ ቤት በተሰጠ የችሮታ ጊዜ ዉስጥ ተዋዋዩ ግዴታዉን ካልተወጣ ፤(3) ከተዋዋዮቹ አንደኛዉ ወገን የገባበትን ግዴታ ለመፈጸም የማይቻለዉ ሆኖ ከተገኘና በዚህ ምክንያት የዉሉ መሰረታዊ ስምምነት ከተነካ ፤ እንዲሁም (4) ከተዋዋዮቹ አንዱ ወገን የዉል ግዴታዉን የማይፈጽም ስለመሆኑ ግልጽ በሆነ መንገድ ሲያሳዉቅ የሚሉ ናቸዉ፡፡ሕጉ እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎች በመስፈርትነት ያስቀመጠዉ በተቻለ መጠን በሕግ አግባብ የተደረጉ ዉሎች እንዲፈጸሙ ጥበቃ ለማድረግና በተናጠል የሚደረገዉ የዉል መሰረዝ የመፍትሄ አማራጭ በልዩ ሁኔታ በተወሰኑ ሁኔታዎች ብቻ ተፈጻሚ እንዲሆን በመፈለግ ነዉ፡፡ ስለሆነም አንደኛዉ ተዋዋይ ወገን ሌላዉ ወገን ግዴታዉን ባለመወጣቱ ዉሉን በተናጠል ሰርዣለሁ በማለት በተከራከረ ጊዜ ከተጠቀሱት ቅድመ ሁኔታዎች መካከል ቢያንስ አንዱ መኖሩን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡
በአንድ ወገን ብቻ የሚደረግ ዉል መሠረዝ (Unilateral cancellation of contract) ተግባራዊ ሊሆን የሚችለዉ በፍ/ብ/ሕጉ ከቁጥር 1786 እስከ 1889 ከተደነገጉት አራት ቅድመ ሁኔታዎች አንዱ ተሟልቶ ሲገኝ ነዉ፡፡እነዚህም ቅድመ ሁኔታዎች፡-(1) የዉል ማፍረሻ የሚሆኑ የዉል ቃሎች በዉሉ ተገልጸዉ ሲገኙና ይሄዉ ሁኔታ ተፈጽሞ ሲገኝ ፤(2) ቁርጠኛ የሆነ የዉል መፈጸሚያ ጊዜ በዉሉ ከተመለከተ፣በማስጠንቀቂያዉ ላይ በተሰጠዉ ጊዜ ወይም በፍርድ ቤት በተሰጠ የችሮታ ጊዜ ዉስጥ ተዋዋዩ ግዴታዉን ካልተወጣ ፤(3) ከተዋዋዮቹ አንደኛዉ ወገን የገባበትን ግዴታ ለመፈጸም የማይቻለዉ ሆኖ ከተገኘና በዚህ ምክንያት የዉሉ መሰረታዊ ስምምነት ከተነካ ፤ እንዲሁም (4) ከተዋዋዮቹ አንዱ ወገን የዉል ግዴታዉን የማይፈጽም ስለመሆኑ ግልጽ በሆነ መንገድ ሲያሳዉቅ የሚሉ ናቸዉ፡፡ሕጉ እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎች በመስፈርትነት ያስቀመጠዉ በተቻለ መጠን በሕግ አግባብ የተደረጉ ዉሎች እንዲፈጸሙ ጥበቃ ለማድረግና በተናጠል የሚደረገዉ የዉል መሰረዝ የመፍትሄ አማራጭ በልዩ ሁኔታ በተወሰኑ ሁኔታዎች ብቻ ተፈጻሚ እንዲሆን በመፈለግ ነዉ፡፡ ስለሆነም አንደኛዉ ተዋዋይ ወገን ሌላዉ ወገን ግዴታዉን ባለመወጣቱ ዉሉን በተናጠል ሰርዣለሁ በማለት በተከራከረ ጊዜ ከተጠቀሱት ቅድመ ሁኔታዎች መካከል ቢያንስ አንዱ መኖሩን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡
ታክስን/ግብርን ዘግይቶ መክፈል የሚያስከትለው ቅጣት
ታክስዎን/ግብርዎን በወቅቱ ሲከፍሉ ከብዙ እንግልት ከመዳንዎ በተጨማሪ አላስፈላጊ ቅጣት ከመቀጣት ይድናሉ፡፡ ግብርን በወቅቱ ከከፈሉ ደግሞ ለሀገርዎ እና ለእርስዎ የሚጠቅመውን በወቅቱ እና በአስፈላጊው ወቅት እንዳደረጉ ይቆጠራል፡፡
ታክስዎን በተለያየ ምክንያት ሳይከፍሉ ካዘገዩ ከሚደርስብዎት ውጣ ውረድ በተጨማሪ ቅጣቶችንም ለማስተናገድ ይገደዳሉ፡፡ ከነኚህ ቅጣቶች ውስጥ ለእርስዎ ለግንዛቤ ይረዳዎት ዘንድ የሚከተሉት ተቀንጭበው ቀርበዋል፡፡
ማንኛውም ታክስ ከፋይ በታክስ መክፈያ ጊዜው ውስጥ ታክስ ሳይከፍል ከቀረ ለዘገየበት ጊዜ፦
1. ለአንድ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ታክስ ላይ 5% (አምስት በመቶ)፤ እና
2. ከዚያ በኋላ ለዘገየበት ለእያንዳንዱ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ታክስ ላይ ተጨማሪ 2% (ሁለት በመቶ)፤ ቅጣት ይከፈላል፡፡
I. የሚጣለው የቅጣት መጠን ከዋናው የታክስ ዕዳ መብለጥ የለበትም፡፡
II. መከፈል በማይገባው ታክስ ላይ ሳይከፈል በዘገየበት የተጣለ ቅጣት ለታክስ ከፋዩ ይመለሳል፡፡
III. ታክስን ዘግይቶ መክፈል የሚያስከትለው ቅጣት ከተከፋይ ሂሣብ ላይ ተቀንሶ ከሚከፈል ታክስ ጋር በተገናኘ የሚጣል ቅጣት በሚመለከተው ያልተከፈለ ታክስ ላይ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡
ታክስዎን/ግብርዎን በወቅቱ ሲከፍሉ ከብዙ እንግልት ከመዳንዎ በተጨማሪ አላስፈላጊ ቅጣት ከመቀጣት ይድናሉ፡፡ ግብርን በወቅቱ ከከፈሉ ደግሞ ለሀገርዎ እና ለእርስዎ የሚጠቅመውን በወቅቱ እና በአስፈላጊው ወቅት እንዳደረጉ ይቆጠራል፡፡
ታክስዎን በተለያየ ምክንያት ሳይከፍሉ ካዘገዩ ከሚደርስብዎት ውጣ ውረድ በተጨማሪ ቅጣቶችንም ለማስተናገድ ይገደዳሉ፡፡ ከነኚህ ቅጣቶች ውስጥ ለእርስዎ ለግንዛቤ ይረዳዎት ዘንድ የሚከተሉት ተቀንጭበው ቀርበዋል፡፡
ማንኛውም ታክስ ከፋይ በታክስ መክፈያ ጊዜው ውስጥ ታክስ ሳይከፍል ከቀረ ለዘገየበት ጊዜ፦
1. ለአንድ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ታክስ ላይ 5% (አምስት በመቶ)፤ እና
2. ከዚያ በኋላ ለዘገየበት ለእያንዳንዱ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ታክስ ላይ ተጨማሪ 2% (ሁለት በመቶ)፤ ቅጣት ይከፈላል፡፡
I. የሚጣለው የቅጣት መጠን ከዋናው የታክስ ዕዳ መብለጥ የለበትም፡፡
II. መከፈል በማይገባው ታክስ ላይ ሳይከፈል በዘገየበት የተጣለ ቅጣት ለታክስ ከፋዩ ይመለሳል፡፡
III. ታክስን ዘግይቶ መክፈል የሚያስከትለው ቅጣት ከተከፋይ ሂሣብ ላይ ተቀንሶ ከሚከፈል ታክስ ጋር በተገናኘ የሚጣል ቅጣት በሚመለከተው ያልተከፈለ ታክስ ላይ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡
222680.pdf
869 KB
በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 2005/1 ላይ የሚገኘው parol evidence rule በውል አዋዋይ ፊት ተረጋግጦ ያልተመዘገበ የቤት ሽያጭ ውል መኖሩ በሚታመንበት ጊዜ ተፈጻሚነት የለውም። የውሉ ይዘት ለምሳሌ የገንዘቡ መጠን፡ በውሉ ላይ ያለው ቀን ወዘተ በሌላ ውጫዊ ማስረጃ ሊስተባበል ይችላል።
በውል አዋዋይ ፊት ተረጋግጦ ያልተመዘገበ የቤት ሽያጭ ውል መኖሩ ታምኖ የውሉ ይዘት ፊርማን ጨምሮ በአከራከረ ጊዜ በምን አይነት ማስረጃ ሊረጋገጥ ይገባል? የሚለው ጥያቄ በተመለከተ የሰበር ችሎት የሚከተለውን የህግ ትርጉም ሰጥቷል።
የቤት ሽያጭ ውል በሕግ ሥልጣን በተሰጠው ውል አዋዋይ ፊት መደረግ አለበት በሚል በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1723/1 ስር የተደነገገበት አንዱ አላማ ውሉ በጽሁፍ በሰፈረው አግባብ በእርግጥ የተደረገ ስለመሆኑ እና ይዘቱም እምነት የሚጣልበት መሆኑን ለማረጋገጥ ነው፡፡በመሆኑም በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 2005/1 ስር በጽሑፍ ሰነድ ላይ የሚገኝ የስምምነት ቃል እንዲሁም በላዩ ላይ የተጻፈው ቀን በፈራሚዎቹ መካከል ሙሉ እምነት የሚጣልበት በቂ ማስረጃ ነው የሚለው በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1678/ሐ፣1719/2 እና 1723/1 ስር በተደነገገው መሰረት በሕግ የታዘዘውን የአጻጻፍ ሥርዓት ተከትሎ ለተደረገ ውል እንጂ ለማንኛውም ውል አይደለም፡፡
በውል አዋዋይ ፊት ተረጋግጦ ያልተመዘገበ የቤት ሽያጭ ውል መኖሩ ታምኖ የውሉ ይዘት ፊርማን ጨምሮ በአከራከረ ጊዜ በምን አይነት ማስረጃ ሊረጋገጥ ይገባል? የሚለው ጥያቄ በተመለከተ የሰበር ችሎት የሚከተለውን የህግ ትርጉም ሰጥቷል።
የቤት ሽያጭ ውል በሕግ ሥልጣን በተሰጠው ውል አዋዋይ ፊት መደረግ አለበት በሚል በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1723/1 ስር የተደነገገበት አንዱ አላማ ውሉ በጽሁፍ በሰፈረው አግባብ በእርግጥ የተደረገ ስለመሆኑ እና ይዘቱም እምነት የሚጣልበት መሆኑን ለማረጋገጥ ነው፡፡በመሆኑም በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 2005/1 ስር በጽሑፍ ሰነድ ላይ የሚገኝ የስምምነት ቃል እንዲሁም በላዩ ላይ የተጻፈው ቀን በፈራሚዎቹ መካከል ሙሉ እምነት የሚጣልበት በቂ ማስረጃ ነው የሚለው በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1678/ሐ፣1719/2 እና 1723/1 ስር በተደነገገው መሰረት በሕግ የታዘዘውን የአጻጻፍ ሥርዓት ተከትሎ ለተደረገ ውል እንጂ ለማንኛውም ውል አይደለም፡፡
🔹The Commercial Bank of Ethiopia New Vacancy
Position :1 Senior Attorney
Position :2 Senior Legal Advisor
Position :3 Legal Surveillance Officer
Education : LLM/LLB Degree in Law , Banking, Financial Institutions or other Business Organizations.Diploma in police science or Diploma in social science fields
Date March 27, 2023 - April 05, 2023.
How to Apply
👇👇👇
https://ethiolatestjobs.com/job/commercial-bank-of-ethiopia/
Share for your friends
👇👇👇
https://t.me/shegarjob
Position :1 Senior Attorney
Position :2 Senior Legal Advisor
Position :3 Legal Surveillance Officer
Education : LLM/LLB Degree in Law , Banking, Financial Institutions or other Business Organizations.Diploma in police science or Diploma in social science fields
Date March 27, 2023 - April 05, 2023.
How to Apply
👇👇👇
https://ethiolatestjobs.com/job/commercial-bank-of-ethiopia/
Share for your friends
👇👇👇
https://t.me/shegarjob
ethiolatestjobs.com
Commercial Bank of Ethiopia - ethiolatestjobs.com
በምስሉ ላይ የምትመለከቱት Ricky Jackson ይባላል። Cleveland, Ohio ነዋሪ ሲሆን ገና በ18 አመቱ በለጋ እድሜው ባልሰራው ወንጀል የሞት ፍርድ ተፈርዶበት 39 አመት ከታሰረ በኋላ (አብዛኛውን ግዜ የሞት ፍርድ የሀገሪቱ ርዕሰ ብሄር ካላፀደቁት ወደ እድሜ ልክ ይለወጣል)፣ ትክክለኛው ወንጀል ፈጻሚ በመገኘቱ ዳጎስ ያለ ካሳ ተከፍሎት በነፃ የተለቀቀ ሰው ነው።
እናም ልክ ከእስር ቤት ተለቆ ሲወጣ ያሳሰረውን ሰው አገኘውና ... «ይቅር ብዬሃለው» .... ብሎ አቀፈው።
ቃለ መጠይቅ ላደረጉለት ጋዜጠኞች ደግሞ እንዲ ሲል ተናገረ :-
....«እስር ቤት ውስጥ ነህ ማለት እስረኛ ነህ ማለት አይደለም»....
ነጻነት ያለው ያላችሁበት ስፍራ ላይ ሳይሆን አይምሯቹ ውስጥ ነው። የቂምና የጥላቻ እስረኛ እንዳትሆኑ ይቅር በሉ!!
ይቅር በሉ፣ መራመድ አታቁሙ ፣ ጉዳታችሁ ላይ አትቆዩ! ህይወት ሰፊና ፣ ብዙ ደርዝ ያላት የጉዞ ሃዲድ ናት!!
ይቅርታ ለራስ የሚሰጥ ድንቅ ስጦታ ነው ሰው ይቅር ማለት ሲጀምር ህይወት ይጀምራል።
የበደለንን ይቅር ማለት መሸነፍ ሣይሆን ፍቅርን ማስተማር ፣ ቀንነትን መዝራት ፣ ህይወትን ማደስ ነው።
ፈጣሪ ይቅርታን የሚጠይቅ አንደበትና ይቅር የሚል ብሩህ ልብ ይስጠን!
ምንጭ ከአንቂ መጻሕፍት ገፆች
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
እናም ልክ ከእስር ቤት ተለቆ ሲወጣ ያሳሰረውን ሰው አገኘውና ... «ይቅር ብዬሃለው» .... ብሎ አቀፈው።
ቃለ መጠይቅ ላደረጉለት ጋዜጠኞች ደግሞ እንዲ ሲል ተናገረ :-
....«እስር ቤት ውስጥ ነህ ማለት እስረኛ ነህ ማለት አይደለም»....
ነጻነት ያለው ያላችሁበት ስፍራ ላይ ሳይሆን አይምሯቹ ውስጥ ነው። የቂምና የጥላቻ እስረኛ እንዳትሆኑ ይቅር በሉ!!
ይቅር በሉ፣ መራመድ አታቁሙ ፣ ጉዳታችሁ ላይ አትቆዩ! ህይወት ሰፊና ፣ ብዙ ደርዝ ያላት የጉዞ ሃዲድ ናት!!
ይቅርታ ለራስ የሚሰጥ ድንቅ ስጦታ ነው ሰው ይቅር ማለት ሲጀምር ህይወት ይጀምራል።
የበደለንን ይቅር ማለት መሸነፍ ሣይሆን ፍቅርን ማስተማር ፣ ቀንነትን መዝራት ፣ ህይወትን ማደስ ነው።
ፈጣሪ ይቅርታን የሚጠይቅ አንደበትና ይቅር የሚል ብሩህ ልብ ይስጠን!
ምንጭ ከአንቂ መጻሕፍት ገፆች
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Urgent Vacancy
1. Driver
Full time
Work station: Addis Ababa
👉Having experience is advisable.
👉 How to Apply 👈
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
consultantentrust@gmail.com
Deadline
March, 30/2023
Share for your friends
👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
1. Driver
Full time
Work station: Addis Ababa
👉Having experience is advisable.
👉 How to Apply 👈
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
consultantentrust@gmail.com
Deadline
March, 30/2023
Share for your friends
👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ
ለፋርድ አፈጻጻም ተገልጋዮች በሙሉ_1.PDF
891.2 KB
የመገናኛ ብዙኃን በችሎት ዘገባ ጊዜ ሊከተሏቸው የሚገቡ ጥንቃቄዎች
መገናኛ ብዙኃን ዘርፈ ብዙ መረጃዎችን ለህዝብ የሚያቀርቡ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ለህዝብ ከሚያቀርቧቸው መረጃዎች መካከል የፍርድ ቤት ክርክሮችን የተመለከቱ መረጃዎች ይጠቀሳሉ፡፡ በህግ መሰረት እንይገለፁ ከተከለከሉ ወይም የፍርድ ቤት ነፃነትን የሚጋፉ ካልሆነ በቀር የሚሰጡ ውሳኔዎች፣ ትእዛዞች እንዲሁም ሌሎች ሂደቶች ለህዝብ ግልፅ በመሆናቸው መገናኛ ብዙህን መረጃዎቹን ለህዝብ ያደርሳሉ፡፡ መገናኛ ብዙኃን እነዚህ ግልፅ የሆኑ የችሎት ሥራዎች እና የክርክር ሂደቶች ሲዘግቡ ግን ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የመገናኛ ብዙኃን ምንነት፣ መገናኛ ብዙኃን በችሎት ዘገባ ጊዜ ሊያደርጓቸው የሚገቡ ጥንቃቄዎች እና የሥነ ምግባር ሁኔታዎች ይዳሰሳሉ፡፡
የመገናኛ ብዙኃን ምንነት
በመገናኛ ብዙኃን በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 አንቀፅ 2(1) መሠረት መገናኛ ብዙኃን ማለት በየጊዜው የሚወጣ ህትመትን የብሮድካስት አገልግሎትን እና የበይነመረብ የመገናኛ ብዙኃንን በመጠቀም የዜና እና የፕሮግራም አገልግሎት ለሕዝብ ለማቅረብ የተቋቋሙ አካላት ሲሆኑ ይህም መፃሕፍትን፣ ማኅበራዊ መገኛኛ ብዙኃንን፣ ጦማሮችን እና በየጊዜው የሚወጣ ህትመት አካል ያልሆኑ ፎቶ፣ ስዕልና ካርቱን ሳይጨምር የዜና አገልግሎት ድርጅቶችን የሚያካትት ነው፡፡
በችሎት ዘገባ ወቅት ሊደረጉ የሚገቡ ጥንቃቄዎች
1. የተከሳሽን ንፁህ ሆኖ የመገመት መብት ማክበር
ማንኛዉም ተከሳሽ የጥፋተኝነት ፍርድ ከመሰጠቱ በፊት ከወንጀል ንፁህ ሆኖ የመገመት መብት እንዳለው በህግ መንግስቱ አንቀፅ 20/3/ ስር ተመላክቷል፡፡ ምክንያቱም ከክርክር በኋላ ተከሳሹ ነፃ ሆኖ ሊገኝም ስለሚችል ነው፡፡ በመሆኑም ጋዜጠኖች የችሎት ዘገባዎችን ሲሰሩ የጥፋተኝት ፍርድ ያልተሰጠበትን ተከሳሽ ጥፋተኛ አድርጎ ከመዘገብ መቆጠብ አለባቸው፡፡
2. ሚዛናዊ መሆን
መገናኛ ብዙኃን በክርክር ላይ ባለ እና ውሳኔ ባልተሰጠው ጉዳይ ላይ አንዱ ወገን አሸናፊ በሚያስመስል መልኩ ወይም ለአንዱ ተከራካሪ ወገን በማዳላት ሚዛናዊ ባልሆነ አግባብ መዘገብ የለባቸውም፡፡ የሚያቀርቧቸው ዘገባዎችና ትንተናዎች ፍርድ ቤት አከራክሮ ውሳኔ ሊሰጥበት በሚገባው ጉዳይ ከፍርድ ቤቱ አስቀድሞ ውሳኔ መስጠት በሚመስል መልኩ የሚቀርቡ መሆን የለባቸውም፡፡
3. የምስክሮች ከጥቃት የመጠበቅ መብት
ማንኛውም ምስክር ለፍትህ እርዳት የመስጠት ህጋዊ ግዴታ አለበት፡፡ ጥቆማ ወይም ምስክርነት በመስጠቱ ምክንያት በምስክሮችና በቤተሰቦቻቸው ህይወት ወይም ንብረት ላይ አደጋ የሚፈጠር ከሆነ የምስክሮች ማንነት፣ አድራሻ፣ ንብረት እንዳይገለፅ በማድረግ የህግ ጥብቃ ይደረግላቸዋል፡፡ በመሆኑም መሰል ሁኔታዎች ሲኖሩ የምስክሮች ህይወት ወይም ንብረት አደጋ ላይ እንዳይወድቅ በችሎት የተገኙ ምስክሮችን ማንነት በመገናኛ ብዙኃን ከመግለፅና በዘገባ ዉስጥ ከማካተት መቆጠብ ይገባል፡፡
4. የጉዳዩን ፍሬ ነገር እንዳይዛባ መጠንቀቅ
መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎችን ሲሰሩ በችሎት ሂደት የነበረውን ሁኔታ ሳይጨምሩና ሳይቀንሱ በመዘገብ የጉዳዩ ፍሬ ነገሮች እንዳይዘቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው፡፡ በተጨማሪም አንዳንድ ጊዜ ህግ የራሱ የሆኑ ልዩ ባህሪያት ያሉት በመሆኑ ዘገባዎች የተዛቡ እንዳይሆኑ ከህግ ባለሞያ ማብራሪያ በመጠየቅ ቢሰሩ ተሻለ ይሆናል፡፡
5. ችሎት ማክበር
ችሎት የራሱ ሥነ ሥርአት አለው፡፡ ማንኛውም በችሎት የሚገኝ ሰው ይህን የችሎት ሥርአት ማክበር ያለበት በመሆኑ ዘጋቢዎች ዘገባ ለመስራት በችሎት ሲገኙ የፍርድ ቤትን የችሎት ሥነ ሥርአት ጠንቅቆ ማወቅ እና ችሎት ማክበር ይጠበቅባቸዋል፡፡
6. የግል ህይወት መብትን ማክበር
የግል ህይወት መከበር በህገ መንግስቱ አንቀፅ 26 መሠረት በህግ ጥበቃ የተደረገለት ሰብዓዊ መብት ነው፡፡ ይህም መብት የአንድ ሰው የግል ሕይወት፣ ሰዉነት፣ ንብረት እንዲሁም የሚፃፃፋቸው ድብዳቤዎች የተጠበቁ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ይህ መብት ለሀገር ሰላም፣ ወንጀልን ለመከላከል፣ ለህዝብ ጤና እና ሞራል ሲባል በልዩ ሁኔታ በህግ መሰረት ብቻ ሊገደብ የሚችል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የሚሰሩ ዘገባዎች የተከራካሪ ወገኖችንም ሆነ የማንኛውንም ዜጋ የግል ነፃነትና መብት የሚጋፉ መሆን የለባቸውም፡፡
7. ሥነ ምግባር
እያንዳንዱ ሙያ የሚጠይቀው የራሱ የሆነ ሥነ ምግባር አለ፡፡ የመገናኛ ብዙኃን ባለሞያ መሆንም የሚጠይቀው የራሱ የሆነ የሙያ ሥነ ምግባር አለው፡፡ ለአብነትም ከአድሎ የፀዳ እና የተለያዩ ሀሳቦችን በእኩል የሚያስተናግድ ሊሆን ይገባል፡፡ በመሆኑም ማንኛውም የችሎት ዘገባ የሚሰራ ባለሞያ የሙያ ሥነ ምግባሩን በጥብቅ ማክበር ይጠበቅበታል፡፡
ማጠቃለያ
መገናኛ ብዙኃን የችሎት ዘገባዎችን ጨምሮ ሌሎች መረጃዎችን ለዜጎች በሚያደርሱበት ወቅት ሊከተሏቸው የሚገቡ የሥነ ምግባር ደንቦችን ማክበር ይገባቸዋል፡፡ በተለይ ችሎት ውስጥ መረጃ ሲሰበሱቡም ሆነ ሲዘግቡ በፍርድ ቤት የተቀመጡ የችሎት መመሪያዎችንና የችሎት ሥነ ሥርአት በጥንቃቄ ሊያከብሩ የሚገባ ከመሆኑም በተጨማሪ ለህዝብ የሚደርሱ ዘገባዎች የተከራካሪ ወገኖችን መብትና ነፃነትን የሚያከብሩ፣ የምስክሮችን ደህንነት የሚያስጠብቁ እንዲሁም የፍርድ ቤትን ነፃነት የማይጋፉ መሆን ይገባቸዋል፡፡
FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
መገናኛ ብዙኃን ዘርፈ ብዙ መረጃዎችን ለህዝብ የሚያቀርቡ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ለህዝብ ከሚያቀርቧቸው መረጃዎች መካከል የፍርድ ቤት ክርክሮችን የተመለከቱ መረጃዎች ይጠቀሳሉ፡፡ በህግ መሰረት እንይገለፁ ከተከለከሉ ወይም የፍርድ ቤት ነፃነትን የሚጋፉ ካልሆነ በቀር የሚሰጡ ውሳኔዎች፣ ትእዛዞች እንዲሁም ሌሎች ሂደቶች ለህዝብ ግልፅ በመሆናቸው መገናኛ ብዙህን መረጃዎቹን ለህዝብ ያደርሳሉ፡፡ መገናኛ ብዙኃን እነዚህ ግልፅ የሆኑ የችሎት ሥራዎች እና የክርክር ሂደቶች ሲዘግቡ ግን ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የመገናኛ ብዙኃን ምንነት፣ መገናኛ ብዙኃን በችሎት ዘገባ ጊዜ ሊያደርጓቸው የሚገቡ ጥንቃቄዎች እና የሥነ ምግባር ሁኔታዎች ይዳሰሳሉ፡፡
የመገናኛ ብዙኃን ምንነት
በመገናኛ ብዙኃን በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 አንቀፅ 2(1) መሠረት መገናኛ ብዙኃን ማለት በየጊዜው የሚወጣ ህትመትን የብሮድካስት አገልግሎትን እና የበይነመረብ የመገናኛ ብዙኃንን በመጠቀም የዜና እና የፕሮግራም አገልግሎት ለሕዝብ ለማቅረብ የተቋቋሙ አካላት ሲሆኑ ይህም መፃሕፍትን፣ ማኅበራዊ መገኛኛ ብዙኃንን፣ ጦማሮችን እና በየጊዜው የሚወጣ ህትመት አካል ያልሆኑ ፎቶ፣ ስዕልና ካርቱን ሳይጨምር የዜና አገልግሎት ድርጅቶችን የሚያካትት ነው፡፡
በችሎት ዘገባ ወቅት ሊደረጉ የሚገቡ ጥንቃቄዎች
1. የተከሳሽን ንፁህ ሆኖ የመገመት መብት ማክበር
ማንኛዉም ተከሳሽ የጥፋተኝነት ፍርድ ከመሰጠቱ በፊት ከወንጀል ንፁህ ሆኖ የመገመት መብት እንዳለው በህግ መንግስቱ አንቀፅ 20/3/ ስር ተመላክቷል፡፡ ምክንያቱም ከክርክር በኋላ ተከሳሹ ነፃ ሆኖ ሊገኝም ስለሚችል ነው፡፡ በመሆኑም ጋዜጠኖች የችሎት ዘገባዎችን ሲሰሩ የጥፋተኝት ፍርድ ያልተሰጠበትን ተከሳሽ ጥፋተኛ አድርጎ ከመዘገብ መቆጠብ አለባቸው፡፡
2. ሚዛናዊ መሆን
መገናኛ ብዙኃን በክርክር ላይ ባለ እና ውሳኔ ባልተሰጠው ጉዳይ ላይ አንዱ ወገን አሸናፊ በሚያስመስል መልኩ ወይም ለአንዱ ተከራካሪ ወገን በማዳላት ሚዛናዊ ባልሆነ አግባብ መዘገብ የለባቸውም፡፡ የሚያቀርቧቸው ዘገባዎችና ትንተናዎች ፍርድ ቤት አከራክሮ ውሳኔ ሊሰጥበት በሚገባው ጉዳይ ከፍርድ ቤቱ አስቀድሞ ውሳኔ መስጠት በሚመስል መልኩ የሚቀርቡ መሆን የለባቸውም፡፡
3. የምስክሮች ከጥቃት የመጠበቅ መብት
ማንኛውም ምስክር ለፍትህ እርዳት የመስጠት ህጋዊ ግዴታ አለበት፡፡ ጥቆማ ወይም ምስክርነት በመስጠቱ ምክንያት በምስክሮችና በቤተሰቦቻቸው ህይወት ወይም ንብረት ላይ አደጋ የሚፈጠር ከሆነ የምስክሮች ማንነት፣ አድራሻ፣ ንብረት እንዳይገለፅ በማድረግ የህግ ጥብቃ ይደረግላቸዋል፡፡ በመሆኑም መሰል ሁኔታዎች ሲኖሩ የምስክሮች ህይወት ወይም ንብረት አደጋ ላይ እንዳይወድቅ በችሎት የተገኙ ምስክሮችን ማንነት በመገናኛ ብዙኃን ከመግለፅና በዘገባ ዉስጥ ከማካተት መቆጠብ ይገባል፡፡
4. የጉዳዩን ፍሬ ነገር እንዳይዛባ መጠንቀቅ
መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎችን ሲሰሩ በችሎት ሂደት የነበረውን ሁኔታ ሳይጨምሩና ሳይቀንሱ በመዘገብ የጉዳዩ ፍሬ ነገሮች እንዳይዘቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው፡፡ በተጨማሪም አንዳንድ ጊዜ ህግ የራሱ የሆኑ ልዩ ባህሪያት ያሉት በመሆኑ ዘገባዎች የተዛቡ እንዳይሆኑ ከህግ ባለሞያ ማብራሪያ በመጠየቅ ቢሰሩ ተሻለ ይሆናል፡፡
5. ችሎት ማክበር
ችሎት የራሱ ሥነ ሥርአት አለው፡፡ ማንኛውም በችሎት የሚገኝ ሰው ይህን የችሎት ሥርአት ማክበር ያለበት በመሆኑ ዘጋቢዎች ዘገባ ለመስራት በችሎት ሲገኙ የፍርድ ቤትን የችሎት ሥነ ሥርአት ጠንቅቆ ማወቅ እና ችሎት ማክበር ይጠበቅባቸዋል፡፡
6. የግል ህይወት መብትን ማክበር
የግል ህይወት መከበር በህገ መንግስቱ አንቀፅ 26 መሠረት በህግ ጥበቃ የተደረገለት ሰብዓዊ መብት ነው፡፡ ይህም መብት የአንድ ሰው የግል ሕይወት፣ ሰዉነት፣ ንብረት እንዲሁም የሚፃፃፋቸው ድብዳቤዎች የተጠበቁ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ይህ መብት ለሀገር ሰላም፣ ወንጀልን ለመከላከል፣ ለህዝብ ጤና እና ሞራል ሲባል በልዩ ሁኔታ በህግ መሰረት ብቻ ሊገደብ የሚችል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የሚሰሩ ዘገባዎች የተከራካሪ ወገኖችንም ሆነ የማንኛውንም ዜጋ የግል ነፃነትና መብት የሚጋፉ መሆን የለባቸውም፡፡
7. ሥነ ምግባር
እያንዳንዱ ሙያ የሚጠይቀው የራሱ የሆነ ሥነ ምግባር አለ፡፡ የመገናኛ ብዙኃን ባለሞያ መሆንም የሚጠይቀው የራሱ የሆነ የሙያ ሥነ ምግባር አለው፡፡ ለአብነትም ከአድሎ የፀዳ እና የተለያዩ ሀሳቦችን በእኩል የሚያስተናግድ ሊሆን ይገባል፡፡ በመሆኑም ማንኛውም የችሎት ዘገባ የሚሰራ ባለሞያ የሙያ ሥነ ምግባሩን በጥብቅ ማክበር ይጠበቅበታል፡፡
ማጠቃለያ
መገናኛ ብዙኃን የችሎት ዘገባዎችን ጨምሮ ሌሎች መረጃዎችን ለዜጎች በሚያደርሱበት ወቅት ሊከተሏቸው የሚገቡ የሥነ ምግባር ደንቦችን ማክበር ይገባቸዋል፡፡ በተለይ ችሎት ውስጥ መረጃ ሲሰበሱቡም ሆነ ሲዘግቡ በፍርድ ቤት የተቀመጡ የችሎት መመሪያዎችንና የችሎት ሥነ ሥርአት በጥንቃቄ ሊያከብሩ የሚገባ ከመሆኑም በተጨማሪ ለህዝብ የሚደርሱ ዘገባዎች የተከራካሪ ወገኖችን መብትና ነፃነትን የሚያከብሩ፣ የምስክሮችን ደህንነት የሚያስጠብቁ እንዲሁም የፍርድ ቤትን ነፃነት የማይጋፉ መሆን ይገባቸዋል፡፡
FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ከገቢ ግብር ነፃ የተደረጉ ገቢዎች
/ክፍል ሁለት/
ከገቢ ግብር ነፃ የተደረጉ ገቢዎችን በተመለከተ ክፍል አንድ መረጃ አቅርበን ነበር የመረጃውን ቀጣይ እና የመጨረሻ ክፍል እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡
የሚከተሉት ከመቀጠር የሚገኙ ገቢዎች ከግብር ነፃ ይሆናሉ፡-¬
ልብ ይበሉ:- ሚኒስትሩ በዚህ ፊደል ተራ በቁጥር (1) ፣(2) ፣(3) እና (5) በተመለከቱት ላይ ባወጣው መመሪያ ቁጥር 1/2011 መሰረት ያደረገው ገደብ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለተቀጣሪው የሚከፈሉ የሚከተሉት ገቢዎች ከገቢ ግብር ነፃ ናቸው፡-
1. በሥራ ውል መሠረት ለሠራተኛው የሚከፈል የትራንስፖርት አበል፤
2. በሥራ ቦታው ወይም በሥራ ሁኔታው አስቸጋሪነት ምክንያት ለሠራተኛው የሚከፈል አበል፤
3. ሠራተኛው ከመደበኛ ሥራው ውጪ ሥራውን ለማከናወን ሲንቀሳቀስ የሚከፈለው የመጓጓዣ ወጪ እና የውሎ አበል፤
4. የመጓጓዣ ወጪው በቅጥር ውሉ መሠረት የተከፈለ ከሆነ ከሥራ ቦታው ውጪ ተመልምሎ ለተቀጠረ ሠራተኛ ወደ ሥራው ሲመጣ ወይም ሥራውን አጠናቆ ሲመለስ የሚከፈለው የመጓጓዣ ወጪ፣ እንዲሁም የውጭ ሀገር ሠራተኞች ከሀገራቸው ሲመጡና ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ የሚከፈል የመጓጓዣ ወጪ፤
5. የማዕድን ማውጣት፣ የማኑፋክቸሪንግ እና የግብርና የንግድ ሥራ የሚሠራ ቀጣሪ ለተቀጣሪው በነፃ የሚያቀርበው ምግብና መጠጥ፤
6. የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት በውጭ አገር ለሚመድባቸው ሠራተኞች የሚከፈል አበል፤
7. ለሠራተኛው ጥቅም ተብሎ ከተቀጣሪው የወር ደመወዝ 15 % (አሥራ አምስት በመቶ) ባልበለጠ መጠን በየወሩ በቀጣሪው የሚዋጣ የጡረታ መዋጮ ወይም የፕሮቪደንት ፈንድ፤
8. በተቀባዩ ላይ በደረሰ ጉዳት ወይም በሌላ ሰው ሞት ምክንያት የሚከፈል ካሳ፤
9. በዚህ አዋጅ አንቀጽ 59 የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ስጦታው የመቀጠር፣የኪራይ ወይም የንግድ ሥራ ገቢ ካልሆነ በስተቀር በስጦታ ወይም በውርስ የሚገኝ ጥሬ ገንዘብ ወይም ሀብት፤
10. ድርጅቱ ከተቋቋመበት ዓላማ ጋር የማይገናኝ የንግድ ሥራ ገቢን ሳይጨምር ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት የሚያገኘው ገቢ፤
11. ገንዘብ በሚቆጠርበት ጊዜ ለሚደርሰው ጉድለት ማካካሻ በሚሆን መጠን ብቻ ቀጣሪው ለተቀጣሪው የሚከፍለው እና ለዚሁ ዓላማ መዋሉ የተረጋገጠ የጥሬ ገንዘብ ማካካሻ ክፍያ፤
12. በኢትዮጵያ ፀንቶ በሚሰራበት ሕግ መሠረት በተለይ ከገቢ ግብር ነፃ የተደረገ ገቢ፤
13. ለመኖሪያ ቤት ሠራተኞች የሚከፈል ደመወዝ፤
14. በነዳጅ ሥራ ላይ የተሰማራ ሥራ ተቋራጭ ለንዑስ ሥራ ተቋራጮች የሚፈፅመው ክፍያ፡፡
15. ለሠራተኛ የሚከፈል የትራንስፖርት አበል፤ በሥራ ቦታው ወይም በሥራ ሁኔታው አስቸጋሪነት ምክንያት የሚከፈል አበል፤ ሠራተኛው ከመደበኛ የሥራ ቦታ ውጪ ሲንቀሳቀስ የሚከፈለው የመጓጓዣ ወጪ እና የውሎ አበል፣ የማዕድን ማውጣት፣ የማኑፋክቸሪንግ እና የግብርና የንግድ ሥራ የሚሠራ ቀጣሪ ለተቀጣሪው በነፃ የሚያቀርበው ምግብና መጠጥ ከግብር ነጻ የሚሆነው የገንዘብ መጠን ልክ የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ ይወሰናል፡፡
16. የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ ለኢኮኖሚ፣ ለአስተዳደራዊ ወይም ለማህበራዊ ምክንያቶች አንድን ገቢ ከገቢ ግብር ነፃ ሊያደርግ ይችላል፡፡
ገቢዎች
/ክፍል ሁለት/
ከገቢ ግብር ነፃ የተደረጉ ገቢዎችን በተመለከተ ክፍል አንድ መረጃ አቅርበን ነበር የመረጃውን ቀጣይ እና የመጨረሻ ክፍል እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡
የሚከተሉት ከመቀጠር የሚገኙ ገቢዎች ከግብር ነፃ ይሆናሉ፡-¬
ልብ ይበሉ:- ሚኒስትሩ በዚህ ፊደል ተራ በቁጥር (1) ፣(2) ፣(3) እና (5) በተመለከቱት ላይ ባወጣው መመሪያ ቁጥር 1/2011 መሰረት ያደረገው ገደብ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለተቀጣሪው የሚከፈሉ የሚከተሉት ገቢዎች ከገቢ ግብር ነፃ ናቸው፡-
1. በሥራ ውል መሠረት ለሠራተኛው የሚከፈል የትራንስፖርት አበል፤
2. በሥራ ቦታው ወይም በሥራ ሁኔታው አስቸጋሪነት ምክንያት ለሠራተኛው የሚከፈል አበል፤
3. ሠራተኛው ከመደበኛ ሥራው ውጪ ሥራውን ለማከናወን ሲንቀሳቀስ የሚከፈለው የመጓጓዣ ወጪ እና የውሎ አበል፤
4. የመጓጓዣ ወጪው በቅጥር ውሉ መሠረት የተከፈለ ከሆነ ከሥራ ቦታው ውጪ ተመልምሎ ለተቀጠረ ሠራተኛ ወደ ሥራው ሲመጣ ወይም ሥራውን አጠናቆ ሲመለስ የሚከፈለው የመጓጓዣ ወጪ፣ እንዲሁም የውጭ ሀገር ሠራተኞች ከሀገራቸው ሲመጡና ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ የሚከፈል የመጓጓዣ ወጪ፤
5. የማዕድን ማውጣት፣ የማኑፋክቸሪንግ እና የግብርና የንግድ ሥራ የሚሠራ ቀጣሪ ለተቀጣሪው በነፃ የሚያቀርበው ምግብና መጠጥ፤
6. የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት በውጭ አገር ለሚመድባቸው ሠራተኞች የሚከፈል አበል፤
7. ለሠራተኛው ጥቅም ተብሎ ከተቀጣሪው የወር ደመወዝ 15 % (አሥራ አምስት በመቶ) ባልበለጠ መጠን በየወሩ በቀጣሪው የሚዋጣ የጡረታ መዋጮ ወይም የፕሮቪደንት ፈንድ፤
8. በተቀባዩ ላይ በደረሰ ጉዳት ወይም በሌላ ሰው ሞት ምክንያት የሚከፈል ካሳ፤
9. በዚህ አዋጅ አንቀጽ 59 የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ስጦታው የመቀጠር፣የኪራይ ወይም የንግድ ሥራ ገቢ ካልሆነ በስተቀር በስጦታ ወይም በውርስ የሚገኝ ጥሬ ገንዘብ ወይም ሀብት፤
10. ድርጅቱ ከተቋቋመበት ዓላማ ጋር የማይገናኝ የንግድ ሥራ ገቢን ሳይጨምር ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት የሚያገኘው ገቢ፤
11. ገንዘብ በሚቆጠርበት ጊዜ ለሚደርሰው ጉድለት ማካካሻ በሚሆን መጠን ብቻ ቀጣሪው ለተቀጣሪው የሚከፍለው እና ለዚሁ ዓላማ መዋሉ የተረጋገጠ የጥሬ ገንዘብ ማካካሻ ክፍያ፤
12. በኢትዮጵያ ፀንቶ በሚሰራበት ሕግ መሠረት በተለይ ከገቢ ግብር ነፃ የተደረገ ገቢ፤
13. ለመኖሪያ ቤት ሠራተኞች የሚከፈል ደመወዝ፤
14. በነዳጅ ሥራ ላይ የተሰማራ ሥራ ተቋራጭ ለንዑስ ሥራ ተቋራጮች የሚፈፅመው ክፍያ፡፡
15. ለሠራተኛ የሚከፈል የትራንስፖርት አበል፤ በሥራ ቦታው ወይም በሥራ ሁኔታው አስቸጋሪነት ምክንያት የሚከፈል አበል፤ ሠራተኛው ከመደበኛ የሥራ ቦታ ውጪ ሲንቀሳቀስ የሚከፈለው የመጓጓዣ ወጪ እና የውሎ አበል፣ የማዕድን ማውጣት፣ የማኑፋክቸሪንግ እና የግብርና የንግድ ሥራ የሚሠራ ቀጣሪ ለተቀጣሪው በነፃ የሚያቀርበው ምግብና መጠጥ ከግብር ነጻ የሚሆነው የገንዘብ መጠን ልክ የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ ይወሰናል፡፡
16. የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ ለኢኮኖሚ፣ ለአስተዳደራዊ ወይም ለማህበራዊ ምክንያቶች አንድን ገቢ ከገቢ ግብር ነፃ ሊያደርግ ይችላል፡፡
ገቢዎች
የዲጂታል መታወቂያ ምንነት እና የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ቁጥር 1284/2015 ዋና ዋና ገጽታዎች
ዘመናዊ የመታወቂያ ስርዓት በአንድ ሀገር ውስጥ ተግባራዊ ሲደረግ መሰረታዊ የሚባሉ ጠቀሜታዎች ያሉት ሲሆን፣ ከነዚህ ጠቀሜታዎች መካከልም ሃገራዊ ልማትን በአግባቡ ለማቀድ፣ ምጣኔ ሃብታዊ ሽግግር ለመፍጠር፣ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን፣ የሀብት ብክነትን ለመቀነስ፣ ወንጀልን ለመከላከል፣ ፖሊሲዎች ሲቀረጹ እና የልማት ሥራዎች ሲከናወኑ ድግግሞሽን ለመቅረፍ እና አካታችነትን ለማጎልበት የሚረዳ መሆኑ የተረጋገጠ ነው፡፡ በኢትዮጵያም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የበለፀገ፣ ዘርፍ ተሻጋሪ፣ መሠረታዊ የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት መዘርጋት አሰፈላጊ መሆኑ ታምኖበት የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት ተቋቁሞ ላለፉት ሁለት ዓመታት በግንባታና በሙከራ ሂደት ላይ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ ከተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች ጋር ለማስተሳሰር የሙከራ ትግበራ ስራዎችን በማከናወን ወደ 1.4 ሚሊዮን የሚጠጉ ነዋሪዎችን መዝግቦ አብዛኞቹን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ ተችሏል።
በዚህ የሙከራ ትግበራ ወቅት ከተከናወኑ ተግባራት ውስጥ ሌላው የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ማዘጋጀት ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ "የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ቁጥር 1284/2015" አድርጎ አፅድቆታል፡፡ አዋጁ ከሌሎች ሀገሮች የመታወቂያ አዋጆች አንፃር ዘግየት ብሎ የወጣ በመሆኑ በሌሎች ሀገሮች የታዩ ክፍተቶችን ለመድፈን በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ዘመኑ የደረሰበትን የዲጂታል መታወቂያ በዘመናዊ መልኩ ለነዋሪዎች ለመስጠት እና ለማስተዳደር በማለም የወጣ ነው፡፡ አዋጁ በርካታ ጉዳዮችን የያዘ ሲሆን፣ በዝርዝር በሌላ ፅሁፍ የምንመለስበት ሲሆን፣ በዚህ ክፍል የአዋጁን ዋናዋና ድንጋጌዎች በተለይም ከዓላማዉ ጋር በማገናኘት ለማየት እንሞክራለን፡፡
1. የዲጂታል መታወቂያ ምንነት እና አገልግሎት
በየትኛውም ሀገር የሚገኝ የመታወቂያ ሥርዓት በሁለት የሚከፈል ሲሆን እነሱም አገልግሎት ተኮር መታወቂያ (Functional ID) እና መሰረታዊ መታወቂያ (Foundational ID) ናቸው፡፡ አገልግሎት ተኮር የመታወቂያ (Functional ID) ማለት የተወሰነ አገልግሎት ለማግኘት የሚያስችል መታወቂያ ነው። እንዲህ አይነት መታወቂያ፣ ከተሰጠበት አገልግሎት ውጭ ለሌሎች ነዋሪነትን እና ማንነትን በማረጋገጥ ለሚሰጡ አገልግሎቶች ተቀባይነት ላይኖራቸው ይችላል፡፡ መሰረታዊ መታወቂያ (Foundational ID) ማለት በተሰጠበት ሀገር ውስጥ በየትኛውም ቦታ ተቀባይነት ያለው እና ማንነትን በማረጋገጥ ለሚሰጡ የትኛውም አገልግሎቶች ተቀባይነት ያለው የመታወቂያ አይነት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ መሰረታዊ መታወቂያ (Foundational ID) ለአገልግሎት ተኮር መታወቂያዎች (Functional ID) እንደመረጃ ምንጭ ሆኖ ያገለግላል፡፡
መሰረታዊ መታወቂያ በተለያዩ ሀገራት የተለያዩ ስያሜዎች ሊኖሩት የሚችሉ ሲሆን ብሄራዊ መታወቂያ ወይም የዲጂታል መታወቂያ በብዛት መሰረታዊ መታወቂያ የሚጠራባቸው ስያሜዎች ናቸው፡፡
በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት ተግባራዊ ለማድረግ በሙከራ ላይ የሚገኘው የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት (Foundational ID) መሰረታዊ መታወቂያ የሚሰጥበት ስርዓት ነው፡፡ የዲጂታል መታወቂ ማለት ማንኛውም በሀገሪቱ ውስጥ የሚኖር ሰው ተቋሙ ወይም በተቋሙ ውክልና የተሰጠው አካል በሚያደርገው የምዝገባ ሂደት የባዮሜትሪክ እና ዲሞግራፊክ መረጃዎችን በመስጠት ከተመዘገበ በኋላ ማንነቱን ለማረጋገጥ የሚሰጥ ልዩ ቁጥር(Unique Number) ነው፡፡ ይህ ልዩ ቁጥር ወይም ዲጂታል መታወቂ የሚመነጨው ከግለሰቡ የባዮሜትሪክ እና ዲሞግራፊክ ዳታ በመሆኑ፣ ግለሰብን በልዩ ሁኔታ ለመለየት የሚስያስችል አስተማማኝ የመታወቂ ስርዓት ነው፡፡
ይህን የመታወቂያ ስርዓት ተግባራዊ ለማድረግ እና የህግ ድጋፍ እንዲኖረው ለማስቻል በብሄራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ፅ/ቤት የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ከተዘጋጀ በኋላ ረቂቁን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አዋጅ ቁጥር 1284/2015 አድርጎ አፅድቆታል፡፡ በአዋጁ አንቀፅ 14 ላይ በግልፅ እንደተመለከተው የዲጂታል መታወቂያ የአንድን ነዋሪ ማንነትን ለማስረዳት ወይም ለማረጋገጥ እንደ ህጋዊ እና በቂ ማስረጃ ተደርጎ እንደሚወሰድ እና ማንኛውም ተጠቃሚ አካል ለነዋሪው ለሚሰጠው አገልግሎት የዲጂታል መታወቂያ እንደ አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታ የሚያደርግ አሠራር በሚመለከተው ተቆጣጣሪ አካል ፍቃድ መዘርጋት እንዳለበት ተደንግጓል፡፡ ስለሆነም አሁን በኢትዮጵያ ተግባራዊ የሚደረገው ዲጂታል መታወቂያ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ተቀባይነት ያለው እና ማንነትን በማረጋገጥ ለሚሰጡ አገልግሎቶች እንደ አስገዳጅ የመታወቂያ አይነት የሚወሰድ ሲሆን፣ በዚህ መታወቂያ አገልግሎት ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆነ ማንኛውም ሰው በወንጀል እንደሚጠየቅ አዋጁ አንቀፅ 21/1/ በሚከተለው መልኩ ደንግጓል፡፡
"በዚህ አዋጅ እና ይህን አዋጅ ተከትለው በሚወጡ ደንቦች እና መመሪያዎች መሠረት ስልጣን ባለው አካል የተሰጠን ዲጂታል መታወቂያን እንደ ህጋዊ መታወቂያ ለመቀበል ፈቃደኛ ያልሆነ ወይም ማንነትን ብቻ በማረጋገጥ የሚሰጡ አገልግሎቶችን በዲጂታል መታወቂያ ለመስጠት ፍቃደኛ ያልሆነ ወይም በዚህ አዋጅ አንቀፀ 19 ላይ የተመለከተውን የመተባበር ግዴታ የተላለፈ ማንኛውም ሰው ከአስር ሺህ እስከ አንድ መቶ ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል"
ከላይ እንደተገለጸው ዲጂታል መታወቂያ የሚባሉው ልዩ ቁጥሩ ሲሆን፣ ይህንን መታወቂያ በካርድ መልኩ መያዝ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ተገቢውም ክፍያ በመፈፀም ከተቋሙ ወይም ተቋሙ ውክልና ከሰጠው ማንኛውም አታሚ ድርጅት የመታወቂያ ካርዱን ማግኘት የሚቻልበት ስርዓት ተዘርግቷል፡፡
2. የአዋጁ ዓላማ
የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ቁጥር 1284/2015 ዋና ዓላማው የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት መዘርጋት ነው፡፡ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ምንድን ነው የሚለው ሰፊ ትንታኔ የሚፈልግ ሲሆን፣ ጠቅላላ የሆነ ትርጓሜውን ግን ከዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ዓላማ ከሚለው ድንጋጌ መገንዘብ ይቻላል፡፡ በመሆኑም በአዋጁ አንቀፅ 5 ላይ እንደተመለከተው የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ዓላማ ነዋሪዎች በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ሲንቀሳቀሱ በቀላሉ የመታወቅ መብታቸው እንዲረጋገጥ በማድረግ ለሰብአዊ መብቶቸ አከባበር እና ለመልካም አስተዳደር መሻሻል አስተዋፅኦ ማድረግ፣ አገልግሎት ማግኘት የሚፈልጉ ግለሰቦችን በቀላሉ ለመለየት የሚያስችል የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት በመዘርጋት በአገልግሎት ሰጪ እና አገልግሎት ተቀባይ መካከል እምነት እንዲጎለብት ማድረግ፣ ሕገ-ወጥ ተግባራትን መከላከል፣ ሀገር አቀፍ የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት በማደራጀት ሀገራዊ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎች እና እቅዶች ሲቀረጹ እና የልማት ሥራዎች ሲከናወኑ ድግግሞሽን መቅረፍ፣ በዚህም የሀብት ብክነትን መቀነስ እና አካታችነትን ማጎልበት፣ የነዋሪዎችን የዲሞግራፊክ እና ባዮሜትሪክ መረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችል ሥርዓት በመዘርጋት፣ ለሌሎች መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ አካላት የመታወቂያ ሥርዓት መረጃ ምንጭ ሆኖ ማገልገል እና አገልግሎት ተኮር የሆኑ የመታወቂያ ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት እንዲሸጋገሩ ማጠናከር መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
3. የዲጂታል መታወቂያ የማግኘት መብት እና ዲጂታል መታወቂያ ለማግኘት ስለሚሰበሰቡ መረጃዎች
ዘመናዊ የመታወቂያ ስርዓት በአንድ ሀገር ውስጥ ተግባራዊ ሲደረግ መሰረታዊ የሚባሉ ጠቀሜታዎች ያሉት ሲሆን፣ ከነዚህ ጠቀሜታዎች መካከልም ሃገራዊ ልማትን በአግባቡ ለማቀድ፣ ምጣኔ ሃብታዊ ሽግግር ለመፍጠር፣ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን፣ የሀብት ብክነትን ለመቀነስ፣ ወንጀልን ለመከላከል፣ ፖሊሲዎች ሲቀረጹ እና የልማት ሥራዎች ሲከናወኑ ድግግሞሽን ለመቅረፍ እና አካታችነትን ለማጎልበት የሚረዳ መሆኑ የተረጋገጠ ነው፡፡ በኢትዮጵያም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የበለፀገ፣ ዘርፍ ተሻጋሪ፣ መሠረታዊ የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት መዘርጋት አሰፈላጊ መሆኑ ታምኖበት የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት ተቋቁሞ ላለፉት ሁለት ዓመታት በግንባታና በሙከራ ሂደት ላይ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ ከተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች ጋር ለማስተሳሰር የሙከራ ትግበራ ስራዎችን በማከናወን ወደ 1.4 ሚሊዮን የሚጠጉ ነዋሪዎችን መዝግቦ አብዛኞቹን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ ተችሏል።
በዚህ የሙከራ ትግበራ ወቅት ከተከናወኑ ተግባራት ውስጥ ሌላው የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ማዘጋጀት ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ "የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ቁጥር 1284/2015" አድርጎ አፅድቆታል፡፡ አዋጁ ከሌሎች ሀገሮች የመታወቂያ አዋጆች አንፃር ዘግየት ብሎ የወጣ በመሆኑ በሌሎች ሀገሮች የታዩ ክፍተቶችን ለመድፈን በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ዘመኑ የደረሰበትን የዲጂታል መታወቂያ በዘመናዊ መልኩ ለነዋሪዎች ለመስጠት እና ለማስተዳደር በማለም የወጣ ነው፡፡ አዋጁ በርካታ ጉዳዮችን የያዘ ሲሆን፣ በዝርዝር በሌላ ፅሁፍ የምንመለስበት ሲሆን፣ በዚህ ክፍል የአዋጁን ዋናዋና ድንጋጌዎች በተለይም ከዓላማዉ ጋር በማገናኘት ለማየት እንሞክራለን፡፡
1. የዲጂታል መታወቂያ ምንነት እና አገልግሎት
በየትኛውም ሀገር የሚገኝ የመታወቂያ ሥርዓት በሁለት የሚከፈል ሲሆን እነሱም አገልግሎት ተኮር መታወቂያ (Functional ID) እና መሰረታዊ መታወቂያ (Foundational ID) ናቸው፡፡ አገልግሎት ተኮር የመታወቂያ (Functional ID) ማለት የተወሰነ አገልግሎት ለማግኘት የሚያስችል መታወቂያ ነው። እንዲህ አይነት መታወቂያ፣ ከተሰጠበት አገልግሎት ውጭ ለሌሎች ነዋሪነትን እና ማንነትን በማረጋገጥ ለሚሰጡ አገልግሎቶች ተቀባይነት ላይኖራቸው ይችላል፡፡ መሰረታዊ መታወቂያ (Foundational ID) ማለት በተሰጠበት ሀገር ውስጥ በየትኛውም ቦታ ተቀባይነት ያለው እና ማንነትን በማረጋገጥ ለሚሰጡ የትኛውም አገልግሎቶች ተቀባይነት ያለው የመታወቂያ አይነት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ መሰረታዊ መታወቂያ (Foundational ID) ለአገልግሎት ተኮር መታወቂያዎች (Functional ID) እንደመረጃ ምንጭ ሆኖ ያገለግላል፡፡
መሰረታዊ መታወቂያ በተለያዩ ሀገራት የተለያዩ ስያሜዎች ሊኖሩት የሚችሉ ሲሆን ብሄራዊ መታወቂያ ወይም የዲጂታል መታወቂያ በብዛት መሰረታዊ መታወቂያ የሚጠራባቸው ስያሜዎች ናቸው፡፡
በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት ተግባራዊ ለማድረግ በሙከራ ላይ የሚገኘው የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት (Foundational ID) መሰረታዊ መታወቂያ የሚሰጥበት ስርዓት ነው፡፡ የዲጂታል መታወቂ ማለት ማንኛውም በሀገሪቱ ውስጥ የሚኖር ሰው ተቋሙ ወይም በተቋሙ ውክልና የተሰጠው አካል በሚያደርገው የምዝገባ ሂደት የባዮሜትሪክ እና ዲሞግራፊክ መረጃዎችን በመስጠት ከተመዘገበ በኋላ ማንነቱን ለማረጋገጥ የሚሰጥ ልዩ ቁጥር(Unique Number) ነው፡፡ ይህ ልዩ ቁጥር ወይም ዲጂታል መታወቂ የሚመነጨው ከግለሰቡ የባዮሜትሪክ እና ዲሞግራፊክ ዳታ በመሆኑ፣ ግለሰብን በልዩ ሁኔታ ለመለየት የሚስያስችል አስተማማኝ የመታወቂ ስርዓት ነው፡፡
ይህን የመታወቂያ ስርዓት ተግባራዊ ለማድረግ እና የህግ ድጋፍ እንዲኖረው ለማስቻል በብሄራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ፅ/ቤት የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ከተዘጋጀ በኋላ ረቂቁን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አዋጅ ቁጥር 1284/2015 አድርጎ አፅድቆታል፡፡ በአዋጁ አንቀፅ 14 ላይ በግልፅ እንደተመለከተው የዲጂታል መታወቂያ የአንድን ነዋሪ ማንነትን ለማስረዳት ወይም ለማረጋገጥ እንደ ህጋዊ እና በቂ ማስረጃ ተደርጎ እንደሚወሰድ እና ማንኛውም ተጠቃሚ አካል ለነዋሪው ለሚሰጠው አገልግሎት የዲጂታል መታወቂያ እንደ አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታ የሚያደርግ አሠራር በሚመለከተው ተቆጣጣሪ አካል ፍቃድ መዘርጋት እንዳለበት ተደንግጓል፡፡ ስለሆነም አሁን በኢትዮጵያ ተግባራዊ የሚደረገው ዲጂታል መታወቂያ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ተቀባይነት ያለው እና ማንነትን በማረጋገጥ ለሚሰጡ አገልግሎቶች እንደ አስገዳጅ የመታወቂያ አይነት የሚወሰድ ሲሆን፣ በዚህ መታወቂያ አገልግሎት ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆነ ማንኛውም ሰው በወንጀል እንደሚጠየቅ አዋጁ አንቀፅ 21/1/ በሚከተለው መልኩ ደንግጓል፡፡
"በዚህ አዋጅ እና ይህን አዋጅ ተከትለው በሚወጡ ደንቦች እና መመሪያዎች መሠረት ስልጣን ባለው አካል የተሰጠን ዲጂታል መታወቂያን እንደ ህጋዊ መታወቂያ ለመቀበል ፈቃደኛ ያልሆነ ወይም ማንነትን ብቻ በማረጋገጥ የሚሰጡ አገልግሎቶችን በዲጂታል መታወቂያ ለመስጠት ፍቃደኛ ያልሆነ ወይም በዚህ አዋጅ አንቀፀ 19 ላይ የተመለከተውን የመተባበር ግዴታ የተላለፈ ማንኛውም ሰው ከአስር ሺህ እስከ አንድ መቶ ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል"
ከላይ እንደተገለጸው ዲጂታል መታወቂያ የሚባሉው ልዩ ቁጥሩ ሲሆን፣ ይህንን መታወቂያ በካርድ መልኩ መያዝ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ተገቢውም ክፍያ በመፈፀም ከተቋሙ ወይም ተቋሙ ውክልና ከሰጠው ማንኛውም አታሚ ድርጅት የመታወቂያ ካርዱን ማግኘት የሚቻልበት ስርዓት ተዘርግቷል፡፡
2. የአዋጁ ዓላማ
የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ቁጥር 1284/2015 ዋና ዓላማው የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት መዘርጋት ነው፡፡ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ምንድን ነው የሚለው ሰፊ ትንታኔ የሚፈልግ ሲሆን፣ ጠቅላላ የሆነ ትርጓሜውን ግን ከዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ዓላማ ከሚለው ድንጋጌ መገንዘብ ይቻላል፡፡ በመሆኑም በአዋጁ አንቀፅ 5 ላይ እንደተመለከተው የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ዓላማ ነዋሪዎች በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ሲንቀሳቀሱ በቀላሉ የመታወቅ መብታቸው እንዲረጋገጥ በማድረግ ለሰብአዊ መብቶቸ አከባበር እና ለመልካም አስተዳደር መሻሻል አስተዋፅኦ ማድረግ፣ አገልግሎት ማግኘት የሚፈልጉ ግለሰቦችን በቀላሉ ለመለየት የሚያስችል የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት በመዘርጋት በአገልግሎት ሰጪ እና አገልግሎት ተቀባይ መካከል እምነት እንዲጎለብት ማድረግ፣ ሕገ-ወጥ ተግባራትን መከላከል፣ ሀገር አቀፍ የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት በማደራጀት ሀገራዊ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎች እና እቅዶች ሲቀረጹ እና የልማት ሥራዎች ሲከናወኑ ድግግሞሽን መቅረፍ፣ በዚህም የሀብት ብክነትን መቀነስ እና አካታችነትን ማጎልበት፣ የነዋሪዎችን የዲሞግራፊክ እና ባዮሜትሪክ መረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችል ሥርዓት በመዘርጋት፣ ለሌሎች መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ አካላት የመታወቂያ ሥርዓት መረጃ ምንጭ ሆኖ ማገልገል እና አገልግሎት ተኮር የሆኑ የመታወቂያ ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት እንዲሸጋገሩ ማጠናከር መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
3. የዲጂታል መታወቂያ የማግኘት መብት እና ዲጂታል መታወቂያ ለማግኘት ስለሚሰበሰቡ መረጃዎች
በአዋጁ አንቀፅ 7 ላይ በግልፅ እንደተመለከተው ማንኛውም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖር ሰው የባዮሜትሪክ እና ዲሞግራፊክ መረጃዎችን በመስጠትና በመመዝገብ የዲጂታል መታወቂያ የማግኘት መብት አለው፡፡ ነዋሪው የዲጂታል መታወቂያ ለመውሰድ እሱነቱን ለማረጋገጥ የሚያገለግሉ የመታወቂያ ሰነዶች እና ሌሎች በተቋሙ ተቀባይነት ያላቸውን ሰነዶች ወይም የሰው ምስክር ማስረጃዎችን በመጠቀም በማረጋገጥ መመዝገብ ይችላል፡፡ ከላይ እንደተመለከተው ወደ ዲጂታል መታወቂያ ስርዓት የሚገባ የግል መረጃ የእያንዳንዱን ተመዝጋቢ የዲሞግራፊክ መረጃ እና ባዮሜትሪክ መረጃን ያካተተ መሆን ያለበት ሲሆን፣ የዲሞግራክ መረጃ የሚባሉትም ስም ፣ የአባት ስም ፣ የአያት ስም ፣ ወይም በዚህ መልክ የተደራጀ ህጋዊ ስም ለሌለው ተመዝጋቢ ተቋሙ ህጋዊ የሆነውን ስያሜ ወይም ተመዝጋቢው በአካባቢው ማህበረሰብ የሚጠራበትን ስም፣ ዜግነት፣ የትውልድ ቀን፣ ወር እና ዓመት፣ ፆታ፣ መኖሪያ አድራሻ ሲሆኑ እንደአስፈላጊነቱ ስልክ ቁጥር፣ የኢሜይል አድራሻ እና ፖስታ አድራሻንም ሊያካትት ይችላል፡፡ የሚሰበሰቡት የባዮሜትሪክ መረጃዎች ድግሞ የአስር ጣት አሻራ፣ የሁለቱም አይኖች ብሌን እና የፊት ገፅታ ናቸው፡፡ እነዚህን የባዮሜትሪክ እና ዲሞግራፊክ መረጃዎች የሰጠ ማንኛውም ሰው የዲጂታል መታወቂያ ማግኘት ይችላል፡፡
አንዳንድ ጊዜ የባዮሜትሪክ መረጃዎችን ለመስጠት የሚቸገሩ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ ጣት የሌለው ሰው፣ በእርጅና እና በተለያዩ ምክንያቶች አሻራቸው የማይነበብ ሰዎች በሚኖሩበት ጊዜ እና መሰል ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ፣ በዲሞግራፊክ መረጃ ብቻ መታወቂያውን መስጠት የሚገባ ስለመሆኑ በአዋጁ ተደንግጓል፡፡
4. የዲጂታል መታወቂያ ከሌሎች መታወቂያዎች፣
የባንክ አካውንቶች እና መሰል ማንነትን ለማረጋገጥ ከሚያገለግሉ ሰነዶች ጋር የሚኖረው ግንኙነት
የዲጂታል መታወቂያ ራሱን የቻለ መታወቂያ ቢሆንም፣ ሌሎች መታወቂያዎችን የሚያጠናክር የመታወቂያ አይነት ነው፡፡ ሁሉም ከላይ በርዕሱ ላይ የተመለከቱን ማንነትን ለማረጋገጥ የሚያገለግሉ ሰነዶች ወደ ዲጂታል መታወቂያ ስርዓት እንዲገቡ የሚደርግ አሰራር ተዘርግቷል፡፡ ለምሳሌ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤቱ ከብሄራዊ ባንክ ጋር በመተባበር ከሁሉም በሀገሪቱ ውስጥ ከሚገኙ ባንኮች ጋር ስምምነት ላይ በመድረስ፣ ሁሉም ባንኮች ደንበኞቻቸውን ወደ ዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ለማስገባት ስራ ጀምረዋል፡፡ እንዲሁም ፅህፈት ቤቱ እና ገቢዎች ሚኒስቴር የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረም ሁሉንም ግብር ከፋይ የታክስ ከፋይነት መለያ ቁጥሩን መሰረት በማድረግ ወደ ዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ለማስገባት የሚስችል ስራ ተጀምሯል፡፡ ከዚህ መገንዘብ የምንችለው የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ሌሎች መታወቂያ ስርዓቶችን እያጠናከረ የሚሄድ የመታወቂያ አይነት መሆኑን እና ራሱንም ችሎ ማናቸውንም አገልግሎት ለማግኘት የሚያስችል የመታወቂያ አይነት መሆኑን ነው፡፡
5. የመረጃ አጠባበቅ ስርዓት
የዲጂታል መታወቂያ ለማግኘት የሚሰበሰቡ መረጃዎች በተለይም የባዮሜትሪክ መረጃዎች በጥንቃቄ ካልተያዙ ለተለያዩ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ሊያጋልጡ ይችላሉ፡ ስለዚህ ለዲጂታል መታወቂያ የተሰበሰቡ መረጃዎች በጥንቃቄ መያዝ ያለባቸው በመሆኑ አዋጁ ተቋሙ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት የግል መረጃን በአስተማማኝነት የሚይዝ ጠንካራ የመረጃ አስተዳደር ስርዓት መዘርጋት አለበት፤ በሚል የደነገገ ሲሆን፣ አሰራርና ህግን ጠብቆ በዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ለተሰበሰበ የማንኛውም ተመዝጋቢ ግላዊ መረጃ ያለ ተመዝጋቢው ፈቃድ ለሌላ ሰው መግለጽ ፣ ማስተላለፍም ሆነ እንዲለወጥ መፍቀድ የተከለከለ መሆኑን ህጉ በግልፅ አስቀምጧል፡፡ ይህን ክልከላ መተላለፍም በወንጀል የሚስጠይቅ ስለመሆኑ በአዋጁ አንቀጥፅ 25 ላይ ተደንግጓል፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ለፍትህ ስራ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ በህግ ስልጣን ለተሰጠው ወይም በፍርድ ቤት ትዕዛዝ መሠረት የግል መረጃው ለሚመለከተው ህጋዊ አካል ሊገለጽ ወይም ሊተላለፍ እንደሚችል የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ቁጥር 1284/2015 አንቀፅ 16 ተደንግጓል፡፡
በንቃተ ህግ፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
አንዳንድ ጊዜ የባዮሜትሪክ መረጃዎችን ለመስጠት የሚቸገሩ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ ጣት የሌለው ሰው፣ በእርጅና እና በተለያዩ ምክንያቶች አሻራቸው የማይነበብ ሰዎች በሚኖሩበት ጊዜ እና መሰል ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ፣ በዲሞግራፊክ መረጃ ብቻ መታወቂያውን መስጠት የሚገባ ስለመሆኑ በአዋጁ ተደንግጓል፡፡
4. የዲጂታል መታወቂያ ከሌሎች መታወቂያዎች፣
የባንክ አካውንቶች እና መሰል ማንነትን ለማረጋገጥ ከሚያገለግሉ ሰነዶች ጋር የሚኖረው ግንኙነት
የዲጂታል መታወቂያ ራሱን የቻለ መታወቂያ ቢሆንም፣ ሌሎች መታወቂያዎችን የሚያጠናክር የመታወቂያ አይነት ነው፡፡ ሁሉም ከላይ በርዕሱ ላይ የተመለከቱን ማንነትን ለማረጋገጥ የሚያገለግሉ ሰነዶች ወደ ዲጂታል መታወቂያ ስርዓት እንዲገቡ የሚደርግ አሰራር ተዘርግቷል፡፡ ለምሳሌ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤቱ ከብሄራዊ ባንክ ጋር በመተባበር ከሁሉም በሀገሪቱ ውስጥ ከሚገኙ ባንኮች ጋር ስምምነት ላይ በመድረስ፣ ሁሉም ባንኮች ደንበኞቻቸውን ወደ ዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ለማስገባት ስራ ጀምረዋል፡፡ እንዲሁም ፅህፈት ቤቱ እና ገቢዎች ሚኒስቴር የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረም ሁሉንም ግብር ከፋይ የታክስ ከፋይነት መለያ ቁጥሩን መሰረት በማድረግ ወደ ዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ለማስገባት የሚስችል ስራ ተጀምሯል፡፡ ከዚህ መገንዘብ የምንችለው የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ሌሎች መታወቂያ ስርዓቶችን እያጠናከረ የሚሄድ የመታወቂያ አይነት መሆኑን እና ራሱንም ችሎ ማናቸውንም አገልግሎት ለማግኘት የሚያስችል የመታወቂያ አይነት መሆኑን ነው፡፡
5. የመረጃ አጠባበቅ ስርዓት
የዲጂታል መታወቂያ ለማግኘት የሚሰበሰቡ መረጃዎች በተለይም የባዮሜትሪክ መረጃዎች በጥንቃቄ ካልተያዙ ለተለያዩ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ሊያጋልጡ ይችላሉ፡ ስለዚህ ለዲጂታል መታወቂያ የተሰበሰቡ መረጃዎች በጥንቃቄ መያዝ ያለባቸው በመሆኑ አዋጁ ተቋሙ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት የግል መረጃን በአስተማማኝነት የሚይዝ ጠንካራ የመረጃ አስተዳደር ስርዓት መዘርጋት አለበት፤ በሚል የደነገገ ሲሆን፣ አሰራርና ህግን ጠብቆ በዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ለተሰበሰበ የማንኛውም ተመዝጋቢ ግላዊ መረጃ ያለ ተመዝጋቢው ፈቃድ ለሌላ ሰው መግለጽ ፣ ማስተላለፍም ሆነ እንዲለወጥ መፍቀድ የተከለከለ መሆኑን ህጉ በግልፅ አስቀምጧል፡፡ ይህን ክልከላ መተላለፍም በወንጀል የሚስጠይቅ ስለመሆኑ በአዋጁ አንቀጥፅ 25 ላይ ተደንግጓል፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ለፍትህ ስራ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ በህግ ስልጣን ለተሰጠው ወይም በፍርድ ቤት ትዕዛዝ መሠረት የግል መረጃው ለሚመለከተው ህጋዊ አካል ሊገለጽ ወይም ሊተላለፍ እንደሚችል የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ቁጥር 1284/2015 አንቀፅ 16 ተደንግጓል፡፡
በንቃተ ህግ፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የደምዳሚ (ድምዳሜ) ማስረጃ /conclusive evidence/ 5 የሰበር ችሎት ትርጓሜዎች
1//// የተሟላና ሙሉ ዕምነት የሚጣልበት ማስረጃ
የልዩ አዋቂ /expert/ የሚደርስበት የመጨረሻ አስተያየት ከሚኖረው ሙያዊ ዕውቀት አድማስ፣ ከሚታገዝበት መሣሪያና ከመሳሰሉት ጋር የተሟላና ሙሉ ዕምነት የሚጣልበት ማስረጃ /conclusive evidence/ ሊሆን ስለማይችል በዓይን ምስክሮች የተነገረን ፍሬ ነገር ለማስተባበል የሚያበቃ አቅም አይኖረውም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 43453 ቅጽ 12
የትራፊክ ፖሊስ የአደጋ ፕላን ሪፖርት የባለሙያ ሙያዊ አስተያየትን በወረቀት ላይ ስዕላዊ በሆነ መንገድ የሚያስቀምጥ በባለሙያ የሚረጋገጥ ሰነድ በመሆኑ እንደ ማንኛውም የልዩ አዋቂ የምስክርነት ቃል በተገቢው መንገድ ሊመዘን የሚገባው የማስረጃ አይነት እንጅ ሁልጊዜ ድምዳሜ ማስረጃ (Conclusive Evidence) ያለመሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 92141 ቅጽ 17
2//// አሳሪ ማስረጃ
በአስተዳደር አካል የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ነው ተብሎ የምስክር ወረቀት መስጠት ማስረጃውን ደምዳሚ ወይም አሳሪ (Conclusive Evidence) የሚያደርገው አይደለም፡፡ ይልቁንም ይኸው ማስረጃ የተሰጠበት አግባብ በፍ/ህ/ህ/ቁ. 1195 ድንጋጌ ስር በተመለከቱት ሁኔታዎች መሰረት ስለመሆኑ ማስረዳት ከተቻለ በፍ/ህ/ቁ. 1195 ስር የተመለከተው ሕጋዊ ግምት ሊስተባበል የሚችል (rebuttable legal presumption) መሆኑን ከድንጋጌዎቹ ይዘትና መንፈስ የምንገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 64014 ቅጽ 13
3//// ማስተባበያ ሊቀርብበት የማይችል ወሳኝ ማስረጃ
አንድ ለማይንቀሳቀስ ንብረት የተሰጠ የባለሃብትነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ባለሃብትነትን በተመለከተ የህግ ግምት የሚያሰጥ ቢሆንም በሌላ ተቃራኒ ማስረጃ ሊስተባበል፣ በተቃራኒው ከሚቀርቡት ማስረጃዎች ጋር ሊመዘን የሚችል እንጂ እንጅ ማስተባበያ ሊቀርብበት የማይችል ወሳኝ /conclusive evidence/ ያለመሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 67011 ቅጽ 13
4//// የመጨረሻ ማስረጃ
የልጅነት ሁኔታ መኖሩን ማስረዳት ከተቻለ ፍ/ቤት ልጅ ነው ሲል የሕግ ግምት ሊወስድ የሚችል መሆኑን የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 157/1/ ያመለክታል፡፡ ከአንቀፁ መረዳት እንደሚቻለው የልጅነት ሁኔታ መኖሩን ማረጋገጥ የመጨረሻ ማስረጃ (conclusive evidence) ሳይሆን የሕግ ግምት ብቻ ነው፡፡ ግምቱም ቢሆን አስገዳጅነት ያለው የሕግ ግምት አይደለም፡፡ ግምቱን የሚቃወም ወገን ማስረጃ በማቅረብ ማፍረስ እንደሚችል ንዑስ አንቀፅ 2 ይደነግጋል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 42648 ቅጽ 10
5///// ክርክር ሊነሳበት የማይችል፣ ሙሉ እምነት ሊጣልበት የሚችል ማስረጃ
ልጅነት የሚረጋገጥበት ዋናው ማስረጃ የልደት ምስክር ወረቀት እንደሆነ በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ በአንቀጽ 154 ላይ ተመልክቷል፡፡ ይህ ማለት ግን የልደት ምስክር ወረቀት ክርክር ሊነሳበት የማይችል ሙሉ እምነት ሊጣልበት የሚችል /Conclusive/ ማስረጃ ነው ማለት ግን አይደለም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 33440 ቅጽ 5
1//// የተሟላና ሙሉ ዕምነት የሚጣልበት ማስረጃ
የልዩ አዋቂ /expert/ የሚደርስበት የመጨረሻ አስተያየት ከሚኖረው ሙያዊ ዕውቀት አድማስ፣ ከሚታገዝበት መሣሪያና ከመሳሰሉት ጋር የተሟላና ሙሉ ዕምነት የሚጣልበት ማስረጃ /conclusive evidence/ ሊሆን ስለማይችል በዓይን ምስክሮች የተነገረን ፍሬ ነገር ለማስተባበል የሚያበቃ አቅም አይኖረውም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 43453 ቅጽ 12
የትራፊክ ፖሊስ የአደጋ ፕላን ሪፖርት የባለሙያ ሙያዊ አስተያየትን በወረቀት ላይ ስዕላዊ በሆነ መንገድ የሚያስቀምጥ በባለሙያ የሚረጋገጥ ሰነድ በመሆኑ እንደ ማንኛውም የልዩ አዋቂ የምስክርነት ቃል በተገቢው መንገድ ሊመዘን የሚገባው የማስረጃ አይነት እንጅ ሁልጊዜ ድምዳሜ ማስረጃ (Conclusive Evidence) ያለመሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 92141 ቅጽ 17
2//// አሳሪ ማስረጃ
በአስተዳደር አካል የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ነው ተብሎ የምስክር ወረቀት መስጠት ማስረጃውን ደምዳሚ ወይም አሳሪ (Conclusive Evidence) የሚያደርገው አይደለም፡፡ ይልቁንም ይኸው ማስረጃ የተሰጠበት አግባብ በፍ/ህ/ህ/ቁ. 1195 ድንጋጌ ስር በተመለከቱት ሁኔታዎች መሰረት ስለመሆኑ ማስረዳት ከተቻለ በፍ/ህ/ቁ. 1195 ስር የተመለከተው ሕጋዊ ግምት ሊስተባበል የሚችል (rebuttable legal presumption) መሆኑን ከድንጋጌዎቹ ይዘትና መንፈስ የምንገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 64014 ቅጽ 13
3//// ማስተባበያ ሊቀርብበት የማይችል ወሳኝ ማስረጃ
አንድ ለማይንቀሳቀስ ንብረት የተሰጠ የባለሃብትነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ባለሃብትነትን በተመለከተ የህግ ግምት የሚያሰጥ ቢሆንም በሌላ ተቃራኒ ማስረጃ ሊስተባበል፣ በተቃራኒው ከሚቀርቡት ማስረጃዎች ጋር ሊመዘን የሚችል እንጂ እንጅ ማስተባበያ ሊቀርብበት የማይችል ወሳኝ /conclusive evidence/ ያለመሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 67011 ቅጽ 13
4//// የመጨረሻ ማስረጃ
የልጅነት ሁኔታ መኖሩን ማስረዳት ከተቻለ ፍ/ቤት ልጅ ነው ሲል የሕግ ግምት ሊወስድ የሚችል መሆኑን የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 157/1/ ያመለክታል፡፡ ከአንቀፁ መረዳት እንደሚቻለው የልጅነት ሁኔታ መኖሩን ማረጋገጥ የመጨረሻ ማስረጃ (conclusive evidence) ሳይሆን የሕግ ግምት ብቻ ነው፡፡ ግምቱም ቢሆን አስገዳጅነት ያለው የሕግ ግምት አይደለም፡፡ ግምቱን የሚቃወም ወገን ማስረጃ በማቅረብ ማፍረስ እንደሚችል ንዑስ አንቀፅ 2 ይደነግጋል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 42648 ቅጽ 10
5///// ክርክር ሊነሳበት የማይችል፣ ሙሉ እምነት ሊጣልበት የሚችል ማስረጃ
ልጅነት የሚረጋገጥበት ዋናው ማስረጃ የልደት ምስክር ወረቀት እንደሆነ በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ በአንቀጽ 154 ላይ ተመልክቷል፡፡ ይህ ማለት ግን የልደት ምስክር ወረቀት ክርክር ሊነሳበት የማይችል ሙሉ እምነት ሊጣልበት የሚችል /Conclusive/ ማስረጃ ነው ማለት ግን አይደለም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 33440 ቅጽ 5
Federal Judges Code of Conduct and Disciplinary Procedure Regulation
Regulation Number 1/2013
link: bit.ly/40yp2Jy
📌📌Note
: This translation was undertaken by volunteer Year III students of Addis Ababa University School of Law for the benefit of fellow students who are not native Amharic speakers.
Regulation Number 1/2013
link: bit.ly/40yp2Jy
📌📌Note
: This translation was undertaken by volunteer Year III students of Addis Ababa University School of Law for the benefit of fellow students who are not native Amharic speakers.
www.academia.edu
Federal Judges Code of Conduct and
Disciplinary Procedure Regulation reg. No. 1/2013
Disciplinary Procedure Regulation reg. No. 1/2013
Note also that only substantive parts of the Code are included in this document, and the students have considered the ongoing translation being undertaken by the Federal Supreme Court.