የወሊድ ፈቃድ
1/ ነፍሰጡር የሆነች ሠራተኛ ከእርግዝናዋ ጋር የተያያዘ ምርመራ ለማድረግ አሠሪው ከደመወዝ ጋር ፈቃድ ይሰጣታል፤ ሆኖም ሠራተኛዋ ከምርመራ በኋላ የሐኪም ማስረጃ ማቅረብ አለባት፡፡
2/ ነፍሰጡር የሆነች ሠራተኛ ከመውለዷ በፊት ሐኪም እንድታርፍ ካዘዘ አሠሪው ከክፍያ ጋር እረፍት ይሰጣታል፡፡ ሕግ አገልግሎት
3/ ነፍሰጡር የሆነች ሠራተኛ እወልዳለሁ ብላ ከገመተችበት ቀን በፊት የ 30 (ሰላሳ) ተከታታይ ቀናት የቅድመ-ወሊድ ፈቃድ ፣ እንዲሁም ስትወልድ ከወለደችበት ቀን ጀምሮ ለ 90 (ዘጠና) ተከታታይ ቀናት የድህረ-ወሊድ ፈቃድ ከክፍያ ጋር ይሰጣታል፡፡
4, ሠራተኛዋ ከመውለዷ በፊት የወሰደችው የ 30 (ሰላሳ) የሥራ ቀናት የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ሲያልቅ ካልወለደች እስከምትወልድበት ቀን ድረስ ከላይ በቁጥር ሁለት ስር በተመለከተው መሠረት እረፍት ልታገኝ ትችላለች፡፡ የ 30 (ሰላሳ) የሥራ ቀናት
የቅድመ-ወሊድ ፈቃዷ ሳያልቅ ከወለደች 90 (ዘጠና) የሥራ ቀናት የድህረ-ወሊድ ፈቃዷ ይጀምራል፡፡
የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀፅ 88
https://t.me/lawsocieties
1/ ነፍሰጡር የሆነች ሠራተኛ ከእርግዝናዋ ጋር የተያያዘ ምርመራ ለማድረግ አሠሪው ከደመወዝ ጋር ፈቃድ ይሰጣታል፤ ሆኖም ሠራተኛዋ ከምርመራ በኋላ የሐኪም ማስረጃ ማቅረብ አለባት፡፡
2/ ነፍሰጡር የሆነች ሠራተኛ ከመውለዷ በፊት ሐኪም እንድታርፍ ካዘዘ አሠሪው ከክፍያ ጋር እረፍት ይሰጣታል፡፡ ሕግ አገልግሎት
3/ ነፍሰጡር የሆነች ሠራተኛ እወልዳለሁ ብላ ከገመተችበት ቀን በፊት የ 30 (ሰላሳ) ተከታታይ ቀናት የቅድመ-ወሊድ ፈቃድ ፣ እንዲሁም ስትወልድ ከወለደችበት ቀን ጀምሮ ለ 90 (ዘጠና) ተከታታይ ቀናት የድህረ-ወሊድ ፈቃድ ከክፍያ ጋር ይሰጣታል፡፡
4, ሠራተኛዋ ከመውለዷ በፊት የወሰደችው የ 30 (ሰላሳ) የሥራ ቀናት የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ሲያልቅ ካልወለደች እስከምትወልድበት ቀን ድረስ ከላይ በቁጥር ሁለት ስር በተመለከተው መሠረት እረፍት ልታገኝ ትችላለች፡፡ የ 30 (ሰላሳ) የሥራ ቀናት
የቅድመ-ወሊድ ፈቃዷ ሳያልቅ ከወለደች 90 (ዘጠና) የሥራ ቀናት የድህረ-ወሊድ ፈቃዷ ይጀምራል፡፡
የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀፅ 88
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ህጋዊ መከላከል (Self Defence) በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ
.............
ህጋዊ መከላከል ማንኛውም ሰው እራሱን ወይም ሌላውን ሰው ከማንኛውም ጥቃት የሚጠብቅበት በህግ የተፈቀደ ተግባር ነው፡፡ ሆኖም ህጋዊ መከላከል በህግ በተቀመጠው መልኩ ብቻ መተግበር ያለበት ነው፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ ህጋዊ መካላከልን እንደሚከተለው በዝርዝር እንመለከታለን፡፡
ህጋዊ መከላከል (Self Defence) ምንነት
በ1996 ዓ.ም ከወጣዉ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 78 እንደምንረዳው ህጋዊ መከላከል "የራስን ወይም የሌላዉን ሰዉ መብት ህገወጥ ከሆነ ጥቃት ወይም በቅርቡ ከሚደርስ ሕገወጥ ጥቃት ለማዳን ጥቃቱ እንዳይደርስ ለማድረግ ሌላ መንገድ ሳይኖር ሲቀር ከሁኔታዉ መጠን ባለማለፍ የሚፈፀም ድርጊት ነው”፡፡ የህጋዊ መከላከል ፅንሰ ሀሳብ እንደየ ሀገሩ ህግ የተለያየ አገላለፅ ቢኖረዉም ሁሉም የሚስማሙበት አንድ ዋና ነጥብ አለ፡፡ ይኸዉም ራስን ወይም ሌላዉን፣ የራስን ወይም የሌላዉን ሰዉ ፍትሐዊ መብት ህገወጥ ከሆነ ጥቃት ለመከላከል ከመጠን ባለማለፍ የሚፈፀም የኃይል ተግባር እንደ ወንጀል የማታይና በህግ የተፈቀደ መሠረታዊ መብት መሆኑን ነዉ፡፡
አንድ ድርጊት ህጋዊ መከላከል መሆኑ የሚረጋገጠው በወንጀል ህጉ አንቀጽ 78 ላይ ያሉ ፍሬ ነገሮች መሟላታቸው ሲረጋገጡ ብቻ ነው፡፡ እነዚህ ፍሬ ነገሮችን በዝርዝር ስንመለከት፡-
• አስቀድሞ የተሰነዘረ ወይም በርግጠኛ ሊደርስ የሚችል ህገወጥ ጥቃት መኖር
ህጋዊ መከላከል ለማድረግ በመጀመሪያ ህገ-ወጥ የሆነ ጥቃት መሰንዘር ወይም በእርግጠኝነት በቅርብ ሊሰነዘር እንደሆነ መታወቅ አለበት፡፡ ይህ ህገ-ወጥ ጥቃት ጥቃቱን በሚከላከለው ሰው ላይ ወይም ደግሞ በሌላ ሰው ላይ መድረሱ አሊያም ጥቃቱ በቅርብ ሊደርስ እንደሆነ መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ ይህም እርግጠኛ ባልሆነ እና ገና ለገና ይደርሳል ብሎ በመገመት ብቻ ህጋዊ መከላከል መውሰድ እንደማይቻል ሚያስገነዝብ ነው፡፡
• ተመጣጣኝ መሆን
አንድ ድርጊት እንደ ህጋዊ መከላከል የሚቆጠረዉ ወይም ህጋዊ መከላከል የሚሆነው መከላከሉ ከተሰነዘረዉ ጥቃት ወይም ሊሰነዘር ከነበረው ጥቃት ጋር ተመጣጣኝ ሲሆን ነዉ፡፡ ህጋዊ መከላከሉ ከጥቃቱ ጋር ተመጣጣኝ መሆን አለመሆኑን ለመወሰን መታየት ያለባቸዉ ብዙ ሁኔታዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሁኔታዎችን ስንመለከት የተሰነዘረው ጥቃት ወይም ሊደርስ የነበረው ጥቃት ክብደት፣ የጥቃት አድራሹ ሁኔታና አቅም፣ አጥቂው የተጠቀመበት መሳሪያ ምንነት፣ ጥቃቱ የተሰነዘረበት ሰው አቅም ከአጥቂው ጋር ሲነጻጸር ያለበት ሁኔታ፣ ለመከላከል የተጠቀመው ዘዴ እና መሳሪያ መታየት ይኖርበታል፡፡ ይህ ማለት አጥቂዉ የሰነዘረዉ ጥቃት ክብደት፣ ጥቃቱ የተሰነዘረበት ሰው መብት እና በዚህ መብት ላይ ሊደርስ የሚችለዉ ጉዳት መጠን ተመርምሮ የጥቃቱ ክብደትና የተጠቂዉ መብት መመዛዘን አለባቸዉ ማለት ነዉ፡፡ ይህም ሲባል የደረሰው ህገ-ወጥ ጥቃት ወይም ሊደርስ የነበረው ጥቃት አነስተኛ መሆን ህጋዊ የመከላከል መብትን ያስቀራል ማለት አይደለም፡፡ የጥቃቱ መጠን ምንም ይሁን ተከላካዩ ጥቃቱን ለማስወገድ ከሚያስፈልገዉ በላይ እስካልሄደ ወይም መከላከሉ ከጥቃቱ መጠን ጋር የተመጣጠነ እስከሆነ ድረስ ማንኛዉንም መብቱን ሕገወጥ ከሆነ ጥቃት መከላከል ይችላል፡፡
አጥቂዉ ጥቃቱን ለማድረስና ተከላካዩም ለመከላከል የተጠቀመበት ዘዴና መሣሪያ ከግምት ዉስጥ መግባት አለበት ሲባል ግን አጥቂዉ የተጠቀመበትና ተከላካዩ የተከላከለበት መሣሪያ የግድ ተመሳሳይ ይሁን ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንም ተከላካዩ ጥቃቱን ለመከላከል የተጠቀመበት መሣሪያ አጥቂዉ ከተጠቀመበት መሣሪያና ሊደርስ ከነበረዉ ጥቃት ጋር ተመጣጣኝ መሆን አለበት ማለት ነዉ፡፡
በተጨማሪም የአጥቂዉና የተከላካዩ ጥንካሬና ዕድሜ አብሮ መታየት ያለበት ጉዳይ ነዉ፡፡ ለምሳሌ አንድ የሠላሳ አመት ሰው የአስራ አምስት አመት ልጅ ልትመታው ስትሰነዝር ከምቱ ለመዳን ወይም ምቱን ለመቀልበስ በያዘው የጦር መሳሪያ ተኩሶ ቢመታትና ብትሞት ራስን ለመከላከል የተወሰደ እርምጃ ነው አያስብልም፡፡ ምክንያቱም የተሰነዘረበት ጥቃት፣ ለመከላከል የተጠቀመበት መሣሪያ፣ ከአጥቂዋ ጥንካሬና ዕድሜ አንጻር ሲመረመር የመከላከሉ ድርጊት ተመጣጣኝ አለመሆኑ በግልፅ ይታያል፡፡
• ጥቃቱ እንዳይደርስ ለመድረግ ሌላ መንገድ አለመኖር
ህጋዊ መካላከል ሊደረግ የሚችለው ጥቃተ የተሰነዘረበት ሰው ጥቃቱን ለመቀልበስ ወይም በቅርብ ሊሰነዘር የሚችል ህገወጥ ጥቃትን ለማስቀረት ከህጋዊ መካላከል ውጪ ሌላ አማራጭ የሌለው ከሆነ ብቻ ነው፡፡
ህጋዊ መካላከልና ተጠያቂነት
ህጋዊ የመከላከል እርምጃ ህጉን የተከተለ እስከሆነ ወይም ከአስፈላጊዉ መጠን እስካላለፈ ድረስ ህጋዊ መከላከል የወሰደዉን ሰዉ ሙሉ በሙሉ ከወንጀል ተጠያቂነት ነፃ የሚያደርግ ድርጊት ነዉ፡፡ ሆኖም የመከላከል ሂደቱ ከመጠን ያለፈ ከሆነ እንደተፈፀመው ወንጀል አይነት በወንጀል ህጉ የተመለከተውን ቅጣት ይቀጣል፡፡
በእርግጥ ህጋዊ የመከላከል መብትን ከመጠን በማለፍ ምክንያት ጥፋተኛ የሆነ ሰዉ ፍርድ ቤት እንደመሰለዉ ቅጣት ሊያቀልለት እንደሚችል የወንጀል ህጉ በግልጽ ደንግጎ ይገኛል፡፡ የመከላከል ድረጊቱ ከመጠን ያለፈዉ ጥቃቱ ባስከተለበት ይቅርታ ሊያስገኝ በሚችል ፍርሃት፣ ድንገተኛ ድንጋጤ ወይም በደም ፍላት ምክንያት እንደሆነ ፍርድ ቤት ሙሉ በሙሉ ከቅጣት ነፃ ሊያደርገዉ እንደሚችል በወንጀል ህጉ አንቀፅ 79(2) ላይ ተደንግጓል፡፡
ማጠቃለያ
በኢ.ፍ.ድ.ሪ የወንጀል ህግ መሠረት ህጋዊ መከላከል በህግ የተፈቀደ መብት ቢሆንም፣ ጥቃት የደረሰበት ሰዉ ወይም ሊደርስበት የነበረ ሰዉ ሁሉ በህጋዊ መከላከል ሰበብ የፈለገዉን ድርጊት ሁሉ ይፈፅማል ማለት አይደለም፡፡ አንድ ሰው በቀጥታ የመከለከል እርምጃ ከመወሰዱ በፊት ሌላ ከጥቃቱ ሊያመልጥ የሚችልበት ዘዴ መፈለግ ያለበት ሲሆን ህጋዊ መከላከሉ አስፈላጊ ከሆነም ሊወሰድ የሚገባዉ መከላከል ከጥቃቱ ጋር ተመጣጣኝ መሆን ይኖርበታል፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/lawsocieties
.............
ህጋዊ መከላከል ማንኛውም ሰው እራሱን ወይም ሌላውን ሰው ከማንኛውም ጥቃት የሚጠብቅበት በህግ የተፈቀደ ተግባር ነው፡፡ ሆኖም ህጋዊ መከላከል በህግ በተቀመጠው መልኩ ብቻ መተግበር ያለበት ነው፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ ህጋዊ መካላከልን እንደሚከተለው በዝርዝር እንመለከታለን፡፡
ህጋዊ መከላከል (Self Defence) ምንነት
በ1996 ዓ.ም ከወጣዉ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 78 እንደምንረዳው ህጋዊ መከላከል "የራስን ወይም የሌላዉን ሰዉ መብት ህገወጥ ከሆነ ጥቃት ወይም በቅርቡ ከሚደርስ ሕገወጥ ጥቃት ለማዳን ጥቃቱ እንዳይደርስ ለማድረግ ሌላ መንገድ ሳይኖር ሲቀር ከሁኔታዉ መጠን ባለማለፍ የሚፈፀም ድርጊት ነው”፡፡ የህጋዊ መከላከል ፅንሰ ሀሳብ እንደየ ሀገሩ ህግ የተለያየ አገላለፅ ቢኖረዉም ሁሉም የሚስማሙበት አንድ ዋና ነጥብ አለ፡፡ ይኸዉም ራስን ወይም ሌላዉን፣ የራስን ወይም የሌላዉን ሰዉ ፍትሐዊ መብት ህገወጥ ከሆነ ጥቃት ለመከላከል ከመጠን ባለማለፍ የሚፈፀም የኃይል ተግባር እንደ ወንጀል የማታይና በህግ የተፈቀደ መሠረታዊ መብት መሆኑን ነዉ፡፡
አንድ ድርጊት ህጋዊ መከላከል መሆኑ የሚረጋገጠው በወንጀል ህጉ አንቀጽ 78 ላይ ያሉ ፍሬ ነገሮች መሟላታቸው ሲረጋገጡ ብቻ ነው፡፡ እነዚህ ፍሬ ነገሮችን በዝርዝር ስንመለከት፡-
• አስቀድሞ የተሰነዘረ ወይም በርግጠኛ ሊደርስ የሚችል ህገወጥ ጥቃት መኖር
ህጋዊ መከላከል ለማድረግ በመጀመሪያ ህገ-ወጥ የሆነ ጥቃት መሰንዘር ወይም በእርግጠኝነት በቅርብ ሊሰነዘር እንደሆነ መታወቅ አለበት፡፡ ይህ ህገ-ወጥ ጥቃት ጥቃቱን በሚከላከለው ሰው ላይ ወይም ደግሞ በሌላ ሰው ላይ መድረሱ አሊያም ጥቃቱ በቅርብ ሊደርስ እንደሆነ መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ ይህም እርግጠኛ ባልሆነ እና ገና ለገና ይደርሳል ብሎ በመገመት ብቻ ህጋዊ መከላከል መውሰድ እንደማይቻል ሚያስገነዝብ ነው፡፡
• ተመጣጣኝ መሆን
አንድ ድርጊት እንደ ህጋዊ መከላከል የሚቆጠረዉ ወይም ህጋዊ መከላከል የሚሆነው መከላከሉ ከተሰነዘረዉ ጥቃት ወይም ሊሰነዘር ከነበረው ጥቃት ጋር ተመጣጣኝ ሲሆን ነዉ፡፡ ህጋዊ መከላከሉ ከጥቃቱ ጋር ተመጣጣኝ መሆን አለመሆኑን ለመወሰን መታየት ያለባቸዉ ብዙ ሁኔታዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሁኔታዎችን ስንመለከት የተሰነዘረው ጥቃት ወይም ሊደርስ የነበረው ጥቃት ክብደት፣ የጥቃት አድራሹ ሁኔታና አቅም፣ አጥቂው የተጠቀመበት መሳሪያ ምንነት፣ ጥቃቱ የተሰነዘረበት ሰው አቅም ከአጥቂው ጋር ሲነጻጸር ያለበት ሁኔታ፣ ለመከላከል የተጠቀመው ዘዴ እና መሳሪያ መታየት ይኖርበታል፡፡ ይህ ማለት አጥቂዉ የሰነዘረዉ ጥቃት ክብደት፣ ጥቃቱ የተሰነዘረበት ሰው መብት እና በዚህ መብት ላይ ሊደርስ የሚችለዉ ጉዳት መጠን ተመርምሮ የጥቃቱ ክብደትና የተጠቂዉ መብት መመዛዘን አለባቸዉ ማለት ነዉ፡፡ ይህም ሲባል የደረሰው ህገ-ወጥ ጥቃት ወይም ሊደርስ የነበረው ጥቃት አነስተኛ መሆን ህጋዊ የመከላከል መብትን ያስቀራል ማለት አይደለም፡፡ የጥቃቱ መጠን ምንም ይሁን ተከላካዩ ጥቃቱን ለማስወገድ ከሚያስፈልገዉ በላይ እስካልሄደ ወይም መከላከሉ ከጥቃቱ መጠን ጋር የተመጣጠነ እስከሆነ ድረስ ማንኛዉንም መብቱን ሕገወጥ ከሆነ ጥቃት መከላከል ይችላል፡፡
አጥቂዉ ጥቃቱን ለማድረስና ተከላካዩም ለመከላከል የተጠቀመበት ዘዴና መሣሪያ ከግምት ዉስጥ መግባት አለበት ሲባል ግን አጥቂዉ የተጠቀመበትና ተከላካዩ የተከላከለበት መሣሪያ የግድ ተመሳሳይ ይሁን ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንም ተከላካዩ ጥቃቱን ለመከላከል የተጠቀመበት መሣሪያ አጥቂዉ ከተጠቀመበት መሣሪያና ሊደርስ ከነበረዉ ጥቃት ጋር ተመጣጣኝ መሆን አለበት ማለት ነዉ፡፡
በተጨማሪም የአጥቂዉና የተከላካዩ ጥንካሬና ዕድሜ አብሮ መታየት ያለበት ጉዳይ ነዉ፡፡ ለምሳሌ አንድ የሠላሳ አመት ሰው የአስራ አምስት አመት ልጅ ልትመታው ስትሰነዝር ከምቱ ለመዳን ወይም ምቱን ለመቀልበስ በያዘው የጦር መሳሪያ ተኩሶ ቢመታትና ብትሞት ራስን ለመከላከል የተወሰደ እርምጃ ነው አያስብልም፡፡ ምክንያቱም የተሰነዘረበት ጥቃት፣ ለመከላከል የተጠቀመበት መሣሪያ፣ ከአጥቂዋ ጥንካሬና ዕድሜ አንጻር ሲመረመር የመከላከሉ ድርጊት ተመጣጣኝ አለመሆኑ በግልፅ ይታያል፡፡
• ጥቃቱ እንዳይደርስ ለመድረግ ሌላ መንገድ አለመኖር
ህጋዊ መካላከል ሊደረግ የሚችለው ጥቃተ የተሰነዘረበት ሰው ጥቃቱን ለመቀልበስ ወይም በቅርብ ሊሰነዘር የሚችል ህገወጥ ጥቃትን ለማስቀረት ከህጋዊ መካላከል ውጪ ሌላ አማራጭ የሌለው ከሆነ ብቻ ነው፡፡
ህጋዊ መካላከልና ተጠያቂነት
ህጋዊ የመከላከል እርምጃ ህጉን የተከተለ እስከሆነ ወይም ከአስፈላጊዉ መጠን እስካላለፈ ድረስ ህጋዊ መከላከል የወሰደዉን ሰዉ ሙሉ በሙሉ ከወንጀል ተጠያቂነት ነፃ የሚያደርግ ድርጊት ነዉ፡፡ ሆኖም የመከላከል ሂደቱ ከመጠን ያለፈ ከሆነ እንደተፈፀመው ወንጀል አይነት በወንጀል ህጉ የተመለከተውን ቅጣት ይቀጣል፡፡
በእርግጥ ህጋዊ የመከላከል መብትን ከመጠን በማለፍ ምክንያት ጥፋተኛ የሆነ ሰዉ ፍርድ ቤት እንደመሰለዉ ቅጣት ሊያቀልለት እንደሚችል የወንጀል ህጉ በግልጽ ደንግጎ ይገኛል፡፡ የመከላከል ድረጊቱ ከመጠን ያለፈዉ ጥቃቱ ባስከተለበት ይቅርታ ሊያስገኝ በሚችል ፍርሃት፣ ድንገተኛ ድንጋጤ ወይም በደም ፍላት ምክንያት እንደሆነ ፍርድ ቤት ሙሉ በሙሉ ከቅጣት ነፃ ሊያደርገዉ እንደሚችል በወንጀል ህጉ አንቀፅ 79(2) ላይ ተደንግጓል፡፡
ማጠቃለያ
በኢ.ፍ.ድ.ሪ የወንጀል ህግ መሠረት ህጋዊ መከላከል በህግ የተፈቀደ መብት ቢሆንም፣ ጥቃት የደረሰበት ሰዉ ወይም ሊደርስበት የነበረ ሰዉ ሁሉ በህጋዊ መከላከል ሰበብ የፈለገዉን ድርጊት ሁሉ ይፈፅማል ማለት አይደለም፡፡ አንድ ሰው በቀጥታ የመከለከል እርምጃ ከመወሰዱ በፊት ሌላ ከጥቃቱ ሊያመልጥ የሚችልበት ዘዴ መፈለግ ያለበት ሲሆን ህጋዊ መከላከሉ አስፈላጊ ከሆነም ሊወሰድ የሚገባዉ መከላከል ከጥቃቱ ጋር ተመጣጣኝ መሆን ይኖርበታል፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
83771.pdf
196.1 KB
የየሰ/መ/ቁ 83771
በተከራካሪ ወገኖች ክርክር በሚካሄድበት ወቅት በፍ/ቤት ትእዛዝ በተከራካሪ ወገን ስም በባንክ የሚገኝ ገንዘብ ታግዶ እንዲቆይ ተደርጐ ትእዛዙ ፀንቶ በነበረበት ግዜ በገንዘቡ ላይ ወለድ ሊታሰብ ይገባል ወይስ አይገባም በሚል ክርክር የተነሣ እንደሆነ ከጉዳዩ ልዩ ባህሪ ጋር በተገናኘ ፍ/ቤቶች የልዩ አዋቂ ምስክርነትና የባለሙያ ማብራሪያን አስቀርበው በማጣራት ሊወሰኑ የሚገባ ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 136 የሰ/መ/ቁ 83771የሰ/መ/ቁ 83771 በተከራካሪ ወገኖች ክርክር በሚካሄድበት ወቅት በፍ/ቤት ትእዛዝ በተከራካሪ ወገን ስም በባንክ የሚገኝ ገንዘብ ታግዶ እንዲቆይ ተደርጐ ትእዛዙ ፀንቶ በነበረበት ግዜ በገንዘቡ ላይ ወለድ ሊታሰብ ይገባል ወይስ አይገባም በሚል ክርክር የተነሣ እንደሆነ ከጉዳዩ ልዩ ባህሪ ጋር በተገናኘ ፍ/ቤቶች የልዩ አዋቂ ምስክርነትና የባለሙያ ማብራሪያን አስቀርበው በማጣራት ሊወሰኑ የሚገባ ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 136
በተከራካሪ ወገኖች ክርክር በሚካሄድበት ወቅት በፍ/ቤት ትእዛዝ በተከራካሪ ወገን ስም በባንክ የሚገኝ ገንዘብ ታግዶ እንዲቆይ ተደርጐ ትእዛዙ ፀንቶ በነበረበት ግዜ በገንዘቡ ላይ ወለድ ሊታሰብ ይገባል ወይስ አይገባም በሚል ክርክር የተነሣ እንደሆነ ከጉዳዩ ልዩ ባህሪ ጋር በተገናኘ ፍ/ቤቶች የልዩ አዋቂ ምስክርነትና የባለሙያ ማብራሪያን አስቀርበው በማጣራት ሊወሰኑ የሚገባ ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 136 የሰ/መ/ቁ 83771የሰ/መ/ቁ 83771 በተከራካሪ ወገኖች ክርክር በሚካሄድበት ወቅት በፍ/ቤት ትእዛዝ በተከራካሪ ወገን ስም በባንክ የሚገኝ ገንዘብ ታግዶ እንዲቆይ ተደርጐ ትእዛዙ ፀንቶ በነበረበት ግዜ በገንዘቡ ላይ ወለድ ሊታሰብ ይገባል ወይስ አይገባም በሚል ክርክር የተነሣ እንደሆነ ከጉዳዩ ልዩ ባህሪ ጋር በተገናኘ ፍ/ቤቶች የልዩ አዋቂ ምስክርነትና የባለሙያ ማብራሪያን አስቀርበው በማጣራት ሊወሰኑ የሚገባ ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 136
እንኳን አደረሳችሁ🙏 መልካም በዓል‼️
........... @lawsocieties ......
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ቤተሰብነታችሁን አረጋግጡ።
👆👆👆👆👆👆👆👆👆
https://t.me/lawsocieties
........... @lawsocieties ......
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ቤተሰብነታችሁን አረጋግጡ።
👆👆👆👆👆👆👆👆👆
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ስለ_ህግ ለማወቅ አማራጭ መንገድ የሆነውን አለ ህግ ቻናልን ቤተሰብ ይሁኑ።
#ህግ አለን
#ባለሙያ አለን
#ለእናንተ ጊዜም አለን
#ሁሉም አለ
ይህንን ጠቃሚ የህግ ቻናል ለሚወዱት ወዳጅ ዘመድ ሼር በማድረግ መልካም መሆንዎን ያረጋግጡ።
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#ህግ አለን
#ባለሙያ አለን
#ለእናንተ ጊዜም አለን
#ሁሉም አለ
ይህንን ጠቃሚ የህግ ቻናል ለሚወዱት ወዳጅ ዘመድ ሼር በማድረግ መልካም መሆንዎን ያረጋግጡ።
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
በጣም ጠቃሚ ሰበሮች ስለ ውል ህጎች
የሰበር መዝገብ ቁጥር 26565
ሊፈጠር ወይም ሊከሰት እንደሚችል ቀድሞ ሊገመት ወይም ሊታሰብና ጥንቃቄ ሊደረግበት የሚቻል ሁኔታ ድንገተኛ ደራሽ ቢሆን እንኳ ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ (Force majeure) ተብሎ የማይወሰድ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ ህ/ቁ. 1792(2)
የሰበር መዝገብ ቁጥር 29369
የባለዕዳው ቀጥተኛ የውል ፈፃሚነት ከውሉ ባህሪ አኳያ ማስፈፀም አለመቻል ውሉ እንዲሰረዝ መጠየቅ ሳያስፈልግ ኪሣራ ካለ መጠየቅ ስለመቻሉ ( በውል መሠረት ግዴታውን ያልተወጣ ወገንን አስገድዶ ለማስፈፀም የማይቻል በሆነ ጊዜ በውሉ ግዴታውን የተወጣው ወገን ውሉ ባለመፈፀሙ ምክንያት የደረሰውን ኪሣራ ለመጠየቅ ስለመቻሉ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1771(1) እና (2)
የሰበር መዝገብ ቁጥር 30947
የስልክ ክፍያ እንዲከፈል ለተገልጋይ የተሰጠ ማስታወቂያ ክፍያው እንዲከፈል ለማድረግ እንጂ ክፍያውን ላለመፈፀም ምክንያት ሊሆን አለመቻሉ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1901
የሰበር መዝገብ ቁጥር 31480
ለአቅመ አዳም ካልደረሰ ልጅ ጋር የሚደረግ የመያዛ ውል ተፈፃሚ የማይሆን ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 2187/1
የሰበር መዝገብ ቁጥር 12719
በሁለት ወገኖች መካከል የተፈረመ ሰነድን እንደ ህጋዊ ስምምነት ለመውሰድ የፈራሚ ወገኖችን ሃሳብና ፍላጐት መመርመር አስፈላጊ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1734, 1952/1/
የሰበር መዝገብ ቁጥር 20232
የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች የተዋዋይ ወገኖች መብትና ግዴታዎች የሚፈጠሩባቸውና የሚረጋገጡባቸው በመሆናቸው የውል ህግ መሰረታዊ ድንጋጌዎች መሟላታቸው አስፈላጊ ሁኔታ ስለመሆኑ የንግድ ህግ ቁ. 715, የፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1706, 1679
የሰበር መዝገብ ቁጥር 22448
ፍርድ እንዲፈፀም ለመጠየቅ ችሎታ ያለው ፍርድ የተፈረደለት ሰው /ወገን/ ብቻ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ ህ/ቁ. 378/1/
የሰበር መዝገብ ቁጥር 24974
በውል ከተገባ ግዴታ አመዛኙ ክፍል ተፈፀመ ወይም/እና አይነተኛ የሆነ የውል መጣስ ተከስቷል ለማለት ባልተቻለ ጊዜ ውል እንዲሰረዝ ለመወሰን የማይቻል ስለመሆኑየፍ/ብ/ህ/ቁ. 1771,1784, 1785
የሰበር መዝገብ ቁጥር 26996
ውል የተደረገበት ጉዳይ ሊፈፀም የማይችል ሆኖ በተገኘ ጊዜ ተዋዋይ ወገኖችን ወደ ነበሩበት ቦታ የመመለስ ውጤት ያለው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1715, 1815
የሰበር መዝገብ ቁጥር 27349
ተዋዋይ ወገኖች በመካከላቸው የሚፈጠርን አለመግባባት በስምምነት ወይም ደግሞ በአስታራቂ አማካኝነት ለመፍታት የተስማሙ ከሆነ ይኼው ስምምነት ተፈፃሚ መሆን ያለበት ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1765, 1731/1/
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የሰበር መዝገብ ቁጥር 26565
ሊፈጠር ወይም ሊከሰት እንደሚችል ቀድሞ ሊገመት ወይም ሊታሰብና ጥንቃቄ ሊደረግበት የሚቻል ሁኔታ ድንገተኛ ደራሽ ቢሆን እንኳ ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ (Force majeure) ተብሎ የማይወሰድ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ ህ/ቁ. 1792(2)
የሰበር መዝገብ ቁጥር 29369
የባለዕዳው ቀጥተኛ የውል ፈፃሚነት ከውሉ ባህሪ አኳያ ማስፈፀም አለመቻል ውሉ እንዲሰረዝ መጠየቅ ሳያስፈልግ ኪሣራ ካለ መጠየቅ ስለመቻሉ ( በውል መሠረት ግዴታውን ያልተወጣ ወገንን አስገድዶ ለማስፈፀም የማይቻል በሆነ ጊዜ በውሉ ግዴታውን የተወጣው ወገን ውሉ ባለመፈፀሙ ምክንያት የደረሰውን ኪሣራ ለመጠየቅ ስለመቻሉ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1771(1) እና (2)
የሰበር መዝገብ ቁጥር 30947
የስልክ ክፍያ እንዲከፈል ለተገልጋይ የተሰጠ ማስታወቂያ ክፍያው እንዲከፈል ለማድረግ እንጂ ክፍያውን ላለመፈፀም ምክንያት ሊሆን አለመቻሉ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1901
የሰበር መዝገብ ቁጥር 31480
ለአቅመ አዳም ካልደረሰ ልጅ ጋር የሚደረግ የመያዛ ውል ተፈፃሚ የማይሆን ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 2187/1
የሰበር መዝገብ ቁጥር 12719
በሁለት ወገኖች መካከል የተፈረመ ሰነድን እንደ ህጋዊ ስምምነት ለመውሰድ የፈራሚ ወገኖችን ሃሳብና ፍላጐት መመርመር አስፈላጊ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1734, 1952/1/
የሰበር መዝገብ ቁጥር 20232
የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች የተዋዋይ ወገኖች መብትና ግዴታዎች የሚፈጠሩባቸውና የሚረጋገጡባቸው በመሆናቸው የውል ህግ መሰረታዊ ድንጋጌዎች መሟላታቸው አስፈላጊ ሁኔታ ስለመሆኑ የንግድ ህግ ቁ. 715, የፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1706, 1679
የሰበር መዝገብ ቁጥር 22448
ፍርድ እንዲፈፀም ለመጠየቅ ችሎታ ያለው ፍርድ የተፈረደለት ሰው /ወገን/ ብቻ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ ህ/ቁ. 378/1/
የሰበር መዝገብ ቁጥር 24974
በውል ከተገባ ግዴታ አመዛኙ ክፍል ተፈፀመ ወይም/እና አይነተኛ የሆነ የውል መጣስ ተከስቷል ለማለት ባልተቻለ ጊዜ ውል እንዲሰረዝ ለመወሰን የማይቻል ስለመሆኑየፍ/ብ/ህ/ቁ. 1771,1784, 1785
የሰበር መዝገብ ቁጥር 26996
ውል የተደረገበት ጉዳይ ሊፈፀም የማይችል ሆኖ በተገኘ ጊዜ ተዋዋይ ወገኖችን ወደ ነበሩበት ቦታ የመመለስ ውጤት ያለው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1715, 1815
የሰበር መዝገብ ቁጥር 27349
ተዋዋይ ወገኖች በመካከላቸው የሚፈጠርን አለመግባባት በስምምነት ወይም ደግሞ በአስታራቂ አማካኝነት ለመፍታት የተስማሙ ከሆነ ይኼው ስምምነት ተፈፃሚ መሆን ያለበት ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1765, 1731/1/
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
በይርጋ የማይታገዱ የፍትሀብሄር ጉዳዬች
🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑♨️♨️♨️
የይርጋ መሰረታዊ ዓላማ ማንኛውም በህግ በግልፅ የተደነገገ መብትና ግዴታ በህጉ በተወሰነው ወይም በተገደበው ጊዜ ውስጥ ስልጣን ላለው አካል እንዲቀርቡ ግዴታን በማስቀመጥ መብቴ ተጣሰብኝ የሚል ወገን ዳተኛ ሳይሆን በትጋት መብቱን እንዲጠይቅ ለማስቻል መሆኑ ይታወቃል።
ነገር ግን አንዳንድ ጉዳዬች ከንብረቶቹ ልዩ ባህሪና የመንግስት ፖሊሲ አንፃር ህግ አውጪው በይርጋ እንዳይታገዱ አድርጎ ያስቀመጣቸው የፍትሀብሄር ጉዳዬች አሉ። ከእነዚህ መካከል፦
#የመፋለም ክስ ( petitory action)
♨️♨️♨️🛑🛑🛑🛑♨️
ለባለሀብቱ የባለቤትነት መብት ከሚሰጣቸው መብቶች መካከል ንብረቱ ያለ እርሱ ፈቃድ ከህግ ውጪ በሌላ ሰው ወይም ሀይል ከተወሰደ ንብረቱን ካለበት ድረስ በመከታተል የማስመለስ ወይም የመፋለም መብት አንዱ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 ድንጋጌ ያስረዳል፡፡
ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን” በሚል ርዕስ ስር በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1192 የተመለከተው በሚንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት በአስር ዓመት የጊዜ ወሰን /ይርጋ/ ቀሪ የሚሆንበትን አግባብ ያመላከተ ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን ግን አያሳይም፡፡
🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑♨️♨️♨️
የይርጋ መሰረታዊ ዓላማ ማንኛውም በህግ በግልፅ የተደነገገ መብትና ግዴታ በህጉ በተወሰነው ወይም በተገደበው ጊዜ ውስጥ ስልጣን ላለው አካል እንዲቀርቡ ግዴታን በማስቀመጥ መብቴ ተጣሰብኝ የሚል ወገን ዳተኛ ሳይሆን በትጋት መብቱን እንዲጠይቅ ለማስቻል መሆኑ ይታወቃል።
ነገር ግን አንዳንድ ጉዳዬች ከንብረቶቹ ልዩ ባህሪና የመንግስት ፖሊሲ አንፃር ህግ አውጪው በይርጋ እንዳይታገዱ አድርጎ ያስቀመጣቸው የፍትሀብሄር ጉዳዬች አሉ። ከእነዚህ መካከል፦
#የመፋለም ክስ ( petitory action)
♨️♨️♨️🛑🛑🛑🛑♨️
ለባለሀብቱ የባለቤትነት መብት ከሚሰጣቸው መብቶች መካከል ንብረቱ ያለ እርሱ ፈቃድ ከህግ ውጪ በሌላ ሰው ወይም ሀይል ከተወሰደ ንብረቱን ካለበት ድረስ በመከታተል የማስመለስ ወይም የመፋለም መብት አንዱ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 ድንጋጌ ያስረዳል፡፡
ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን” በሚል ርዕስ ስር በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1192 የተመለከተው በሚንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት በአስር ዓመት የጊዜ ወሰን /ይርጋ/ ቀሪ የሚሆንበትን አግባብ ያመላከተ ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን ግን አያሳይም፡፡
Proclamation_No_1074_2018_Driver’s_Qualification_Certification_License.pdf
628.6 KB
Share 'Proclamation-No.-1074-2018-Driver’s-Qualification-Certification-License-Proclamation.pdf'
ጠበቃ ወንድሙ ኢብሳ ከእስር ተለቀው የገና በአልን ከቤተሰቦቻቸው ጋር አሳልፈዋል::
****......
ጠበቃና የሕግ አማካሪ የሆኑት ወንድሙ ኢብሳ እስር ከተፈፀመባቸው ጊዜ ጀምሮ ማህበሩ ተገቢውን ክትትል እያደረገ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል።
ጠበቃ ወንድሙ ኢብሳ ለኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር አመራር በስልክ እንደገለፁት በእስር ቆይታቸው ይህ ነው የተባለ የአያያዝ ችግር ያልገጠማቸውና በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል::
ጠበቃው ችሎት በመድፈር በሚል ታህሳስ 11 ቀን 2015ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ሰበታ ከተማ በሚገኘው የዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት ጋር በተፈጠረ የቃላት ልውውጥ መነሻ ተደርጎ የአራት ወራት እስራት የተፈረደባቸው መሆኑ የሚታወስ ነው::
የይግባኝ ክርክሩም በተሟላ ሁኔታ ታህሳስ 26 ቀን 2015ዓ.ም በኦሮሚያ ጠቅላይ ፍ/ቤት የተደረገ ሲሆን ችሎቱም ከፍተኛው ፍ/ቤት ለችሎት መድፈር መነሻ አድርጌአቸዋለሁ ካላቸው "17 ነጥቦች" 16ቱን ውድቅ በማድረግ የ4 ወራት እስራት ቅጣቱን በመሻር ከ 18 ቀናት እስር በኃላ እንዲለቀቁ ውሳኔ ሰጥቷል::
ጠበቃ ወንድሙ ኢብሳ ይህ የእስር ቅጣት ከተላለፈባቸው ቀን ጀምሮ "ከፍተኛ እገዛ" ላደረገላቸው የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር እና ለማህበሩ መሪዎች እንዲሁም በሂደቱ ለተሳተፉ የህግ ባለሙያዎች ምስጋናቸውንም አቅርበዋል:: የጠበቆች ማህበሩ ጉዳዩን የሚከታተሉ እና በችሎት የሚሰየሙ ጠበቆችን ከመመደብ ጀምሮ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ንግግሮችን ሲያደርግ የቆየ ሲሆን በቀጣይ ከጉዳዩና ተያያዥ ነጥቦች ዙሪያ የተሟላ ሪፖርት እና አቋሙን ይፋ የሚያደርግ መሆኑን ይገልፃል::
ለኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
አዲስ አበባ
****......
ጠበቃና የሕግ አማካሪ የሆኑት ወንድሙ ኢብሳ እስር ከተፈፀመባቸው ጊዜ ጀምሮ ማህበሩ ተገቢውን ክትትል እያደረገ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል።
ጠበቃ ወንድሙ ኢብሳ ለኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር አመራር በስልክ እንደገለፁት በእስር ቆይታቸው ይህ ነው የተባለ የአያያዝ ችግር ያልገጠማቸውና በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል::
ጠበቃው ችሎት በመድፈር በሚል ታህሳስ 11 ቀን 2015ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ሰበታ ከተማ በሚገኘው የዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት ጋር በተፈጠረ የቃላት ልውውጥ መነሻ ተደርጎ የአራት ወራት እስራት የተፈረደባቸው መሆኑ የሚታወስ ነው::
የይግባኝ ክርክሩም በተሟላ ሁኔታ ታህሳስ 26 ቀን 2015ዓ.ም በኦሮሚያ ጠቅላይ ፍ/ቤት የተደረገ ሲሆን ችሎቱም ከፍተኛው ፍ/ቤት ለችሎት መድፈር መነሻ አድርጌአቸዋለሁ ካላቸው "17 ነጥቦች" 16ቱን ውድቅ በማድረግ የ4 ወራት እስራት ቅጣቱን በመሻር ከ 18 ቀናት እስር በኃላ እንዲለቀቁ ውሳኔ ሰጥቷል::
ጠበቃ ወንድሙ ኢብሳ ይህ የእስር ቅጣት ከተላለፈባቸው ቀን ጀምሮ "ከፍተኛ እገዛ" ላደረገላቸው የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር እና ለማህበሩ መሪዎች እንዲሁም በሂደቱ ለተሳተፉ የህግ ባለሙያዎች ምስጋናቸውንም አቅርበዋል:: የጠበቆች ማህበሩ ጉዳዩን የሚከታተሉ እና በችሎት የሚሰየሙ ጠበቆችን ከመመደብ ጀምሮ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ንግግሮችን ሲያደርግ የቆየ ሲሆን በቀጣይ ከጉዳዩና ተያያዥ ነጥቦች ዙሪያ የተሟላ ሪፖርት እና አቋሙን ይፋ የሚያደርግ መሆኑን ይገልፃል::
ለኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
አዲስ አበባ
የዐቃብያነ_ሕግ_የትምህርትና_ስልጠና_ዋስትና_መመሪያ_ቁጥር_19_2015_ዓ_ም_ታህሳስ_5_2015_ዓ_ም.docx
93.7 KB
መመሪያ ቁጥር ---------------------/2015 ዓ.ምበአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፍትሕ ቢሮ የተሻሻለው የዐቃብያነ-ሕግ የትምህርትና ስልጠና ዋስትና መመሪያበየደረጃው ባሉ የፍትሕ ቢሮ መዋቅሮች የሚሰሩ ዐቃብያነ-ሕግን የአጭርና የረጅም ጊዜ ትምህርትና ስልጠና ተጠቃሚ በማድረግ የመፈፀምና የማስፈፀም አቅማቸውን ማጎልበት በማስፈለጉ፤በአጭርም ሆነ በረጅም ጊዜ የዐቃብያነ-ሕግ ትምህርትና ስልጠና አመላመል ዙሪያ እያጋጠሙ ያሉ የተለያዩ ክፍተቶችን የማስተካከሉ አስፈላጊነት ስለታመነበት፤ዐቃብያነ-ሕግ ወደ ትምህርትና ስልጠና ሲገቡ ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንዲወዳደሩ ማድረግ ተገቢ ሆኖ በመገኘቱ፤ የድህረ-ምረቃ ትምህርት እድል ያገኙ ዐቃብያነ-ሕግ የመመረቂያ ማሟያ የምርምር ጽሁፍ ክፍያ ማሻሻያ እንዲደረግበት በክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት በተወሰነው መሰረት ተገቢውን ማስተካከያ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፍትሕ ቢሮ በተሻሻለው የዐቃብያነ-ሕግ መተዳደሪያ ደንብ ቁጥር 52/1999 ዓ.ም አንቀጽ 106 ስር በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል፡፡
ኪራይ ውል ሰ/መ/ቁ. 97111 ሐምሌ 29 ቀን 2007 ዓ.ም (ያልታተመ)
የኪራይ ውል ጊዜው ካበቃ በኋላ ተከራይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት ሆኖም በማስጠንቀቂያው ላይ አዲሱ የኪራይ መጠን ካልተገለጸ ተከራይ ቤቱን ሳይለቅ ለቆየበት ጊዜ ሊከፍል የሚገባው ክስ እስከቀረበበት ጊዜ ድረስ ላለው በድሮው ተመን መሰረት ሲሆን ክስ ቀርቦ መጥሪያ ከደረሰው ቀን ጀምሮ ደግሞ ሊከፍል የሚገባው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2950 ንዑስ አንቀፅ 2 መሰረት፣ በአካባቢው ተመሳሳይ የንግድ ቤቶችን በምን ያህል ዋጋ እንደሚከራዩ በባለሙያዎችና ሽማግሌዎች ተጣርቶ ከቀረበ በኋላ በሚቀርበው ሪፖርት መሰረት ነው።
ፍ/ህ/ቁ 2950 /2/
የኪራይ ውል ጊዜው ካበቃ በኋላ ተከራይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት ሆኖም በማስጠንቀቂያው ላይ አዲሱ የኪራይ መጠን ካልተገለጸ ተከራይ ቤቱን ሳይለቅ ለቆየበት ጊዜ ሊከፍል የሚገባው ክስ እስከቀረበበት ጊዜ ድረስ ላለው በድሮው ተመን መሰረት ሲሆን ክስ ቀርቦ መጥሪያ ከደረሰው ቀን ጀምሮ ደግሞ ሊከፍል የሚገባው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2950 ንዑስ አንቀፅ 2 መሰረት፣ በአካባቢው ተመሳሳይ የንግድ ቤቶችን በምን ያህል ዋጋ እንደሚከራዩ በባለሙያዎችና ሽማግሌዎች ተጣርቶ ከቀረበ በኋላ በሚቀርበው ሪፖርት መሰረት ነው።
ፍ/ህ/ቁ 2950 /2/
በፍትሐብሔር ክርክር የፍርድ ቤት መጥሪያ ደርሶት በቀነ ቀጠሮ ተከራካሪ ወገኖች አለመቅረብ ህጋዊ አንድምታው ምን ይመስላል?
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ፍርድ ቤት አንድ ጉዳይ ማየት እና ውሳኔ ለማስተላለፍ የተለያዩ ቀጠሮዎች እንደሚሰጥ የታወቀ ነው፡፡ የመጀመሪያ ተከሳሽ መከሰሱን አውቆ ለቀረበበት ክስ መከላከያ የሚሆኑ ማስረጃዎችን በፅሁፍ የሚያቀርብበት ነው፡፡ ፍርድ ቤት ተከሳሽ መጥሪያው በአግባቡ ደርሶት መልሱን ይዞ ከቀረበ ፍርድ ቤቱ በስነ-ስርዓት ህጉ 241 እና ተከታዮቹ መሰረት ክሱን ለመስማት ይቀጥራል፡፡
ክስ ለመስማት ፍርድ ቤቱ የሚሰጠው ቀጠሮ ሁለተኛ ቀጠሮ ነው፡፡ በስነ-ስርዓት ህጉ 241 እና ተከታዮቹ መሰረት ክስ መስማት ሁለት ሂደቶችን የያዘ ነው፤ የመጀመሪያው ስለ መጀመሪያ ክስ መስማት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ስለዋናው ክስ መስማት ነው፡፡ የመጀመሪያው ክስ መስማት ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለዋና ክስ መስማት የሚያዘጋጅበት ሂደት ሲሆን፤ ፍርድ ቤት የቀረበውን ክስን እና የተከሳሽን መልስ የሚያነብበት፣ የግራ ቀኙን አቋም የሚሰማበት፣ ተቀዳሚ መቃወሚያ ላይ ብይን የሚሰጥበትና ጭብጥ የሚመሠርትበት ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ዋና ክስ መስማት ሂደት ማለትም የተከራካሪ ወገኖችን ክርክር መስማት፣ ምስክሮችን መስማት እና ማስረጃዎችን መርመር እንዲሁም የፍርድ ውሳኔ የሚሰጥበት ሂደት ነው፡፡.
ከሳሽ ወይም ተከሳሽ በየትኛው ቀነ ቀጠሮ መቅረባቸው እጅግ አስፈላጊ ነው? በሁሉም ቀጠሮዎች ወይስ መከላከያ ማስረጃ በሚቀርበበት ወይስ ክስ በሚሰማበት? ወደሚሉት ነጥቦች ስንገባ በእርግጥ ተከራካሪ ወገኖች እራሳቸው ወይም ወኪሎቻቸው ፍርድ ቤት በሚወስነው በማንኛውም ቀጠሮ ቀን ፍርድ ቤት መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ በቀጠሮዎች አለመገኘት የክስ መዝገብ መዘጋት፣ የመከለከያ ማስረጃ የማቀረብና የመከላከል መብትን ማጣት እና ሌሎች ተከራካሪ ወገኖች ቢቀርቡ ሊቀሩ የሚችሉ ትዕዛዞች እንዲሰጡ ይሆናል፡፡
በፍትሐብሔር የሥነ-ሥርዓት ሕጉ እንዲሁም ሰበር በተለያዩ መዝገቦች የሰጣቸውን ውሳኔዎች (ለምሳሌ በመዝገብ ቁጥር 14184፣ 15835፣ 36412፣ 36390፣ 58487 እና 95638) ስንመለከት ለመልስ በተቀጠረበት ቀጠሮ የከሳሽም ሆነ የተከሳሽ አለመገኘት መዝገብ እንዲዘጋ ወይም ክርክሩ ተከሳሽ በሌለበት እንዲታይም የማድረግ ውጤት አይኖረውም፡፡ ከሳሹ ወይም መጥሪያ እንዲያደርስ ታዞ የነበረው አካል ማድረሱን ወይም አለማድረሱን እንዲያረጋግጥ መጥሪያ በመላክ ወይም በሌላ ማንኛውም ዘዴ ማረጋገጥ አለበት፡፡ ተከሳሹ የደረሰው መሆኑን ካረጋገጠ የመጀመሪያ ክስ ለመስማት ቀጠሮ መስጠት የሚችል ሲሆን ተከሳሹ ካልደረሰው ደግሞ ድጋሚ መጥሪያ ለተከሳሹ መላክ ይኖርበታል፡፡
በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ህጉ አንቀጽ 69 መሰረት ፍርድ ቤቱ ቃል/ጉዳዩ ሊሰማ (hearing of suit) በወስነው ቀነ ቀጠሮ ከሳሽ (ክስ ያቀረበው) እና ተከሳሽ ራሳቸው ወይም ወኪሎቻቸው መቅረብ አለባቸው (ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 69) ፍርድ ቤቱ ጉዳዩ ሊሰማ በተወሰነበት ቀነ ቀጠሮ አለመቅረብ የሚያስከትለው ውጤት እንደ ቀሪው ተከራካሪ ወገን ይወሰናል፡፡ ሁለቱም ተከራካሪዎች ሳይቀርቡ ሲቀር፣ ከሳሽ ሲቀር እና ተከሳሽ ሲቀር ተፈጻሚ የሚሆነው ሥርዓት የተለያየ ነው፡፡
ሁለቱም ወገኖች ሳይቀርቡ የቀሩ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን ይዘጋዋል፡፡ ከሳሽ በቀነ ቀጠሮ ሳይቀርብ ተከሳሽ ቀርቦ የቀረበበትን ክስ የካደ ከሆነ መዝገቡን በመዝጋት ተከሳሽን ያሰናብተዋል (ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 73)፤ ሆኖም ግን ከሳሽ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በቀዳሚ ቀነ ቀጠሮ ሳይቀርብ የቀረበትን በቂ ምክንያት ገልጾ መዝገቡ እንዲታይ አቤቱታ ካቀረበ ፍርድ ቤቱ ለተከሳሽ የከሳሽ አቤቱታ እንዲደርሰው በማድረግ መዝገቡን እንደገና ከፍቶ ነገሩ እንዲቀጥል ትዕዛዝ በመስጠት ጉዳዩ የሚሰማበትን ቀነ ቀጠሮ ይወስናል፡፡
ፍርድ ቤቱ ጉዳዩ ሊሰማ በተወሰነበት ቀነ ቀጠሮ ከሳሽ ቀርቦ ተከሳሽ ሳይቀርብ የቀረ እንደሆነ የፍርድ ቤቱ ቀዳሚ ስራ መጥሪያው ለተከሳሹ መድረሱን ማረጋገጥ ነው (ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 70)፡፡ ፍርድ ቤቱ ለተከሳሽ የላከው መጥሪያ የደረሰው መሆኑን ካረጋገጠ በሌለበት ጉዳዩን መስማት ይቀጥላል፡፡ መጥሪያው ለተከሳሽ በአግባቡ ያልደሰረው መሆኑን ካረጋገጠ ወይም አጠራጣሪ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ሁለተኛ መጥሪያ እንዲላክ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ ተከሳሽ መጥሪያው የደረሰው መሆኑ ቢረጋገጥ እንኳን ለተከሳሹ የተሰጠበት ቀን ለክሱ መልስ ለማዘጋጀት በቂ ሆኖ በማይገመት አጭር ጊዜ መሆኑን ፍርድ ቤቱ የተረዳው ከሆነ ፍርድ ቤቱ የክርክሩን መሰማት ለሌላ ቀነ ቀጠሮ ያስተላልፈዋል፡፡ አንድ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ተከሳሾች የተላከው መጥሪያ ለአንዱ ወይም ለአንዳንዶች ሳይደርስ የቀረው በከሳሽ ቸልተኘነት ወይም ጉደለት ከሆነ ፍርድ ቤቱ ከሳሽ መጥሪያ ባልደረሰው ወይም ባልደረሳቸው ተከሳሾች ላይ የቀረበውን ክስ ሊዘጋ ወይም ቀነ ቀጠሮ ሊቀይር ይችላል፡፡
ክርክሩ በሌለበት እንዲቀጥል የተወሰነበት ተከሳሽ በቀጣይ ቀነ ቀጠሮ ቀርቦ በቂ በሆነ ምክንያት በመጀመሪው ቀነ ቀጠሮ ያለመቅረቡን ካስረዳ መከላከያውን አቅርቦ የመከራከር መብት ያለው ስለመሆኑ የፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 72 ይደነግጋል፡፡ እንዲሁም ክርክሩ ሊሰማ በተቀጠረበት ቀን ቀርቦ መልስ ሳይሰጥ ወይም መከራከሪያውን ሳያሰማ በሌለበት ትዕዛዝ ወይም ውሳኔ መሰጠቱን ካወቀ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተከሳሽ መጥሪያው በሚገባ ያልደረሰው መሆኑን ወይም በቂ ምክንያት በማቅረብ ትዕዛዙ ወይም ውሳኔው እንዲነሳለት በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 78 መሰረት መጠየቅ ይችላል፡፡ በዚሁ ድንጋጌ መሰረትም ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ ያቀረበውን አቤቱታ አግባብ መሆኑን ከተረዳ ለከሳሽ አቤቱታው እንዲደርሰው በማድረግ ትዕዛዙን ወይም ውሳኔውን በማንሳት ክርክሩን እንደገና ስምቶ ይወስናል፡፡
ሆኖም በቂ ምክንያት ምንድን ነው? የሚለው ነጥብ አከራካሪ ሊሆን ይችላል፡፡ የቀረበው ምክንያት በቂ መሆን አለመሆኑ እንደ ጉዳዩ ዓይነት የሚታይ በመሆኑ አንድ ዓይነት ትርጉም መስጠት አይቻልም፡፡ ነገር ግን የተከራካሪ ወገኖች በእኩል የመዳኘት መብት እንዲሁም ተከሳሽ ለቀረበበት ክስ የበኩሉን መልስ የመስጠት መብቱ፤ የመሰማት መሠረታዊ መብት (The right to be heard) ይበልጥ ሊያስከብር በሚችል ሁኔታ መተርጎም አለበት፡፡ እንዲሁም የስነ ስርዓት ህጉ ዓላማን ፍትሐዊ በሆነ ስርዓት በአጭር ጊዜ፣ በአነስተኛ ውጪ እና ድግግሞሽን ባስቀረ ሁኔታ የተከራካሪ ወገኖችን ጉዳይ መቋጨትን በሚያሳካ መልኩ መተርጓም አለበት፡፡
ሳሙኤል ግርማ
ሕግ ባለሙያ እና ጠበቃ
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ፍርድ ቤት አንድ ጉዳይ ማየት እና ውሳኔ ለማስተላለፍ የተለያዩ ቀጠሮዎች እንደሚሰጥ የታወቀ ነው፡፡ የመጀመሪያ ተከሳሽ መከሰሱን አውቆ ለቀረበበት ክስ መከላከያ የሚሆኑ ማስረጃዎችን በፅሁፍ የሚያቀርብበት ነው፡፡ ፍርድ ቤት ተከሳሽ መጥሪያው በአግባቡ ደርሶት መልሱን ይዞ ከቀረበ ፍርድ ቤቱ በስነ-ስርዓት ህጉ 241 እና ተከታዮቹ መሰረት ክሱን ለመስማት ይቀጥራል፡፡
ክስ ለመስማት ፍርድ ቤቱ የሚሰጠው ቀጠሮ ሁለተኛ ቀጠሮ ነው፡፡ በስነ-ስርዓት ህጉ 241 እና ተከታዮቹ መሰረት ክስ መስማት ሁለት ሂደቶችን የያዘ ነው፤ የመጀመሪያው ስለ መጀመሪያ ክስ መስማት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ስለዋናው ክስ መስማት ነው፡፡ የመጀመሪያው ክስ መስማት ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለዋና ክስ መስማት የሚያዘጋጅበት ሂደት ሲሆን፤ ፍርድ ቤት የቀረበውን ክስን እና የተከሳሽን መልስ የሚያነብበት፣ የግራ ቀኙን አቋም የሚሰማበት፣ ተቀዳሚ መቃወሚያ ላይ ብይን የሚሰጥበትና ጭብጥ የሚመሠርትበት ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ዋና ክስ መስማት ሂደት ማለትም የተከራካሪ ወገኖችን ክርክር መስማት፣ ምስክሮችን መስማት እና ማስረጃዎችን መርመር እንዲሁም የፍርድ ውሳኔ የሚሰጥበት ሂደት ነው፡፡.
ከሳሽ ወይም ተከሳሽ በየትኛው ቀነ ቀጠሮ መቅረባቸው እጅግ አስፈላጊ ነው? በሁሉም ቀጠሮዎች ወይስ መከላከያ ማስረጃ በሚቀርበበት ወይስ ክስ በሚሰማበት? ወደሚሉት ነጥቦች ስንገባ በእርግጥ ተከራካሪ ወገኖች እራሳቸው ወይም ወኪሎቻቸው ፍርድ ቤት በሚወስነው በማንኛውም ቀጠሮ ቀን ፍርድ ቤት መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ በቀጠሮዎች አለመገኘት የክስ መዝገብ መዘጋት፣ የመከለከያ ማስረጃ የማቀረብና የመከላከል መብትን ማጣት እና ሌሎች ተከራካሪ ወገኖች ቢቀርቡ ሊቀሩ የሚችሉ ትዕዛዞች እንዲሰጡ ይሆናል፡፡
በፍትሐብሔር የሥነ-ሥርዓት ሕጉ እንዲሁም ሰበር በተለያዩ መዝገቦች የሰጣቸውን ውሳኔዎች (ለምሳሌ በመዝገብ ቁጥር 14184፣ 15835፣ 36412፣ 36390፣ 58487 እና 95638) ስንመለከት ለመልስ በተቀጠረበት ቀጠሮ የከሳሽም ሆነ የተከሳሽ አለመገኘት መዝገብ እንዲዘጋ ወይም ክርክሩ ተከሳሽ በሌለበት እንዲታይም የማድረግ ውጤት አይኖረውም፡፡ ከሳሹ ወይም መጥሪያ እንዲያደርስ ታዞ የነበረው አካል ማድረሱን ወይም አለማድረሱን እንዲያረጋግጥ መጥሪያ በመላክ ወይም በሌላ ማንኛውም ዘዴ ማረጋገጥ አለበት፡፡ ተከሳሹ የደረሰው መሆኑን ካረጋገጠ የመጀመሪያ ክስ ለመስማት ቀጠሮ መስጠት የሚችል ሲሆን ተከሳሹ ካልደረሰው ደግሞ ድጋሚ መጥሪያ ለተከሳሹ መላክ ይኖርበታል፡፡
በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ህጉ አንቀጽ 69 መሰረት ፍርድ ቤቱ ቃል/ጉዳዩ ሊሰማ (hearing of suit) በወስነው ቀነ ቀጠሮ ከሳሽ (ክስ ያቀረበው) እና ተከሳሽ ራሳቸው ወይም ወኪሎቻቸው መቅረብ አለባቸው (ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 69) ፍርድ ቤቱ ጉዳዩ ሊሰማ በተወሰነበት ቀነ ቀጠሮ አለመቅረብ የሚያስከትለው ውጤት እንደ ቀሪው ተከራካሪ ወገን ይወሰናል፡፡ ሁለቱም ተከራካሪዎች ሳይቀርቡ ሲቀር፣ ከሳሽ ሲቀር እና ተከሳሽ ሲቀር ተፈጻሚ የሚሆነው ሥርዓት የተለያየ ነው፡፡
ሁለቱም ወገኖች ሳይቀርቡ የቀሩ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን ይዘጋዋል፡፡ ከሳሽ በቀነ ቀጠሮ ሳይቀርብ ተከሳሽ ቀርቦ የቀረበበትን ክስ የካደ ከሆነ መዝገቡን በመዝጋት ተከሳሽን ያሰናብተዋል (ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 73)፤ ሆኖም ግን ከሳሽ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በቀዳሚ ቀነ ቀጠሮ ሳይቀርብ የቀረበትን በቂ ምክንያት ገልጾ መዝገቡ እንዲታይ አቤቱታ ካቀረበ ፍርድ ቤቱ ለተከሳሽ የከሳሽ አቤቱታ እንዲደርሰው በማድረግ መዝገቡን እንደገና ከፍቶ ነገሩ እንዲቀጥል ትዕዛዝ በመስጠት ጉዳዩ የሚሰማበትን ቀነ ቀጠሮ ይወስናል፡፡
ፍርድ ቤቱ ጉዳዩ ሊሰማ በተወሰነበት ቀነ ቀጠሮ ከሳሽ ቀርቦ ተከሳሽ ሳይቀርብ የቀረ እንደሆነ የፍርድ ቤቱ ቀዳሚ ስራ መጥሪያው ለተከሳሹ መድረሱን ማረጋገጥ ነው (ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 70)፡፡ ፍርድ ቤቱ ለተከሳሽ የላከው መጥሪያ የደረሰው መሆኑን ካረጋገጠ በሌለበት ጉዳዩን መስማት ይቀጥላል፡፡ መጥሪያው ለተከሳሽ በአግባቡ ያልደሰረው መሆኑን ካረጋገጠ ወይም አጠራጣሪ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ሁለተኛ መጥሪያ እንዲላክ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ ተከሳሽ መጥሪያው የደረሰው መሆኑ ቢረጋገጥ እንኳን ለተከሳሹ የተሰጠበት ቀን ለክሱ መልስ ለማዘጋጀት በቂ ሆኖ በማይገመት አጭር ጊዜ መሆኑን ፍርድ ቤቱ የተረዳው ከሆነ ፍርድ ቤቱ የክርክሩን መሰማት ለሌላ ቀነ ቀጠሮ ያስተላልፈዋል፡፡ አንድ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ተከሳሾች የተላከው መጥሪያ ለአንዱ ወይም ለአንዳንዶች ሳይደርስ የቀረው በከሳሽ ቸልተኘነት ወይም ጉደለት ከሆነ ፍርድ ቤቱ ከሳሽ መጥሪያ ባልደረሰው ወይም ባልደረሳቸው ተከሳሾች ላይ የቀረበውን ክስ ሊዘጋ ወይም ቀነ ቀጠሮ ሊቀይር ይችላል፡፡
ክርክሩ በሌለበት እንዲቀጥል የተወሰነበት ተከሳሽ በቀጣይ ቀነ ቀጠሮ ቀርቦ በቂ በሆነ ምክንያት በመጀመሪው ቀነ ቀጠሮ ያለመቅረቡን ካስረዳ መከላከያውን አቅርቦ የመከራከር መብት ያለው ስለመሆኑ የፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 72 ይደነግጋል፡፡ እንዲሁም ክርክሩ ሊሰማ በተቀጠረበት ቀን ቀርቦ መልስ ሳይሰጥ ወይም መከራከሪያውን ሳያሰማ በሌለበት ትዕዛዝ ወይም ውሳኔ መሰጠቱን ካወቀ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተከሳሽ መጥሪያው በሚገባ ያልደረሰው መሆኑን ወይም በቂ ምክንያት በማቅረብ ትዕዛዙ ወይም ውሳኔው እንዲነሳለት በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 78 መሰረት መጠየቅ ይችላል፡፡ በዚሁ ድንጋጌ መሰረትም ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ ያቀረበውን አቤቱታ አግባብ መሆኑን ከተረዳ ለከሳሽ አቤቱታው እንዲደርሰው በማድረግ ትዕዛዙን ወይም ውሳኔውን በማንሳት ክርክሩን እንደገና ስምቶ ይወስናል፡፡
ሆኖም በቂ ምክንያት ምንድን ነው? የሚለው ነጥብ አከራካሪ ሊሆን ይችላል፡፡ የቀረበው ምክንያት በቂ መሆን አለመሆኑ እንደ ጉዳዩ ዓይነት የሚታይ በመሆኑ አንድ ዓይነት ትርጉም መስጠት አይቻልም፡፡ ነገር ግን የተከራካሪ ወገኖች በእኩል የመዳኘት መብት እንዲሁም ተከሳሽ ለቀረበበት ክስ የበኩሉን መልስ የመስጠት መብቱ፤ የመሰማት መሠረታዊ መብት (The right to be heard) ይበልጥ ሊያስከብር በሚችል ሁኔታ መተርጎም አለበት፡፡ እንዲሁም የስነ ስርዓት ህጉ ዓላማን ፍትሐዊ በሆነ ስርዓት በአጭር ጊዜ፣ በአነስተኛ ውጪ እና ድግግሞሽን ባስቀረ ሁኔታ የተከራካሪ ወገኖችን ጉዳይ መቋጨትን በሚያሳካ መልኩ መተርጓም አለበት፡፡
ሳሙኤል ግርማ
ሕግ ባለሙያ እና ጠበቃ
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ለሙከራ ጊዜ የተቀጠረ #ሰራተኛ ሰ/መ/ቁጥር 212420
አሰሪው ለሙከራ ጊዜ የተቀጠረን ሠራተኛ ለስራው ተስማሚ አለመሆኑን ሳይመዝን ካሰናበተ ስንብቱ #ህገ- ወጥ ነው።
ስንብቱ ህገ-ወጥ በመሆኑ ካሳ የሚከፈለው ሲሆን የስንብት እና የማስጠንቀቂያ ክፍያዎች ግን አገልግልትን ታሳቢ ተደርገው የሚሰሉ በመሆኑ አይከፈሉትም።
የካሳው መጠን ሰራተኛው የሙከራ ጊዜውን (60 ቀናት) ቢጨርስ ሊያገኝ ይችል የነበረውን የ2 ወር ደመወዝ ብቻ ነው።
አብርሀም ዮሀንስ
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
አሰሪው ለሙከራ ጊዜ የተቀጠረን ሠራተኛ ለስራው ተስማሚ አለመሆኑን ሳይመዝን ካሰናበተ ስንብቱ #ህገ- ወጥ ነው።
ስንብቱ ህገ-ወጥ በመሆኑ ካሳ የሚከፈለው ሲሆን የስንብት እና የማስጠንቀቂያ ክፍያዎች ግን አገልግልትን ታሳቢ ተደርገው የሚሰሉ በመሆኑ አይከፈሉትም።
የካሳው መጠን ሰራተኛው የሙከራ ጊዜውን (60 ቀናት) ቢጨርስ ሊያገኝ ይችል የነበረውን የ2 ወር ደመወዝ ብቻ ነው።
አብርሀም ዮሀንስ
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የቁሙ ቀንድ ከበት ማረድ ፤ በባዶ እግር መሄድ ፤ አጭር ቁምጣ መልበስ የተከለከለ ነው!! -
የምስ/ጎጃም ዞን አስተዳደር ም/ቤት የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል ይሕውም፦
1. ያለ እድሜ ጋብቻ እና የህግ ማእቀፍ ያላቸው ሌሎች ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ በወጣው ህግ መሰረት ሳይሸራረፍ ሙሉ በሙሉ ተፈጻሚ እንዲሆን ማድረግ፤
2. ከአለባበስ ባህላችን አኳያ በዞናችን ስር ያላችሁ ሁሉም ወረዳዎች የምንመራው ህዝብ አንድም ሰው በባዶ እግሩ እንዳይሄድና ቁምጣ ሱሪ ለብሶ የሚሄድ ሰው እንዳይኖር በቁርጠኝነት መስራት፤
3. ተዝካርን በተመለከተ በተዝካር ስም የሚፈጸም የተንዛዛ ድግስ እንዳይፈጸም ስርአተ በቤተክስቲያን በሚያዝዘው መሰረት ስርአተ ፍትሃት ላደረጉ ካህናት አባቶች ብቻ ቤተክርስቲያን ላይ 1 በግ/ፍየል እና 2 ሌማት ብቻ እንዲቀርብ፤
4. ጋብቻ አንዱ ባህላዊ እሴታችን መሆኑ የሚታወቅ ስለሆነ እና ትውልድ መቀጠል ስላበት ጋብቻ ይቁም አይባልም ነገር ግን በጋብቻ ስም የሚፈጸም የተንዛዛ ድግስን በተመለከተ
ለአጋቢ ሽማግሌዎችና ለቤተሰብ የሚሆን1 በግ/ፍየል እና 2 ሌማት ብቻ እንዲሆን የተወሰነ ስለሆነ እና የቀንድ ከብት ማረድ ፍጹም የተከለከለ መሆኑ ታውቆ በውሳኔው መሰረት በየደረጃው ያላቹህ የፖለቲካ እና የጸጥታ አመራሮች ከፍትህ ተቋሙ ጋር ተቀናጅታቹህ እንድታስፈጽሙ በጥብቅ እያሳወቅን አፈጻጸሙንም በጋራ እየገመገማቹህ የተገኘውን ውጤት እና የመጣ ለውጥ እስከ ጥር15/2015 ዓ/ም እንድታሳዉቁ እናሳዉቃለን፡፡ -
የምስ/ጎጃም ዞን አስተዳደር ም/ቤት
https://t.me/lawsocieties
የምስ/ጎጃም ዞን አስተዳደር ም/ቤት የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል ይሕውም፦
1. ያለ እድሜ ጋብቻ እና የህግ ማእቀፍ ያላቸው ሌሎች ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ በወጣው ህግ መሰረት ሳይሸራረፍ ሙሉ በሙሉ ተፈጻሚ እንዲሆን ማድረግ፤
2. ከአለባበስ ባህላችን አኳያ በዞናችን ስር ያላችሁ ሁሉም ወረዳዎች የምንመራው ህዝብ አንድም ሰው በባዶ እግሩ እንዳይሄድና ቁምጣ ሱሪ ለብሶ የሚሄድ ሰው እንዳይኖር በቁርጠኝነት መስራት፤
3. ተዝካርን በተመለከተ በተዝካር ስም የሚፈጸም የተንዛዛ ድግስ እንዳይፈጸም ስርአተ በቤተክስቲያን በሚያዝዘው መሰረት ስርአተ ፍትሃት ላደረጉ ካህናት አባቶች ብቻ ቤተክርስቲያን ላይ 1 በግ/ፍየል እና 2 ሌማት ብቻ እንዲቀርብ፤
4. ጋብቻ አንዱ ባህላዊ እሴታችን መሆኑ የሚታወቅ ስለሆነ እና ትውልድ መቀጠል ስላበት ጋብቻ ይቁም አይባልም ነገር ግን በጋብቻ ስም የሚፈጸም የተንዛዛ ድግስን በተመለከተ
ለአጋቢ ሽማግሌዎችና ለቤተሰብ የሚሆን1 በግ/ፍየል እና 2 ሌማት ብቻ እንዲሆን የተወሰነ ስለሆነ እና የቀንድ ከብት ማረድ ፍጹም የተከለከለ መሆኑ ታውቆ በውሳኔው መሰረት በየደረጃው ያላቹህ የፖለቲካ እና የጸጥታ አመራሮች ከፍትህ ተቋሙ ጋር ተቀናጅታቹህ እንድታስፈጽሙ በጥብቅ እያሳወቅን አፈጻጸሙንም በጋራ እየገመገማቹህ የተገኘውን ውጤት እና የመጣ ለውጥ እስከ ጥር15/2015 ዓ/ም እንድታሳዉቁ እናሳዉቃለን፡፡ -
የምስ/ጎጃም ዞን አስተዳደር ም/ቤት
https://t.me/lawsocieties