ያም ሆነ ይህ በተለመደዉ አሰራር መሰረት ዐቃቤህግ የራሱን ምስክር በተመለከተ ቃሉን እየለወጠ መሆኑን ለማስረዳት በፖሊስ ጣቢያ የሰጠዉን ቃል ጽሁፍ ለምስክሩ አሳይቶ ፊርማዉን እንዲያረጋግጥ ካደረገ በኋላ ለፍርድቤት በማቅረብ ሲያስወስን ይታያል:: በተመሳሳይ ሁኔታ የተከሳሹ ምስክር በፖሊስ ምርመራ ጊዜ የሰጠዉን ቃል ጽሁፍ ለማስተባበያነት እንዲታይለት ቢጠይቅ ምን ስህተት አለዉ? የተከሳሽ ምስክር በፖሊስ ጣቢያ የምስክርነት ቃል ሊያስመዘግብ ይችላል? የተከሳሽ ምስክር በወንጀል ምርመራ ጊዜ በጉዳዩ ላይ ቃሉን በምስክርነት ከሰጠ በኋላ ዐቃቤህግ ማስረጃ አድርጎ ሳይቆጥረዉ ቢቀርና ተከሳሽ ምስክሩ ቢያደርገዉ ለፖሊስ ምስክርነቱን የሰጠ ምስክር ሊባል አይችልም?
በኢትዮጵያ ህግ መሰረት የሚደረገዉ ማስተባበል ቀድሞ በተሰጠ ቃል ላይ የተመረኮዘ ነዉ:: ሆኖም የማስትባበል ስራ ቀደም ሲል በምስክሩ በተደረገ ሌላ ተግባርም ሊከናወን ይችላል:: እንዲሁም የምስክሩን ባህሪ (ምናልባትም የመዋሸት) እና በጉዳዩ ዉጤት ምስክሩ የሚኖረዉን ጥቅም በማሳየት ምስክሩን ማስተባበል ይቻላል::
ከወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 145 ዉጪ ያሉ ምስክር ማስተባበያ ዘዴዎች፡- የቀድሞ የምስክር ቃልንም በተመለከተ ህጉ በፖሊስ ጣቢያ የተመዘገበን ቃል ብቻ ይገልጻል:: ቀደም ሲል በፍርድቤት በማንኛዉም ጉዳይ የተመዘገበ ቃልስ ምስክሩን ለማስተባበል አይዉልም? የቀዳሚ ምርመራ ፍርድቤት የመዘገበዉ ምስክርነት ለዚህ አገልግሎት ማዋል አይቻልም? በክስ መስማት ጊዜ በፍርድቤት ከሚደረግ የቃል ምዝገባ ሌላ ቃልን ለመመዝገብ ብቻ በሚሰራ ፍርድቤት ቃል ሊመዘገብ አይችልም (የወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁ. 35)? ምስክሩ ባለዉ የሥራ ኃላፊነት መሰረት የጻፋቸዉ ጽሁፎች ወይም ደብዳቤዎች ምስክሩን ለማስተባበል አያገለግሉም?
በነዚህ በሁሉም ሆነ በፖሊስ ጣቢያ ቃል ምስክርን ለማስተባበል አስቀድሞ ይህን ቃል ወይም መጻጻፍ እና ይዘቱን ማወቅ እንደሚያስፈልግ አያጠያይቅም:: ለዚህ ደግሞ ከዚህ በፊት እንደተገለጸዉ ዝግጅት ማድረግ የማይታለፍ ይሆናል::
Via #Tsegaye Demeke - Lawyer
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
በኢትዮጵያ ህግ መሰረት የሚደረገዉ ማስተባበል ቀድሞ በተሰጠ ቃል ላይ የተመረኮዘ ነዉ:: ሆኖም የማስትባበል ስራ ቀደም ሲል በምስክሩ በተደረገ ሌላ ተግባርም ሊከናወን ይችላል:: እንዲሁም የምስክሩን ባህሪ (ምናልባትም የመዋሸት) እና በጉዳዩ ዉጤት ምስክሩ የሚኖረዉን ጥቅም በማሳየት ምስክሩን ማስተባበል ይቻላል::
ከወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 145 ዉጪ ያሉ ምስክር ማስተባበያ ዘዴዎች፡- የቀድሞ የምስክር ቃልንም በተመለከተ ህጉ በፖሊስ ጣቢያ የተመዘገበን ቃል ብቻ ይገልጻል:: ቀደም ሲል በፍርድቤት በማንኛዉም ጉዳይ የተመዘገበ ቃልስ ምስክሩን ለማስተባበል አይዉልም? የቀዳሚ ምርመራ ፍርድቤት የመዘገበዉ ምስክርነት ለዚህ አገልግሎት ማዋል አይቻልም? በክስ መስማት ጊዜ በፍርድቤት ከሚደረግ የቃል ምዝገባ ሌላ ቃልን ለመመዝገብ ብቻ በሚሰራ ፍርድቤት ቃል ሊመዘገብ አይችልም (የወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁ. 35)? ምስክሩ ባለዉ የሥራ ኃላፊነት መሰረት የጻፋቸዉ ጽሁፎች ወይም ደብዳቤዎች ምስክሩን ለማስተባበል አያገለግሉም?
በነዚህ በሁሉም ሆነ በፖሊስ ጣቢያ ቃል ምስክርን ለማስተባበል አስቀድሞ ይህን ቃል ወይም መጻጻፍ እና ይዘቱን ማወቅ እንደሚያስፈልግ አያጠያይቅም:: ለዚህ ደግሞ ከዚህ በፊት እንደተገለጸዉ ዝግጅት ማድረግ የማይታለፍ ይሆናል::
Via #Tsegaye Demeke - Lawyer
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties