አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የፌዴሬሽን ምክር ቤት የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ በዓለም ዓቀፍ ድርጅቶች ላይ ስላለው ተፈጻሚነት የሰጠው የህገ-መንግስት ትርጉም
በአሠሪና ሠራተኛ ህግ አፈጻጸም አስቸጋሪ ሆነው ከቆዩት ጉዳዮች አንዱ አዋጁ በዓለም ዓቀፍ ድርጅቶችና ዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች ላይ ያለውን ተፈጻሚነት ይመለከራል። በእርግጥ በዚህ ጉዳይ ላይ አዋጁ ግልጽ ነው።
ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶች አዋጁ ተፈጻሚ እንዳይሆን ካልተደረገ በቀር የአዋጁ ተፈጻሚነት ጥያቄ ውስጥ አይገባም
ሆኖም ትልቁ ችግር የአዋጁ የተፈጻሚነት ወሰን ሳይሆን እነዚህ ድርጅቶች ከዓለም ዓቀፍ ስምምነቶች ወይም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ከሚያደርጉት ስምምነት የመነጨ ያለ መከሰስ መብት ስለሚኖራቸው የስራ ክርክር ጉዳይ ሳይታይ ክሱ ወዲያው ውድቅ ይደረጋል።
በ ሰ/መ/ቁ 98541 ቅጽ 17 (አመልካች አቶ አለማየሁ ኦላና እና ተጠሪ የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት (UNDP) ህዳር 10 ቀን 2007 ዓ.ም.) ተጠሪ በዋናው ክርክር ሳይከራከር መዝገቡ አፈጻጸም ደረጃ ላይ እያለ ያለ መከሰስ መብቱ በምክንያትነት ተጠቅሶ አመልካች በፍርድ ያገኙትን መብት ተነጥቀዋል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሰጠው የህገ-መንግስት ትርጉም በተወሰነ መልኩ ይህንን ኢ-ፍትሐዊ የመብት መጣስ የሚያስቀር ይመስላል።
ምክር ቤቱ በውሳኔው ላይ ለሁለት መሰረታዊ ነጥቦች እልባት ሰጥቷል። ይኸውም

1. ያለ መከሰስ መብት ተፈጻሚነቱ ከዲፕሎማቲክ መብትና ድርጊት ጋር በተያያዘ እንጂ በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ጋር የሚያያዝ አይደለም።

2. ዓለም ዓቀፍ ድርጅቶች ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በገቡት ውል መሰረት ያለ መከሰስ መብት ሲያገኙ በውሉ የተመለከተው የአለመግባባት መፍቻ መንገድ ተግባራዊ መሆን ካልቻለ የኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች ጉዳዩን አይቶ የመዳኘት ስልጣን አላቸው። @Lawsocieties
የፌዴራል የፍትሕና የሕግ ኢንስቲትዩት ለቤኒሻንጉል ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፍትሕ አካላት ባለሙያዎች ለስድስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየውን ሥልጠና ዛሬ አጠናቀቀ

(ሰኔ 03 ፣ 2014 ዓ.ም) የፌዴራል የፍትሕና የሕግ ኢንስቲትዩት ለቤኒሻንጉል ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፍትህ አካላት ባለሙያዎች (ለዳኞች፣ ለዓቃቤያነ ህግ እና ለፖሊስ ኮሚሽነሮች) ለስድስት ተከታታይ ቀናት በአሶሳ ከተማ ሲሰጥ የቆየውን የአቅም ግንባታ ሥልጠና ዛሬ አጠናቀቀ።

ሥልጠናው ሶስት የተለያዩ ርዕሶችን፡ የፀረ ሽብርተኝነት ህግ' ፣ 'የክስ አመሰራረትና ክርክር ክህሎት' እና 'የቅጣት አወሳሰን መመሪያን' ያካተተ ሲሆን ርዕሶቹ በክልሉ ፍትሕ አካላት አመራሮች የተመረጡ እና ከዚህ በፊት በክልሉ ሲያጋጥሙ የነበረ ክፍተትን ለማሟላት የታሰበ መሆኑም ተገልጿል።

በሥልጠናው የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገኝተው የመዝግያ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሰዒድ ባባከ የለውጡን ቀጣይነት እና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ የመፈፀምና የማስፈፀም አቅምን ለማሳደግ እንዲሁም በክልሉ የህብረተሰቡን የፍትሕ ጥያቄ ለመመለስ የተሰጠው የአቅም ግንባታ ሥልጠናው ጉልህ ሚና ያለው መሆኑን ገልፀዋል።

አቶ ሰዒድ አክለውም ሁሉንም አስቸጋሪ ጉዳዮችን ለመዳሰስ አስቸጋሪ ቢሆንም የክልሉ ፍትሕ አካላት አመራሮች እና ባለሙያዎች ወጪ ቆጣቢ፣ ፈጣንና ፍትሐዊ የሆነ በተለይም በተሰጡት የስልጠና ርዕሶች ላይ አትኩረው በጥብቅ ስራዎችን በማከናወን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

ዘገባው:- የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
Urgent❗️❗️
paid internship vacancy
Location; Adama
Number; 2
#ተመዝገቡ
Address: Oda ( Warka) Team Business center, 2nd floor
office no. 95

Phone number: 0910100328 / 0974600876

The deadline is on Monday 07/10/2014 ዓ.ም

Transparency International Ethiopia

Head office for General info...
ስልክ +251118279746
@Transparency_Ethiopia_Bot

ethiopiatransparency@gmail.com

@TransparencyEthiopia

https://t.me/TransparencyEthiopia
ዶክተር ለማ
ኢንጂነር ለማ
ህግ....... አቶ
ከዛሬ ጀምሮ በህግ የተመረቀ ሰው የክብር ስሙ *በህግ* ለምን ይባልም
*በህግ ለማ* ከስማችሁ መጀመሪያ ላይ እያስገባችሁ ሞክሩት።
ከተስማማችሁ like and share.
አምስት አመት ተምሮ አቶ ⁉️
ይህ ስም እንዲፀድቅ የሚፈልግ ብቻ share‼️
ጥቆማችሁን #comment ላይ አድርሱን
ማን ይሁን
።።።።።።።። #አለ_ህግ #Ale_Hig ።።።።።።
@Lawsocieties

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

በፌስቡክ Facebook
https://www.facebook.com/lawsocieties/

በቴሌግራም Telegram
https://t.me/lawsocieties

ሊክድን LinkedIn
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/

በ ቲክቶክ Tiktok
tiktok.com/@lawsocieties

ትዊተር Twitter
https://twitter.com/Lawsocieties?t=VFQWzXMBnNQnXyZu7z52bQ&s=09

በዩቲዩብ YouTube
https://youtube.com/channel/UCXYKAPt4crrhEx62KvcPzBw

Email address
lawsocieties@gmail.com

Telegram Bot
@LawsocietiesBot
👍👍👍👍👍👍👍👍❗️❗️❗️❗️❗️❗️


።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።🙏
ዳኛ
አቃቤ ህግ
ህግ ባለሙያ
ጠበቃ
ነገረ ፈጅ
..............
......ሌሎችን የህግ ምሩቃን ማን ብዬ ልጥራቸው
መጠሪያ ግን ይህን ያህል አገብጋቢ ጉዳይ ነው
via #Lawsocieties
Federal Justice and Law Institute begins training of Gambella National Regional State Judiciary

Federal Justice and Law Institute has started capacity building training for judges, prosecutors and police at various levels under the Gambella National Regional State in Gambella town.

The training was opened by the head of the Gambella Regional Justice Bureau, Akwai Abuti, who conveyed a message of welcome to the participants.

He said the main purpose of the training is to build the capacity of the judiciary, adding that participants should attend the training properly and contribute their share to the success of the judiciary.

The training will be delivered by Gambella National Regional State Supreme Court Judge Dol Ukuri, Regional Prosecutor W / Yesus Gelan and Regional Supreme Court Judge Chang Teng.

"
Rural and Urban Land Administration Law,
the Anti-Corruption Law and the Penal Code
" will be given for six consecutive days, including today.

This training is in line with the Federal Justice and Law Institute's plan to provide capacity building training to state and city administration judicial professionals who do not have their own training center in the 2014 fiscal year.

>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>

The report is from the Directorate of Communication Affairs!
በወንጀል ክርክር ወቅት የመስቀለኛ ጥያቄ መጠየቂያ መርሆችና ቴክኒኮች
========================
ዐቃቤህግ በመደበኛ የወንጀል ክስ ለመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት ሲቀርብ ስለጉዳዩ በተለይም ስለምስክርነቱ አስቀድሞ ሳይዘጋጅ ማለትም ዕዉቀት ሳይኖረዉ ነዉ:: መስቀለኛ ጥያቄ ሂደት እንኳንስ ያለቅድመዝግጅት ዝግጅትም ተደርጎ አስቸጋሪ ሥራ ነዉ::
የመከላከያ ምስክሮች ከመዋሸት እስከ ሆን ብሎ አለማስታወስ ድረስ መሰናክል ሊፈጥሩ ይችላሉ:: በመስቀለኛ ጥያቄ ሂደቱ ለዐቃቤህግ ተባባሪ ላይሆኑ ይችላሉ::
ስለዚህ ዐቃቤህግ በዚህ ሂደት ለማግኘት የሚፈልገዉን ምናልባትም ሊያገኝ የሚገባዉን ያለማግኘት ችግር ሊያጋጥመዉ ይችላል:: እንዲያዉም የራሱን ክስ ሊጎዳ የሚችል አጋጣሚ ሊፈጠር ይችላል::
ስለዚህ መስቀለኛ ጥያቄን ለማካሄድ ወይም ላለማካሄድ በከፍተኛ ጥንቃቄ መምረጥ አና ማካሄድ የግድ ነዉ:: ለዚህ ደግሞ አንዳንድ መርሆችንና ቴክኒኮችን ማወቅ ተገቢ ነዉ:: እነዚህ መርሆችና ቴክኒኮች በአሰራር ልማድ የምንፈጥራቸዉን ችግሮች ለማረም እገዛ ሊያደርጉ የሚችሉ ናቸዉ:: እነዚህን ቆየት ብለን የምናያቸዉ ሆኖ ከዚያ በፊት ስለመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት ወሰን እና መጠን አንዳንድ ነገሮች እንይ::
በቅድሚያ ከላይ እንደተገለጸዉ መስቀለኛ ጥያቄ አስቸጋሪ ሂደት ነዉ:: አደጋዎቸ አሉት:: ስለዚህ መስቀለኛ ጥያቄ ማከሄድ ተመራጭ ላይሆን ይችላል:: መስቀለኛ ጥያቄ አለማካሄድ ምን ዉጤት አለዉ? በወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁ. 140 እንደተመለከተዉ መስቀለኛ ጥያቄ አለመጠየቅ በሌላዉ ወገን የተነገረዉን እንደማመን አያስቆጥርም:: ስለዚህ መስቀለኛ ጥያቄ ብዙም ባይደፈር ይመረጣል:: በተለይም የመስቀለኛ ጥያቄ ግብ ከሆኑት (የተቃራኒን ምስክርነት የማይታመን መሆኑን ማሳየት በክሱ ላይ የደረሰዉን ጉዳት ማስተካከል ወዘተ) አንዱን ወይም ከዚያ በላይ ለማሳካት የምንችል ወይም ተገቢ ካልሆነ በቀር ወይም ምስክሩ ለጉዳያችን የምንፈልገዉ መረጃ ብቸኛ ምንጭ ካልሆነ በቀር መስቀለኛ ጥያቄ ማካሄድ የሚመከር አይደለም::
ሆኖም ዘወትር እንደሚስተዋለዉ አንዳንድ ምስክሮች ባህሪያቸዉ ምንም ሳይጠየቁ መሄድ የለባቸዉም የሚያስብል ይሆናል:: በዚህ ጊዜ መስቀለኛ ጥያቄ ማንሳት የግድ ከሆነ ከላይ ሲባል እንደነበረዉ አደጋዉ የበዛ በመሆኑ መጠኑን ማሳነስ ይመከራል::
በወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁ. 137(3) ስር መስቀለኛ ጥያቄ በዋና ጥያቄ ጊዜ በተመለሱ ነገሮች ዉስጥ ያለዉን ስህተት አጠራጣሪ ወይም የማይታመን ቃል ለፍርድ ቤቱ ለመግለጽ ወይም ለማስተባበል የሚደረግ መሆኑ ተደንግጓል:: ስለዚህ ከዚህ የወጣ ጥያቄ ሲነሳ ተቃዉሞ ሊገጥም ይችላል:: ሆኖም በዋና ጥያቄ ከተፈጠረዉ ድንበር ወጥቶ መጠየቅ የሚቻልባቸዉ የተለዩ አጋጣሚዎች ይኖራሉ:: ለምሳሌ የምስክሩን ተዓማኒነት የሚመለከቱ ጥያቄዎች በዋና ጥያቄ ጊዜ ባይነሱም በጠቅላላዉ ምስክሩ የተናገረዉን ነገር ተዓማኒነት የሚመለከት ስለሚሆን ተቀባይነት ያለዉ አካሄድ ነዉ:: ለምሳሌ የተለመደዉ የተከሳሽ መከላከያ ክርክር (በወንጀሉ ጊዜ በወንጀሉ ቦታ አልነበርኩም) ሲቀርብ የሚነገረዉ ታሪክ የተፈጸመበትን ጊዜ ከወንጀሉ ጊዜ ጋር እንዲገጥም የማድረግ ነገር ስለሚኖር ምስክሩ ጊዜን በመለየት ረገድ ስላለዉ ችሎታ ለማረጋገጥ በዚህ ዙሪያ ጥያቄ ቢነሳ ሊከለከል አይገባም:: ምስክሩ ተዓማኒነቱ ምን ያህል እንደሆነ ለማሳየት የሚረዳ በመሆኑ ተገቢ ነዉ::

ከተዓማኒነት ጋር በተያያዘ ምስክሩ በነገሩ ዉስጥ ያለዉ ጥቅም ወይም ፍላጎት ሊታለፍ የማይገባዉ ነጥብ ነዉ:: ምስክሩ የሚሰጠዉ ምስክርነት ከነገሩ ዉስጥ ካለዉ ጥቅም ወይም ፍላጎት የተነሳ ከዕዉነት የራቀ ሊሆን ይችላል:: ስለዚህ በነገሩ ዉስጥ ጥቅም እንዳለዉ ማሳየት በሰጠዉ ምስክርነት ላይ ዕምነት እንዲታጣ ሊያደርግ ስለሚችል በዋና ጥያቄ አልተነሳም ተብሎ ቀሪ ሊደረግ አይገባም::
አንዳንዴ ምስክሩ ራሱ ለመስቀለኛ ጥያቄ በሚመልስበት ጊዜ በዋና ጥያቄ ጊዜ ላልተነሱ ሀሳቦች መንገድ ሊከፍት ይችላል:: በዚህ ጊዜ ምስክሩ ራሱ ባነሳዉ ነገር ላይ ሌላ መስቀለኛ ጥያቄ የማይጠየቅበት ምክንያት አይኖርም:: ስለዚህ ዐቃቤህግ እነዚህን አጋጣሚዎች በንቃት መጠባበቅ ይገባዋል፣ ለዚህም ምስክርነቱን በሚገባ ማዳመጥ ይኖርበታል፡፡
ከጭብጥ ከመዉጣት ሌላ በመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት የማይፈቀድ ነገር ምስክርን ማስፈራራት እና ማንጓጠጥ ነዉ:: ምስክሩ ዐቃቤህግ የሚፈልገዉን እንዲል መገደድ የለበትም:: ይህን ማድረግ የሚቻለዉ ክህሎት በተሞላዉ የአጠያየቅ ዘዴ መሆን አለበት:: አዘዉትሮ በፍርድቤቶች በሚደረግ ክርክር ጊዜ የሚስተዋል በህግ ባለሙያዎች (ዐቃብያነህግ ጠበቆች ዳኞች) የሚባል አንድ ነገር አለ:: ምስክሩ እነዚህ ባለሙያዎች እንደፈለጉት ወይም ዕዉነት ነዉ ብለዉ እንደሚያስቡት ሳይናገር በቀረ ጊዜ በሃሰት መመስከር በወንጀል እንደሚያስቀጣ ይነግሩታል:: ይህ ነገር ማስፈራራት ከመሆኑ በተረፈ ነገሩ ተሰምቶ ሳያልቅ እና ምስክሩ የተናገረዉ ሃሰት ይሁን ዕዉነት ሳይረጋገጥ በጉዳዩም ላይ በምስክሩም ላይ ፍርድ የመስጠት ያህል ይሆናል:: ከዐቃቤህግ የህግ ጠባቂነት ሚና አኳያም የሰዉን መብት የሚደነግጉ ህጎችን የመጣስ ዉጤት ይኖረዋል::

የመስቀለኛ ጥያቄዎች ባህሪያት (መሪ ጥያቄ)፡-- ይህ የጥያቄ አይነት በመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት ዉስጥ በህግ የተፈቀደ ቢሆንም ዐቃቤህግ (ሌሎች ባለሙያዎችም) ሲጠቀሙበት አይስተዋልም:: በርግጥ ይህ የጥያቄ አይነት ስለሚያስከትለዉ መልስ ማወቅን ስለሚጠይቅና ዐቃቤህግ ደግሞ ከላይ እንደተገለጸዉ ያለቅድመዝግጅት ስለሚቀርብ ይህን የጥያቄ አይነት ለመጠቀም አይደፋፈርም:: ሆኖም ዋና ጥያቄ የሚመስል ሂደት በማካሄድ ነገሮችን እንዲደገሙ ከማድረግና በዚህም ችሎትን ከማሰላቸት ግፋ ሲልም የዐቃቤህግን ክስ የሚያፈርስ አጋጣሚ ከመፍጠር በዚያዉ በችሎት በተደረገች ዝግጅትም ቢሆን መሪ ጥያቄ በመጠየቅ ምስክሩን እንዳሻዉ እንዳይናገር መቆጣጠር ይመከራል:: በመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት ዋናዉ ግብ ምስክሩን መቆጣጠር የሚመሰክረዉን ነገር መወሰን በዚህም ለመዋሸት ያለዉን ዝንባሌ ወዘተ ማስቀረት ነዉ:: በዋና ጥያቄ ጊዜ ሊነሱ የሚገባቸዉ ዝግ ያልሆኑ ጥያቄዎችን በማንሳት ምስክሩ የሚናገረዉን ነገር ልቅ ማድረግ ሂደቱን ዐቃቤህጉ ሳይሆን ምስክሩ እንዲቆጣጠረዉ ማድረግ ይሆናል::

አጭርና ነጠላ ጥያቄ፡- የተከሳሽን ምስክር በመስቀለኛ ጥያቄ መቆጣጠር የሚቻልበት መንገድ ጥያቄዉን መሪ ጥያቄ በማድረግ ብቻ አይደለም:: ጥያቄዉን አጭር ማድረግም እንዲሁ በምስክሩ ላይ የበላይነትን ያስገኛል:: ጥያቄዉ ከአንድ በላይ ሃሳብ ከሌለዉ እና ርዝመቱም አጭር ከሆነ ምስክሩ ለዚሁ ብቻ መልስ እንዲሰጥ ሰለሚገደድ ብዙም መፈናፈኛ አይኖረዉም:: በተለይ ከአንድ በላይ ሃሳብ አለመያዙ ምስክሩ መርጦ የመመለስ ስራ እንዳይሰራ ያደርገዋል የመልሱ ወሰን የታጠረ ይሆናል::
ከዚህ በተያያዘ ከአንድ በላይ የሆኑ ጥያቄዎችን አነባብሮ በአንድ ጊዜ መጠየቅ የሚገኘዉን መልስ ግልጽ እንዳይሆን ያደርገዋል:: አንድ መልስ ቢሰጥ ለየትኛዉ ጥያቄ እንደተመለሰ ማወቅ አይቻልም:: ስለዚህ እንደዋና ጥያቄ ጊዜ በአንድ ጊዜ አንድ ጥያቄ ብቻ ማንሳት ተገቢ ይሆናል::