አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ላልተወሰነ ጊዜ አቋርጦት የነበረውን የብድር ውልን የማረጋገጥ አገልግሎት ነገ እንደሚጀምር አስታወቀ

የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ከሐምሌ 5 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ተቋርጠው ከነበሩ አገልግሎቶች መካከል የብድር ውልን የማረጋገጥ አገልግሎት ብቻ ከነገ ህዳር 25 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡
Consultant, Legal Services
 Terms of Reference /ToR/ for Legal Consultant to Provide Contractual Services
At
Ethiopian Charities and Societies Forum (ECSF)
www.fcsf.net

Job Requirements:

Required Qualifications and Skills

LLM in from accredited Law school

Minimum of 5 years of practical experience in providing consultancy services, particularly to civil society organizations in the legal area.

Experience in working with Ethiopian justice sector, mainly in the judiciary or legislative organs.

Experience in conducting assessments or analysis on legislative apparatuses in the Ethiopian justice sector context.

Understanding and knowledge of the Ethiopian justice sector in the overall.

Outstanding communication and research and report writing skills.

Good command of Amharic and English languages.

Genuine interest to work in civil society environment.

How To Apply:

Interested applicants can submit their CV and Motivation Letter to the Ethiopian Civil Society Organizations Forum /ECSF/ Office in Addis Ababa: Bole Sub-City, Around 22 Mazoriya, 100 mt from Awraris Hotel to the West, Next to Oasis Apartment Hotel; P. O. Box: 1270 code 100; E-mail: info@fcsf.net; Website: https://www.fcsf.net.

ECSF highly appreciated women and people with disability (PWD) to apply.

 For any further information about this announcement, call @ 0912852814 
Consultant, Legal Services

Job Description:

 Terms of Reference /ToR/ for Legal Consultant to Provide Contractual Services

ABOUT THE ECSF

The Ethiopian Civil Society Organizations Forum (ECSF is established as a non-partisan, independent, inclusive and voluntary national platform with a focus on the common concerns and challenges of the Civil Society sector in Ethiopia. The Forum’s operational scope is at federal and regional levels with a focus on legal, institutional and operational issues and processes that commonly concerned the civil society sector in Ethiopia. 

The various Networks and Consortia of Civil Society organizations (named as ‘Civil Society Organizations’ in the recently ratified Proclamation No. 1113/2019) operating at Federal and Regional level thus came together and established the) ECSF in May 2013.

Vision

ECSF envisions seeing a strong and vibrant civil society sector for sustainable development.

Mission

ECSF aspires to ensure the existence of enabling environment for civil society organizations sector through strong representation, constructive dialogue and partnership using consortiums and other legal establishments as platform for action. 

The project: Request for Applications (RFA) 1/2020 to improve citizen engagement in the legal and judicial reforms in Ethiopia

Implementing partner: Ethiopian Civil Society Organization’s Forum /ECSF/

Funding Partner: Feteh (Justice) Activity

Objectives of the project: Overall Objective: The project is aimed to enhance the ability of civil society organizations (CSOs) engagement in the legal and judicial reforms process.

JOB SUMMARY

In consultation with the ECSF Program Manager and the Legal Project Officer, the Consultant shall provide contractual based legal advisory and other consultancy services, including writing proceedings, developing short concept notes to workshops, preparing activity-based descriptive reports, forwarding practicable recommendations to specific interventions, etc…focusing on the project backed by USAID - Feteh (Justice) Activity in Ethiopia. The contract shall remain for a fixed period of months whereby it is based on certain deliverables from specific activities of the aforementioned project. 

 Major Duties and Responsibilities

Actively participated and engaged in three relevant consultation workshops on the subject of gathering inputs on the ongoing legislative processes focusing on women, people with disability, and youths.

Gather relevant information from presentations during three public consultations, and interpreted the information in a manner that could be employed to develop recommendations or implications.

Gather inputs on three draft legislations from the network of CSOs focused on women (Network of Ethiopian Women’s Association), youth (Ethiopian Youths Federation) and PWDs (Federation of Ethiopian Associations of People with Disability - FEAPD).

Develop/compile three ‘Input Reports’ on each of the draft legislation to ensure the drafts properly address the rights and constraints of women, youth and PWD and submit to ECSF.

Output/Deliverables

Verbalized three separate reports from inputs collected during consultation workshops among the three target Networks of CSOs.

Compiled three separate reports from interpreted information and presentations during the three specific public consultations. 

Compiled a reports based on the inputs collected from the three Networks of CSOs (NEWA, EYF and FEAPD) on the draft legislations.

Prepared three final ‘Input Reports’ of each of the draft legislations and submit to ECSF.
የኢትዯጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር የፌዴራል የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 1183/2012)ን
1. በአፋርኛ፣
2. በትግርኛ፣
3. በሶማሊኛ፣
4. በሲዳምኛ እና
5. በአፋን ኦሮሞ

ቋንቋዎች በመተርጎም ለተጠቃሚዎች አዘጋጅቷል። ለኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር ምስጋናችን ይደረሳቸው፤

አዋጁን በየቋንቋዎቹ ከዚህ ያግኙ

https://www.abyssinialaw.com/dds/latest-laws
በአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የደንበኞች ትምህርት ቡድን አባል አቶ ምትኩ አበባዉ ለኢትዮጵያ ቼክ ከተናገሩት ፦

- ደብዳቤዎቹ ከኛ ነዉ የወጡት፤ ትክክለኛ ናቸዉ።

- የክልከላው ምክንያት ለንግድ ማይዉሉ የግል መገልገያ ዕቃዎችን ዝርዝር ለመወሰን የወጣዉን መመሪያ 51/2010ን በመጠቀም በተመላላሽ መንገደኞች ከቀረጥ ነጻ የሚገቡ ነገር ግን ለንግድ አላማ እየዋሉ የሚገኙ ዕቃዎች በህጋዊ ነጋዴዎች ላይ ጫና በመፍጠራቸዉ ነው።

- አንድ መንገደኛ ሁሌ የሚመላለስ ከሆነ ያለቀረጥ ሁሌም እየተመላለሰ የሚያመጣ ከሆነ በህጋዊ መልኩ በኮንቴነር የሚያስጭኑና ግብር የሚከፍሉ ነጋዴዎችን ኪሳራ ዉስጥ የሚያስገባና ተጽዕኖ የሚያሳድር በመሆኑ ይህ ደብዳቤ ወጥቷል።

- ማንኛዉም መንገደኛ ማንኛዉንም አልባሳት ሆነ የንግድ ባህሪ ያለዉ ዕቃ ይዞ ከመጣ ቀረጥና ታክስ መክፈሉ እንደተጠበቀ ሆኖ በወንጀል ምርመራ ህግም እስከ ማስጠየቅ ድረስ የሚደርስ ነዉ።

- ከአንድ ወር በላይ የቆዩና ተመላላሽ ያልሆኑ የመጀመሪያ መንገደኞች፤ ቱሪስቶች እና ዲፕሎማቶች ፓስፖርታቸዉና ማህደራቸዉ ታይቶ የንግድ ባህሪ የሌለዉ ዕቃ የያዙ ከሆነ ለጊዜዉ በመመሪያ 51/2010 መሰረት የሚስተናገዱ ይሆናል።

- ጠቅልለዉ ወደ ሀገር የሚመለሱ መንገደኞች ጓዞቻቸዉን ይዘዉ ቢመጡም ሆነ በካርጎ ቢልኩ በመመሪያ 51/2010 የተፈቀደና ሲገለገሉበት የቆየ ዕቃ ከሆነ ከቀረጥ ነጻ ማስገባት ይችላሉ። ይሁን እንጂ በመመሪያዉ ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ የተፈቀዱ ቢሆኑም ዕቃዎቹ አዳዲስ እስከሆኑ ድረስ ቀረጥና ታክስ ይከፈልባቸዋል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/ETHIOPIA-12-06

@tikvahethiopia
ካርታ ማምከን/የይዞታ ማረጋገጫ መሰረዝ/
===================
የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ማረጋገጫ ማስረጃ /ደብተር ወይም
ካርታ/ በመሰረዝ ዋጋ ማሳጣት
አንድ የአስተዳደር አካል የቤት ባለቤትነት ማስረጃ በፈለገው ጊዜ ከሕግ ውጪ
እንዲሰረዝ ማስቻል በኢ.ፌ.ዲ. ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 40/1/ እና /2/
ድንጋጌ ሥር የተከበረውን የንብረት ባለቤትነት መብት ዋጋ የሚያሣጣው ነው፡፡
የፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1195 እና 1196 ድንጋጌዎች አንድ ላይ ሲነበቡም
የአስተዳደር አካል በባለቤት ማረጋገጫ ማስረጃ አሰጣጥ ላይ ፍጽም የሆነ
አስተዳደራዊ ስልጣን ያለው ስለመሆኑ አያሣዩም፡፡ ይልቁንም ድንጋጌዎች
እርስ በእርሣቸውም ሆነ ከፍ/ሕ/ቁጥር 1198 ድንጋጌ ጋር ተዛምደው ሲታዩ
የባለቤት ማረጋገጫ ደብተር የሚሰረዘው በሕጉ በተመለከቱት ምክንያቶች
ብቻ መሆኑን ከሕጉ ውጪ ተግባሩ ተከናውኖ ከተገኘም መብቱ የተነካው ሠው
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 37፣78 እና 79 ድንጋጌዎች መሠረት
ጉዳዩን ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት አቅርቦ አቤቱታው እንዲታይለት
የሚያርግበት ጉዳይ እንጂ አስተዳደር አካሉ የሰጠው ውሣኔ በፍርድ ቤት
እንዳይታይ የሚገደብበት ስርዓት የሌለ መሆኑን የምንገነዘበው ነው፡፡
ከጥቂት ዓመታት ወዲህ የባለቤትነት ማረጋገጫ የመስጠት ስልጣን ያላቸው
አካላት ‘ካርታ ማምከን’ የሚሉት አዲስ ፈሊጥ አምጥተዋል፡፡ ፍርድ ቤቶችም
ቃሉን በተውሶ እያዘወተሩት ወደ ህግ ቃል እየቀየሩት ነው፡፡ ይህ የማምከን
እርምጃ እስከ 2005 ዓ.ም. ድረስ በተደጋገሚ ሲስተዋል የነበረ አሳዛኝ ክስተት
ነው፡፡ ህገ መንግስታዊ ንብረት የማፍራት መብትን አደጋ ውስጥ የከተተው
‘ከመሬት ተነስቶ’ ካርታ የማምከን ተግባር በቅርብ ሆኖ የሚቆጣጠረው
በመጥፋቱ የተነሳ አስተዳደሩ ከህገ ወጥነት ወደ ጋጠ ወጥነት ተሸጋግሯል፡፡
በአስረጂነት ከሚጠቀሱ የሰበር ችሎት መዝገቦች መካከል የሰ/መ/ቁ
17712 አንደኛው ነው፡፡ በዚህ መዝገብ አመልካች ሆኖ የቀረበው የአዲስ
አበባ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ሲሆን ተጠሪ የወሮ ሳድያ እስማኤል ወራሾች
ናቸው፡፡ የጉዳዩ አመጣጥና በሰበር የተሰጠው ውሳኔ በአጭሩ እንዲህ
ይተረካል፡፡
ክርክሩ የተጀመረው በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሲሆን ተጠሪዎች
በውርስ የተላለፉላቸው በአዲስ አበባ የሚገኙ ሁለት የንግድ ቤቶችን
ተከራይተው የሚሰሩባቸው ግለሰብ ቤቶቹን እንዲያስረክቧቸውና ያልተከፈለ
ኪራይም እንዲከፍሉ በማለት ክስ ያቀርባሉ፡፡ ፍርድ ቤቱም መብታቸውን
በማረጋገጥ ወሰነላቸው፡፡ ከውሳኔ በኋላ የአዲስ አበባ መስተዳደር ቤቶቹ
በአዋጅ ቁጥር 47/67 የተወረሱና ከዚህ ቀደም ተሰጥቶ የነበረው
የባለቤትነት ደብተር በአዲስ አበባ አስተዳደር ሥራና ከተማ ልማት ቢሮ
የቤቶች ጉዳይ መምሪያ የተሰረዘ መሆኑን በመግለፅ በክርክሩ ውስጥ
በተቃውሞ ገብቶ የባለቤትነት ጥያቄ ያነሳል፡፡
ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ እና በይግባኝ ያዩት የስር ፍ/ቤቶች ‘ቤቶቹ
ስለመወረሳቸው የሚያረጋግጥ የመረካከቢያ ቅፅ አልቀረበም’ በሚል
የአስተዳደሩን ጥያቄ ውድቅ አደረጉት፡፡ አስተዳደሩ የሥር ፍርድ ውሳኔዎች
መሠረታዊ የሕግ ስህተት ስላለባቸው ይታረምልኝ በማለት የሰበር አቤቱታ
በማቅረቡ የሰበር ችሎት የሚከተለውን ውሳኔ በድምፅ ብልጫ ሰጠ፡፡
በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1195 ንዑስ አንቀፅ 1 ላይ በግልፅ
እንደተመለከተው የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሃብትነትን በማወቅ በአስተዳደር
ክፍል ለአንድ ሰው የተሰጠ የባለሃብትነት የምስክር ወረቀት ማስረጃ
ለተሰጠው ሰው ለዚሁ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሃብት እንደሆነ
እንደሚያስቆጥረው ተመልክቷል፡፡ በአንፃሩ ማስረጃው የተሰጠው ከደንብ
ውጭ በሆነ አሰራር መሆኑ በተረጋገጠ ጊዜ ከፍ ብሎ በፍትሐብሔር ቁጥር
1195 ላይ የተመለከተው የሕሊና ግምት ፈራሸ እንደሚሆን የፍትሐብሔር ሕግ
ቁጥር 1196 (1) ይደነግጋል፡፡ በያዝነው ጉዳይ በሕግ አግባብ ስልጣን
ተሰጥቶት ይህን መሰሉን የባለሃብትነት ማስረጃ የሚሰጠው ክፍል ቁጥር
5127386 የሆነው የባለሃብትነት የምስክር ወረቀት የሰረዘው መሆኑ
ተረጋግጧል፡፡ በተሰረዘ የባለሃብትነት ምስክር ወረቀት ደግሞ የሚገኝ
የባለሃብትነት መብት አይኖርም፡፡ የተጠሪ ወራሾችም አውራሻቸው
ያልነበራቸውን መብት ሊወርሱ አይችሉም፡፡
ለንፅፅር እንዲረዳ በሓሳብ ልዩነት የተሰጠውን አስተያየትና ምክንያት ማየቱ
ተገቢ ነው፡፡
አመልካች የአዲስ አበባ መስተዳደር በቤቶቹ ላይ መብት አለኝ የሚለው
በመንግስት የተወረሱ ናቸው በሚል መሆኑን መዝገቡ ያስረዳል፡፡ ይሁን እንጂ
ቤቶቹ በመንግስት የተወረሱ መሆናቸውን የሚያሳይለት ማስረጃ አላቀረበም፡፡
ለተጠሪዎች አውራሸ ተሰጥቶ የነበረው የባለቤትነት ደብተር ተሰርዟል ማለቱ
ብቻውን ለእርሱ መብት የሚሰጠውና አቤቱታውም በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 358
አግባብ እንዲሰተናገድለት ለማድረግ የሚያስችል አይደለም፡፡ በኔ እምነት
የሥር ፍርድ ቤቶች ወደ ዋናው ጉዳይ ተመልሰው ክርክሩን እንደገና
መመርመር ሳያስፈልጋቸው አመልካቹን ወደ ክርክሩ ለመግባት የሚያስችልህ
መብት መኖሩን አላስረዳህም በሚል ከወዲሁ ጥያቄውን ውድቅ ማድረጋቸው
የፈፀሙት የሕግ ስህተት የለም፡፡
የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1195 ግምት በፍ/ሕ/ቁ 1196 በተደነገገው
መሠረት ማለትም በሕጉ መሠረት ፈራሸ ሊሆን ይችላል፡፡ የባለቤትነት ካርታው
ከደንብ ውጭ የተሰጠ ከሆነ መሰረዙን ህግ ይፈቅዳል፡፡ ሆኖም የመሰረዝ
ስልጣን ያለው አካል የካርታው አሰጣጥ ከደንብ ውጭ ስለመሆኑ የማስረዳት
ግዴታውን ሊወጣ ይገባል፡፡ የአዲስ አበባ መስተዳደር ሥራና ከተማ ልማት
ቢሮ የቤቶች ጉዳይ መምሪያ ካርታውን ሲሰርዝ ካርታው ከደንብ ውጭ የተሰጠ
መሆኑን የማሳየትና የማስረዳት ግዴታ አለበት፡፡ ይህን ካላደረገ እርምጃው
ከሥልጣን በላይ እንደመሆኑ በሕግ ፊት ዋጋ አይኖረውም፡፡ አመልካች
ካርታው ከደንብ ውጭ ስለመሆኑ ወይም ቤቱ በአዋጅ ስለመወረሱ በክርክሩ
ቢጠቅስም ከአባባል ያለፈ በተጨባጭ ማስረዳት አልቻለም፡፡ ስለሆነም
የመሰረዝ ድርጊቱ የሕጋዊነት መርህን የሚጥስ፣ የሕግ የበላይነትን የሚጻረር፣
ከሥልጣን በላይ የሆነ ድርጊት ነው፡፡
የአብላጫው ድምፅ ይህን መሠረታዊ ጭብጥ አላነሳውም፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ ካርታው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1196 (1) መሠረት ተሰርዞ
በምትኩ ለሌላ 3ኛ ወገን ሲተላለፍ ያ ሶስተኛ ወገን የቤቱ ሕጋዊ ባለቤት
ስለመሆኑ መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ የአዲስ አበባ መስተዳድር ባለቤትነቱ
የተሰረዘውን የንግድ ቤት የራሱ ሃብት ሲያደርገው በሕጉ መሠረት የባለቤትነት
መብት የተሰጠው መሆኑን ማረጋገጥ አለበት፡፡ በአዋጅ ቁ 47/67 ተወርሷል
የሚል ከሆነ እንደተወረሰ በበቂ ማስረጃ ማሳየት አለበት፡፡ አመልካች የቤቱ
ባለቤት ስለመሆኑ አሁንም በአብላጫው ድምፅ ላይ ጭብጥ ሆኖ ተነስቶ
ድምዳሜ ላይ አልተደረሰበትም፡፡ በእርግጥ በተሰረዘ የባለሀብትነት የምስክር
ወረቀት የሚገኝ የባለሀብትነት መብት አይኖርም፡፡ ከዚህ ድምዳሜ በፊት ግን
የህግ የበላይነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት አለበት፡፡
ተጠሪዎች እየሞገቱ ያሉት የመሰረዙን ሕጋዊነት ነው፡፡ የተጠሪዎች ሙግት
በአብላጫው ድምፅ ሰሚ አላገኘም፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር
ካርታው ከደንብ ውጭ ለአመልካች እንደተሰጠ ስላላስረዳ ድርጊቱ ሕገ ወጥ
ወይም ከሥልጣን በላይ ነው፡፡ በቤቱ ላይ በሕጉ መሠረት ባለቤት እንደሆነ
ስላላስረዳም ‘ከመሬት ተነስቶ በሌላ ሰው መብት ባለቤትነት ሊኖረው
አይችልም፡፡ ይህን ሀሳብ በአነስተኛ ድምፅ አስተያየት ስንቋጨው፤
አመልካች እንኳንስ መብት ሊኖረው ቀድሞውኑ በተቃውሞ ወደ ክርክር
ውስጥ እንዲገባ ሊፈቀድለት አይገባም ነበር፡፡
በሌላ ተመሳሳይ መዝገብ እንዲሁ ፍርድ ያረፈበት የባለቤትነት መብት
አስተዳደሩ ስላመከነው መና ሆነ ቀርቷል፡፡ በሰ/መ/ቁ. 22719[1] ተጠሪ
በሁለት የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር /ካርታ/ የተመዘገቡ ሶስት የቤት
ቁጥር የተሰጣቸው ቤቶች የራሳቸው መሆናቸው ተረጋግጦ በፍርድ ቤት ውሳኔ
አርፎባቸው በአፈጻጸም መዝገብ ቤቶቹን ተረክበዋል፡፡ የፍርድ ሂደቱ
እንደተጠናቀቀ አመልካች የቤት ማረጋገጫ ደብተሮቹን በመሰረዙ ተጠሪ ክስ
አቀረቡ፡፡ በሰበር ችሎት በነበረው ክርክር ችሎቱ ተጠሪ መብታቸውን በፍርድ
ቤት አስከብረውና አረጋግጠው የተፈጸመባቸው ዓይን ያወጣ ህገ ወጥ ተግባር
ከማረምና የህግ የበላይነትን ከማስከበር ይልቅ ክስ የማቅረብ መብታቸውን
ነፍጓቸዋል፡፡ ችሎቱ ለማመዛን እንደሞከረው፡
አመልካች የተጠሪን የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነዶች ከሰረዘ ተጠሪ አስቀድሞ
በተጠቀሱት ቤቶች ላይ ባለመብት መሆኑን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎችን
በእጁ ማስገባት ይኖርበታል፡፡ ይህ መሠረታዊ ማረጋገጫ ሰነድ ወይም
ማስረጃ ሳይኖረው ፍ/ቤት ሰነድ እንዲሰጠው እንዲወሰንለት መጠየቅ
አይቻልም፡፡
በአጭር አነጋገር ቤቱን በአስተዳደሩ ህገ ወጥ ተግባር የተነጠቀ ሰው ቤቱ
እንዲመለስለት የመጠየቅ መብት እንኳን የለውም፡፡
የሰበር ችሎት ዘግይቶም ቢሆን የሰ/መ/ቁ 17712 እና 22719 ውሳኔ ካገኙ
ከሰባትና አምስት ዓመታት በኋላ ፍጹማዊ በሆነውና ፍጹማዊነቱንም ችሎቱ
ይሁንታ በሰጠው የአስተዳደሩ ካርታ የማምከን ስልጣን ላይ ገደብ ለማበጀት
ተገዷል፡፡ በሰ/መ/ቁ. 42501[2] ፍርድ ባረፈበት ጉዳይ ካርታ ማምከን ህገ
ወጥነቱን ጠንከር ባሉ ቃላት እንደሚከተለው ገስጾታል፡፡
አንድ የአስተዳደር አካል በፍርድ ቤት ክርክር መረታቱን ከተረዳ በኃላ በሕጉ
የተሰጠውን ስልጣን መነሻ በማድረግ ለፍርዱ መሰጠት መሠረት የሆነውን
ማስረጃ ዋጋ በማሣጣቱ ምክንያት የፍርድ አፈፃፀም ዋጋ እንዲያጣ የማድረግ
ውጤት በኢ.ፊ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 78/1/ እና 79/1/ እና /4/
ስር የተረጋገጠውንና የተከበረውን የነፃ ፍርድ ቤት መኖርንና የዳኝነት ስልጣን
ትርጉም አልባ የሚያደርገው ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 42501 ቅጽ 15፣ ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 37፣ 38፣
79፣ ፍ/ህ/ቁ. 1195፣ 1196፣ 1198
አስተዳደራዊ ተቋማት በሕግ ተለይቶ በተሰጣቸው ጉዳይ የመወሰን ሥልጣን
እንዳላቸው የታወቀ ነው፡፡ ይሁንና ለአንድ ባለ ጉዳይ የተሰጠው ካርታ
የተሰጠበት እና የተሻረበት አግባብ በሕግ አግባብ መሆን ያለመሆኑን አጣርቶ
የመወሰን ሥልጣን የፍርድ ቤቶች ነው፡፡ በዚህ ረገድ አንድ ፍርድ ቤት
የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታን የመሰረዝ ሥልጣን የአስተዳደር ክፍል ነው፣
ፍርድ ቤት ጉዳዩን አይቶ የመወሰን ሥልጣን የለውም በማለት የሚደርስበት
ድምዳሜ የጉዳዩን የክርክር ባህሪ እና ይዘት ያላገናዘበ ነው፡፡ ፍርድ ቤቶች
በአስተዳደር ክፍል የተሰጠው ካርታ የተሰጠበት ወይም የተሻረበት ሥርዓት እና
አስተዳደራዊ ውሳኔው ሕግና መመሪያ ያገናዘበ መሆን ያለመሆኑን በማጣራት
ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን እንዳላቸው ከፍ/ህ/ቁ. 1196 እና በህገ
መንግስቱ ስለ ንብረት መብት ከአደረገው ድንጋጌና በፍርድ የሚያልቁ
ጉዳዮችን በተመለከተ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 37 ከተመለከቱት ድንጋጌዎች
ይዘት የምንረዳው ጉዳይ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ 99071 ቅጽ 18፣ ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 37፣ ፍ/ህ/ቁ. 1196
ከቴምብር ቀረጥ ነፃ የመሆን መብት /Stamp Duty Exemption/
-------------------------------------

1. የቴምብር ቀረጥ ምንነት እና ዓላማዉ
መንግስት ገቢ ከሚሰበስብባቸዉ ምንጮች መካከል የቴምብር ቀረጥ አንዱ ነዉ፡፡ የቴምብር ቀረጥ ቀጥተኛ ያልሆነ ታክስ ሲሆን የሚሰበሰበዉም በተወሰኑ ሰነዶች ላይ እንዲለጠፍ ወይም እንዲከፈል በማድረግ ነዉ፡፡ በሀገራችን ኢትጵያ የቴምብር ቀረጥ የተጣለዉ ከንጉሱ ዘመን ጀምሮ በወጡ የቴምብር ቀረጥ አዋጅና ደንብ (አዋጅ ቁጥር 334/1979 ዓም እና በቴምብር ቀረጥ ደንብ ቁጥር 221/ 1951 ዓ.ም) ሲሆን አሁን በሥራ ላይ ያለዉ የቴምብር ቀረጥ አከፋፈል አዋጅ 110/1990 ዓ.ም ነዉ፡፡ የቴምብር ቀረጥ የመንግስት አንዱ የገቢ ምንጭ ከመሆኑ ባሻገር በሰነዶች ላይ የተለያዩ የስራ ዘርፎችን የኪነ-ጥበብ ዕድገትን፣ የፋይናንስ ተቋሞችን እንቅስቃሴ እና የካፒታል ንብረት ዝዉዉርን ለማገዝ የሚያስችል እና የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልባቸዉን ሰነዶችና ከቴምብር ቀረጥ ነፃ ስለመሆን የሚለዉን ለይቶ የማሳወቅ እና ሌሎች አለማወችን ያገናዘበ ነዉ፡፡

የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልባቸዉ እና የማይከፈልባቸዉ ግብይቶች
የቴምብር ቀረጥ በሰነዶች ላይ የሚጣል ታክስ ቢሆንም ሁሉም ሰነዶች ላይ የሚጣል አይደለም፡፡ አዋጁ በአንቀጽ 3 የተለያዩ ሰነዶችን በመዘርዘር የሚከፈልበትን ጊዜ፣ሁኔታና መጠን በግልጽ አመልክቷል፡፡ የቀረጥ ቴምብር የሚከፈለዉ የመንኛዉም ንግድ ማኅበር፣የኅብረት ሥራ ማኅበር ወይም የማኝኛዉም ዓይነት ማኅበር መመሥረቻና መተዳደሪያ ደንብ፤የግልግል ሰነድ፤ ማገቻ፤ የዕቃ ማከማቻ ማረጋገጫ ሰነድ፤ ዉል ስምምነትና የእነዚህ መግለጫ፤የመያዣ ሰነዶች፤የኅብረት ስምምነት፤ የሥራ (ቅጥር) ዉል፤የኪራይ፣የተከራይ አከራይና መሰል መብት የማስተላለፊያ ሰነዶች፤ ማረጋገጫ፣ የዉክልና ሥልጣን እና የንብረት ባለቤትነትን ማስመዝገቢያ ሰነድ ላይ ነዉ፡፡ ከእነዚህ ሰነዶች ዉጭ ባሉ ሰነዶች ላይ የቴምብር ቀረጥ አይከፈልም፡፡ የአዋጁ ዝርዝር ምሉዕ / Exhaustive / በመሆኑ በማመሳሰል / Analogy / ሌሎች ያልተጠቀሱ ( ያልተዘረዘሩ) ሰነዶች ላይ የቴምብር ቀረጥ እንዲለጠፍ ወይም እንዲከፈል መጠየቅ የሚቻል አይደለም፡፡

2. ከቀረጥ ነፃ ስለ መሆን
የቴምብር ቀረጥ አዋጁ ከቀረጥ ነፃ የመሆን መብትን በአንቀጽ 11 ደንግጓል፡፡ ድንጋጌዉ ከቴምብር ቀረጥ ነፃ የሆኑትን ( የቴምብር ነፃ መብት ተጠቃሚዎችን) የዘረዘረ ሲሆን የአትዮጵያ ፌደራላዊ መንግሰት የፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 57/1989 ዓ.ም ተፈፃሚ የሚሆንባቸዉ የመንግስት መሥሪያ ቤቶች፣የአስመጭነት የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸዉ ነጋዴዎች ለሽያጭ የሚያስመጡት ንብረት በአስመጭዎቹ ስም በሚመዘገቡበት ጊዜ፣ በዓለም አቀፍ ስምምነቶች ተጠቃሚ የሆኑ፣ ተመሳሳይ መብት የሚሰጡ ኤምባሴዎችና የአክስዮን ድርሻ የምስክር ወረቀት ሲመዘገብ ከቴምብር ቀረጥ ነፃ የመሆን መብት ይኖራቸዋል፡፡ ባንኮች ለ3ኛ ወገን በሚሰጧቸዉ ቦነዶች / Bid Bond, Performance Bond / ላይ የቴምብር ቀረጥ አይከፍሉም፡፡በተጨማሪም ኢንበስተሮች (ባለሀብቶች) ከኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ ከባንኮች ብድር ሲወስዱ ከቀረጥ ቴምብር ነፃ እንዲሆኑ ተፈቅዷል፡፡

ይህ የሆነዉም ኢነቨስትምንትን ለማበረታት ሲባል ነዉ፡፡ እንዲሁም በአዋጅ ቁጥር 867/07 አንቀጽ 4 መሠረት ከሚወጡት የመንግስት የዕዳ ሰነዶች ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ወይም ሰነዶች ላይ የቴምብር ቀረጥ አይከፈልባቸዉም፡፡ ሌሎችን ደግሞ የገንዘብ ሚኒሰቴር በቂ ምክንያት ሲቀርብለት ከቴምብር ቀረጥ ነፃ ሊያደርግ እንደሚችል ገልጿል፡፡ ይህን ለማስፈፀም በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 7/1988 ዓ.ም እና በፌዴራል ገቢዎች ሚኒስቴር በቁጥር 01/1/9/11/33/3 በቀን 24/02/ 1997 የወጣዉን መመሪያ ይመለከቷል፡፡ የኢንቨስትመንት ኤጀንሲ በቁጥር ኢዲክ9/ኢጠ/1/662 በቀን 22/03/1999 ዓ.ም ማብራሪያ ይህንኑ በግልጽ ያስቀምጣል፡፡

3. ከቴምብር ነፃ ማበረታቻ ከሌሎች ማበረታቻዎች በምን ይለያል
ከቀረጥ ቴምብር ነፃ መሆን ማበረታቻ ከሌሎች ማበረታቻዎች በተለይም ከጉምሩክ ቀረጥ ነፃ እና ከገቢ ግብር ማበረታቻ የሚለየዉ በመመሪያ የተሰጠ መብት በመኖሩ፣ የቴምብር ቀረጡ የሚከፈልበት ጊዜና ሁኔታ የተገለጸ በመሆኑ እና ዝርዝር የመብቱ አጠቃቀም መብቱ የሚጀምርበትና የሚጠናቀቅበት ጊዜ ግን በግልጽ ባለመመልከቱ ነዉ፡፡

4. የቴምብር ቀረጥ አለመከፈል የሚያስከትለዉ ዉጤት
ይህ ጉዳይ በአዋጁ አንቀጽ 10 ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ የቴምብር ቀረጥ በአዋጁ አንቀጽ 12 በተጠቀሰዉ መሠረት በወንጀል ከማስቀጣቱ በተጨማሪ የሚከተሉት ዉጤቶች አሉት፡-
 ማንኛዉም ሰነድ በቴምብር አዋጁ መሰረት ትክክለኛ የተምብር ቀረጥ ካልተከፈለበት በስተቀር በዉል ወይም በሕግ ማስረጃ የመቀበል ሥልጣን ባለዉ ሰዉ ወይም የመንግስት መስሪያቤት ዘንድ በማስረጃነት ተቀባይነት አይኖረዉም፣ ምልክት አይደረግበትም ወይም ማረጋገጫ አይሰጥበትም፡፡
 በአዋጁ መሠረት በመረጃነት ያላገኙ ሰነዶች ሊከፈልባቸዉ የሚገባዉ ቀረጥ በሁለት እጥፍ ተከፍሎባቸዉ በመረጃነት ሊቀርቡ ይችላሉ፡፡ በዚህ ሁኔታ የሚከፈለዉ ቀረጥ ከ ፲ ብር ( አስር ብር) ማነስ የለበትም፡፡
 ዉጤቱ በወንጀል ፍርድ ቤት በሚታይ ክርክር በማስረጃነት የሚቀርቡ ሰነዶችን አይመለከትም፡፡
በአጠቃላይ የቴምብር ቀረጥ አዋጅ 110/1990 ዓ.ም መሠረት ቢሆንም በአንዳንድ ጉዳዮች በተለይም ይግባኝን በተመለከተ በቴምብር ቀረጥ መሻሻያ አዋጅ ቁጥር 612/2001 ዓ.ም ማሻሻያ የተደረገበት መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡ ሌላዉ ጉዳይ በቴምብር ሕጉ አና አተገባበሩ ላይ የተወሰነ ክፍተት የሚታይበት በመሆኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጣና መሰጠት ቢቻል ለዉጥ ይመጣል የሚል ነዉ፡፡
Forwarded from All African/Andinet
Great call from Pm Abiy Ahmed 🇪🇹💚💛❤️

Yes , we Africans ask for a permanent seat and voice at UNSC ASAP .

Wake up Africa 🌎💪🏻
#PanAfricanismPrevails
#BBCfakenews
#WeStandTogether
#PermanentseatforAfricaUNSC
#AfricanUnite
የቱ ነው ልክ ?
ዳኛው የተለመደ ተግባራቸውን ለማከናወን ተቀምጠዋል ፤ ከእርሳቸው አጠገብ በስተቀኝ በኩል ችሎት ጸሐፊያቸው አለ። ከፊት ለፊታቸው ደግሞ ሁለት ሰዎች ቆመዋል፤ ከሳሽና ተከሳሽ ። ዳኛው ቅድሚያ ለከሳሽ እድል በመስጠት ጉዳዩን እንዲያስረዳ ጋበዙት ።ከሳሽም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻው ክሱን በዝርዝር አቀረበ ። ዳኛውም " ይገርማል ያልከው ሁሉ ልክ ነው " አሉና
በቀጣይ መልስ እንዲሰጥበት ተከሳሽን ጋበዙት። ተከሳሽም የተከሰሰው ያለአግባብ መሆኑን በመጥቀስ ክሱን አስተባብሎ በመናገር ጉዳዩን አስረዳ ። አሁንም ዳኛው በመገረም " ይገርማል፤ እጅግ በጣም ይገርማል ልክ ነህ ወዳጄ ፤ ያልከው ነገር ሁሉ ልክ ነው " አሉት ። ይኼኔ ዳኛው ግራቀኙን (ከሳሽንና ተከሳሽን ) ልክ ናችሁ በማለታቸው ግራ የተጋባው ችሎት ጸሓፊያቸው በድንገት ብድግ ይልና " ክቡር ዳኛ እንዴት ነው ነገሩ ? ከሳሽ የተናገረውም ልክ ከሆነ ተከሳሽ የተናገረውም ልክ ከሆነ ጥፋተኛ ማን ሊሆን ነው ? እንዴትስ ሆኖ ነው አንዱ ተበደልኩ ሌላው አልበደልኩም እያለ ሁለቱም ልክ የሚሆኑት ? እኔ ይኼ ነገር አልገባኝም " አለ። ዳኛው ወደ ጸሓፊያቸው እያዩ " ይገርማል አንተም ልክ ነህ " አሉት ይባላል።
ሸንበቆ " አቋምህ ምንድን ነው ?" ተብሎ ሲጠየቅ " ንፋስን ጠይቁት " አለ ይባላል ። እንደ ሸንበቆ አቋማቸው በሚነፍሰው ጊዜያዊ ነፋስ ላይ ብቻ የሚወሰንባቸው ብዙ ሰዎች አሉ ።በራሳቸው ልብ የማያስቡ ፣ በራሳቸው ህሊና የማይበይኑ ፤ ሁሉን እንደየስሜቱና እንደየፈቃዱ የሚዳኙ ፣ ከሁሉ ጋር መስሎና ተመሳስሎ ሕሊናን ሽጦ መኖር የለመዱ በርካቶች አሉ።
እንዲህ ያሉት ናቸው ዛሬ ፍትህ ሲጠፋ ፍርድ ሲጓደል ድሀ ሲበደል ሕዝብ በሌቦች ሲበዘበዝ እያዩ በተሰጣቸው የማስተዳደር ስልጣን ተጠቅመው ማስከበር እየቻሉ ሁሉን ሳያስቀይሙ ለመኖርና የግል ጥቅማቸውን ብቻ ለማስከበር ሲሉ እናንተም እነሱም ያነሳችሁት ጥያቄና ሐሳብ ትክክል ነው ሁለታችሁም ትክክል ናችሁ ተስማሙ እያሉ ብርሃንን ከጨለማ ጋር ሊደምሩ የሚተጉት።
እውነትን እንድፈር እውነትን ተናግረናት ከመሸብን እንደር።
እውነተኛ መሆን ማለት እውነትን በሚጠሉ ሰዎች መገፋት መጠላት ብሎም መሞት ነው።
በስዩም ይዘንጋው
Internship (Law)

Ethiopian Women Lawyers Ass...

Addis Ababa

About EWLA: The Ethiopian Women Lawyers Association (EWLA) is a not-for-profit Civil Society Organization (CSO) founded by Ethiopian women lawyers. It began its work in 1996 after being registered in 1995. It was re-registered as a charitable organization by the Charities and Societies Agency in 2010 as per the Charities and Societies Proclamation No.1113/2019. Its vision is to see a country where women are equal to men. It also has the mission of promoting the economic, political, social, and legal rights of women and, to that end, assisting them to secure full protection of their rights under the Constitution of the Federal Democratic Republic of Ethiopia and other international human rights conventions. Since its establishment, EWLA has been working to achieve this vision and mission. EWLA has eight branch offices in Adama (Oromia Regional State), Bahir Dar (Amhara Regional State), Hawassa (SNNPRS), Asossa (Benishangul Gumuz Regional State), Gambella (Gambella Regional State), Dire Dawa City Administration, Jigjiga (Somali Regional State) and Semera (Afar Regional State). The Association has 54 volunteer committees that work at the zonal and woreda levels. The core program areas of EWLA include: Free Legal Aid Service, Public Education and Capacity Building, Research and Advocacy. Duties and Responsibilities: Assist and support project team members in completing the project Provide technical and logistic support including the scheduling of activities implementation, monitoring and evaluation and reporting Facilitate trainings, workshops and events Perform any other duties as required by the program manager and program coordinator Prepare and submit activity plan and implementation reports And other responsibilities as per the job description of the organization Location/Place of work: Addis Ababa, Head Office of Ethiopian Woman Lawyers Association located at Kirkos Sub-city, around Africa Union behind St. Michael Church Duration: 6 months with possibility of Extension Number required: 2 Educational Requirements: Law back ground Applicants are expected to fulfill the next criteria. Graduate from Faculty of Law and Accounting & Finance of a recognized university Passionate to serve women seeking legal aid service Possible exposure to project coordination experience will be a plus Female applicants encouraged for the position Required Experience: Entry Level (Fresh Graduate
2 Interns (Law)


Ethiopian Women Lawyers Association(EWLA)

JOB DETAILS: Duties and Responsibilities: • Assist and support project team members in completing the project • Provide technical and logistic support including the scheduling of activities implementation, monitoring and evaluation and reporting • Facilitate trainings, workshops and events • Perform any other duties as required by the program manager and program coordinator • Prepare and submit activity plan and implementation reports • And other responsibilities as per the job description of the organization • Location/Place of work: Addis Ababa, Head Office of Ethiopian Woman Lawyers Association located at Kirkos Sub-city, around Africa Union behind St. Michael Church Job Requirements • Law back ground Applicants are expected to fulfill the next criteria. • Graduate from Faculty of Law and Accounting & Finance of a recognized university • Passionate to serve women seeking legal aid service • Possible exposure to project coordination experience will be a plus • Female applicants encouraged for the position Job Experience: No Requirements Work Hours: 8 Level of Education: Bachelor Degree
አዲስ ፓስፖርት ማውጣት እንዲሁም ነባር ለማደስ ለምትፈልጉ በአካል መምጣት ሳይጠበቅባችሁ online እናመለክታለን ቀጠሮ እናሰጣለን።
https://t.me/casemanagers
https://t.me/casemanagers
https://t.me/casemanagers
New vacancy❗️👇👇👇
Internal/External

Reference No:  REC/ 105 /21
Job title:  Legal Advisor
Location:  Addis Ababa with travels to the field sites
Reports to:Systems Director
Closing date: December 19, 2021

About GOAL
GOAL is an Irish international humanitarian organization founded in 1977 and currently operational in 13 countries[1]; in both protracted crisis

and long-term development contexts. GOAL has four programmatic foci: people survive crisis; people have resilient health; people have food and nutrition security; and people have sustainable livelihoods.

Globally, GOAL’s systems approach guides our partnerships to create shared value and promote inclusive growth by linking communities, government, business, and civil society. These initiatives blend social and economic objectives, strengthening the bottom line whilst contributing to social, economic, and environmental outcomes for society. Partnering with the permanent players i.e., government, community & civil society and the private sector is key to improving the systems in which the people we work for live. GOAL works with corporate players to leverage; technology and skills, financial and business development service; and Micro, Small & Medium Enterprises (MSMEs) to increase access to goods and services and economic opportunities for poor people.

GENERAL DESCRIPTION OF THE ROLE

The Legal Advisor is responsible for providing accurate and timely legal advice to the organisation and its management on a variety of legal matters including but not limited to, Labour and Employment, Tax directives and government related guidelines, Immigration, Finance, Supplies, Service & Works contracts, and general operations. Responsibilities include conducting legal analysis and researching and evaluating different risk factors and offering proactive advice on possible legal issues. S/he must also know how to apply the law to the organisation’s circumstances. The Legal Advisor will maintain the country knowledge of laws and provide clarification on legal language and advise the organisation and its management accordingly. The Legal Advisor will regularly monitor and ensure the organisation’s compliance with local laws. In addition, this role will be responsible for handling the organisation’s legal responsibilities, organizing court order responses, preparing and review of contracts and documentation as well as providing a variety of legal support. The Legal Advisor will be delegated by the Country Director to legally represent on behalf of the organisation and expect to perform his/her duty with integrity complying with the rules and regulation of the country and organisation code of conduct policy.

KEY AREAS OF ACCOUNTABILITY/DUTIES:

·         Keeping up with current changes on all relevant areas of laws and contributing to the enhancement of the knowledge base of the organisation’s legal function

·         To conduct legal analysis and research on various legal matters of the organisation

·         To provide advice on different legal issues and assist in drafting legal opinions, memoranda, and other briefing documents

·         To be actively involved in preparing and drafting of different acts and legal submissions and draft the authoritative legal opinions as well

·         To conduct legal research by utilizing various resources and selecting the relevant material to analyze the legal information

·         To assist in reviewing the legal material and any other relevant documents and to identify the most important issues that need to be sorted out on a priority basis

·         To draw up formalities regarding the settlement of disputes and monitor the implementation of the legal clauses

·         Provide monthly legal reports and status to the Country Director and Systems Director
·         Give accurate and timely counsel to the organisation and management in a variety of legal topics not limited to, Labour Laws, Tax regulation, Data Protection, Employment, Immigration, Finance, Supplies, Service & Works contracts, and overall organisation’s operation

·         Research and evaluate different risk factors regarding business decisions and operations and apply effective risk management techniques and offer proactive advice on possible legal issues

·         Maintain current knowledge of alterations in legislation

Serve as liaison between the organisation and external attorneys.

Document and maintain legal files and issues.

High quality advice to the organisation and management on major legal issues and problems

·         S/he is responsible for formulating the best possible legal solution after analyzing the legal problem in depth.

·         S/he should be able to provide the much-needed legal assistance while dealing with legal tasks, litigations, contracts, dispute resolution and guide the organisation on taking an appropriate decision.

·         S/he should be skilled enough to come out with a desired outcome from the organisation’s point of view.

·         He/she should be able to take correct decisions and provide the necessary professional support.

·         S/he should advice whether all the court proceedings of the organisation are in compliance with the requirements of the legislation.

·         S/he will supervise, analyze and research the implication of laws, legislation, etc., that may affect the organisation business.

·         S/he advises the organisation to minimize legal exposure and liability

·         Collaborate with management to devise efficient defense strategies

·         Specify internal governance policies and regularly monitor compliance

·         Deal with complex matters with multiple stakeholders and forces

·         Support HR department in the preparation of disciplinary hearing documents.

·         Support in conducting investigations and prepare witnesses in advance of a disciplinary hearing.

Departments Support:

·         S/he will support in the review of supplier, contract of employment, donor and partners agreement reviews refencing to the relevant country laws

·         Provide clarification on legal language or specifications to the organisation and its management

·         Draft and solidify agreements, contracts, and other legal documents to ensure the organisation’s full legal rights

Work collaboratively with departments/sectoral heads to ensure compliance

Safeguarding:

To foster an inclusive working environment which is non-threatening and safe for all. An environment that addresses safeguarding adequately in its processes and where the barriers to raise and discuss concerns about safeguarding issues are identified and where possible mitigated.

Work Schedule:

The job of Legal Advisor is full time job and requires him/her to work in accordance to the organisation working and may be required to work after working hours

Values & Behaviors:

Strong commitment to upholding and promoting GOAL’s values; Respect, Integrity, Courage, Partnership and Humanitarianism.

Other duties:

Support in the review of HR handbook

Take lead in training staff on data protection policy

Network with GOAL Global Legal/Data Protection/HR departments to keep informed of disciplinary and employment contractual matters (related to HR)

Any other task assigned by the line manager.

COMMITMENTS:

GOAL’s recruitment procedure is fair and transparent which is also in line with the organization’s commitment to its integrity, honesty and culture. GOAL is committed to ensure that, its performance complies with the terms and conditions of relevant agreements, applicable laws & regulations.
Hence, pre-employment background checks will be conducted, and employees are required to read, understand, sign and implement different polices including safeguarding and child protection policy, Protection from Sexual Exploitation and abuse policy, sexual harassment policy, code of conducts and any other policy, rules and regulation of the organization. 

Job Requirements:

JOIN US

Do you want to join an exciting organization that brings high level impact to the community and add value to your professional advancement?  Then join us if you have:

·          Bachelor's/Master’s degree in law-related field

·         7 years’ experience as a Legal Counsel /lawyer and able to attend to routine administrative labour law among other related litigation tasks

·         Must be prepared to make ethical and moral decisions

·         Previous working experience as a Legal Counsel/ lawyer   in business/INGO sector

·         In-depth knowledge of administrative law and procedures

·         Good organisational, prioritization and time-management skills

·         Arbitration and mediation skills

·         Exemplary writing and editing skills, with proficiency in Microsoft Office: - Word, PowerPoint, Excel, Outlook etc.

·         Excellent communication, presentation, and interpersonal skills and analytical skills in both written and spoken; English, Amharic, and Afaan Oromo

·         Working well under pressure

·         Attention to detail

·         Ability to use your initiative.

·         Discretion in handling confidential matters and proactive approach to problem solving.

·         Excellent judgment and ability to anticipate legal issues or risks

·         High degree of professional ethics, integrity, and responsibility

Note: This description is not an exhaustive list of the skill, effort, duties and responsibilities associated with the position.

REMUNERATION and BENEFITS:

GOAL will pay a competitive basic salary based on the salary grading with addition benefits.

A chance to develop tangible experience.

Being part of a team who continue to make a real difference to the lives of the most vulnerable people.   

How To Apply:

APPLICATION PROCEEDURE:

Interested and qualified applicants need to submit ONLY once their non - returnable application with CV for one vacancy. The vacancy reference number along with the title & Duty station need to be written in the application letter and/or subject of the email. Applicants can apply using the following option.

Applicants can directly apply online usingwww.ethiojobs.net  orgoaljobs@et.goal.ie

GOAL strongly encourages female candidates to apply!

Only short-listed candidates will be contacted for an interview and exam.

Shortlisted candidates will need to submit other supporting documents upon request at later stage.

GOAL is not able to contribute towards any costs incurred by candidates during the recruitment process

Posted: 12.09.2021

Deadline: 12.19.2021

Job Category:
Human Resource and Recruitment, Legal, Management
Employment:

Location: GOAL Ethiopia

http://www.goal.ie/Ethiopia/159
የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ
Federal Document Authentication And Registration Agency


ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት

ቅርንጫፍ 1-ላንቻ
ቅርንጫፍ 2-መሳለሚያ
ቅርንጫፍ 3-መገናኛ
ቅርንጫፍ 4-ስድስት ኪሎ
ቅርንጫፍ 5-ጉለሌ
ቅርንጫፍ 6-አየር ጤና
ቅርንጫፍ 7-ቃሊቲ ቅርንጫፍ 8-ካሳንቺስ
ቅርንጫፍ 9-ንፋስ ስልክ ላፍቶ
ቅርንጫፍ 10-ልደታ
ቅርንጫፍ 11-ሲኤምሲ
ቅርንጫፍ 12-ቦሌ
ቅርንጫፍ 13-ጎጃም በረንዳ (መርካቶ)
ቅርንጫፍ 14 – ጀሞ

ተራ በመጠበቅ እና በወረፋ ጊዜዎን እንዳያጠፉ ቤትዎ እና ስራ ቦታዎ ሁነው
online ማንኛውም አይነት ጉዳይ እንሞላለን print አድርገው ብቻ የሚገለገሉበት ሲስተም ላይ አስገብተን በሚመችዎት መንገድ እንልክልዎታለን።
በቴሌግራም ብቻ ጉዳዮን ይጨርሳሉ።
https://t.me/GudayAsfetsami
@GudayAsfetsami
@GudayAsfetsami
በአዲሱ የንግድ ሕግ የተካተቱ አዳዲስ ጉዳዮች

1. መግቢያ
በሥራ ላይ የነበረዉ የንግድ ሕግ (1952 ዓ.ም) አገሪቷ ከደረሰችበት የንግድ እንቅስቃሴና ዘርፉ ከሚፈለገዉ ዕድገት አንፃር ብዙ ክፍተቶች ያሉበት መሆኑ እና የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ የንግድ ሕጉን መፈተሽ እና ማሻሻያዎችን ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ አዲሱ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2014 ሆኖ ታትሞ ሥራ ላይ እንዲዉል ተደርጓል፡፡ አዲሱ የንግድ ሕግ ከዚህ በፊት ከነበረው አንጻር በርካታ ለውጦች ተደርገዉበታል። የሕጉ መውጣት የኢትዮጵያን የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴን በአወንታዊ መንገድ ለመቀየር ከፍተኛ አስተዋጾ አለዉ። በዚህ አጭር ጽሁፍ የንግድ ሕጉን ዓላማዎች፣የንግድ ሕጉን ማሻሻል ያስፈለገበት ምክንያት፣የንግድ ሕጉ ማሻሻል ያለዉ ጠቀሜታ እና አዳዲስ የተካተቱ ጉዳዮች የምንመለከት ይሆናል፡፡

2. የንግድ ሕግ ዓላማዎች
አንድ ግለሰብ ነጋዴ ወይም የንግድ ማኅበር በዕለት ተዕለት የንግድ እንቅስቃሴው ከተለያዩ አካላት ጋር የውል እና ከውል ውጪ የሆኑ ግንኙነቶችን ይፈጥራል።

ለምሳሌ፦ አንድ የንግድ ድርጅት ለማምረት ወይም አገልግሎት ለመስጠት የሚያስፈልጉትን ግብዓቶች ከሚያቀርቡ ድርጅቶች፣ ምርቶቹን እና አገልግሎቶቹን ከሚገዙት ደንበኞች ወይም ሸማቾች፣ ለድርጅቱ ብድር ከሰጡ ወይም በሌላ ምክንያት ከድርጅቱ ገንዘብ የመጠየቅ መብት ካላቸው ሰዎች፣ ከንግድ ተወዳዳሪዎቹ፣ ከተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች እንዲሁም ከድርጅቱ ሠራተኞችና ሥራ አመራሮች ጋር ግንኙነት ይኖረዋል፤ ድርጅቱ ከባለሀብቶቹ የተለየ የራሱ የሕግ ሰውነት ያለው የንግድ ማኅበር ሲሆን ደግሞ ከማኅበርተኞቹ ጭምር ግንኙነት ይኖረዋል። ከላይ ከተገለጹት የንግድ ድርጅት ከሚፈጥራቸው ዘርፈ ብዙ ግንኙነት አኳያ የንግድ ሕጎች ሁለት ዋና ዋና ዓላማዎች አሏቸው፦ አንደኛው ዓላማ አንድ የንግድ ድርጅት ከላይ በተመለከትናቸው ውስብስብ ግንኙነቶች ውስጥ ተንቀሳቅሶ ሀብት እንዲያፈራ እና አትራፊ እንዲሆን የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ማበጀት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ከላይ ለተጠቀሱት ከአንድ የንግድ ድርጅት ጋር የተለያዩ ግንኙነቶች ለሚፈጥሩት አካላት መብቶች እና ቅቡልነት ያላቸው ፍላጎቶች ተገቢውን የሕግ ጥበቃ ማድረግ ነው። የንግድ ሕግ መድብል (ኮድ) እነዚህን ሁለት አንኳር ዓላማዎች ይጋራል። ይህ ሲባል ግን የንግድ ሕግ መድብል (ኮድ) ሁሉንም ከላይ የተመለከትናቸውን ግንኙነቶች አሟልቶ ይገዛል ማለት አይደለም።

3. የንግድ ሕጉን ማሻሻል ያስፈለገበት ምክንያት እና ጠቀሜታ
የንግድ ህጉ አሁን ያለውን ዘመናዊውን አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ሊመልስ በሚችል መልኩ ካልተቀረፀ ወይም ካልተዘጋጀ በሀገሪቱ አጠቃላይ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ የሆነ ጫና የሚኖረው በመሆኑ የንግድ ህግ ዘመናዊ መሆን ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም አሁን የሚመጡ አዳዲስ ዕድገቶችን ታሳቢ ተደርጎ መረቀቅ እና በተጨባጭ ያንን ሊመልስ በሚችል መልኩ መሰራት አለበት፡፡ የእኛ ሀገር የንግድ ህግ ከብዙ ዓመታት በፊት የተዘጋጀ በመሆኑ አሁን ያለውን አገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በንግድ ሂደት የሚፈጠሩ ችግሮች ሊመልስ የማይችልባቸው ምክንያቶች አሉ፡፡ ከነዛ መካከል አንዱ በንግድ ህጉ የተካተቱ በርካታ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ ባለመሆናቸው፣የሚፈፀሙትም ቢሆን አሁን ካለው አጠቃላይ የንግድ እና ኢኮኖሚ እንቅሳሴ ጋር የማይሄዱ በመሆናቸው፣ በተለይም በሀገራችን ከፍተኛ ችግር እየፈጠረ ያለው ከማህበራት ጋር ተያይዞ የሚታዩ ክፍተቶች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ከዚህ ቀደም የነበረው የንግድ ህግ ሊመልሳቸው የሚገቡ ጥያቄዎችን መመለስ ባለመቻሉ የመጣ ችግር ነው፡፡ በመሆኑም ክፍተቶቹን በመፈተሽ አሁን ካለው እና ዘመኑ ከሚጠይቀው ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተገናዘበ ዘመናዊ የንግድ ህግ ማደራጀት በማስፈለጉ የንግድ ህጉ እንደገና እንዲወጣ ተደርጓል፡፡

በዚህ ሕግ መሰረት የትኛውም እንቅስቃሴ ከኢኮኖሚ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ለምሳሌ የንግድ ማህበራት የሚቆጣጠራቸው ሕጉ ነው፡፡ የንግድ ምዝገባ ለማድረግም መነሻ ህጋቸው ይህ ህግ ነው፡፡ የዚህ ሕግ ዘመናዊ ሆኖ መደራጀቱ ለነጋዴው፣ ለንግድ ማህበራት፣ ለ3ኛ ወገኖች እና ሌሎች በርካታ ጉዳዮችን ዘመናዊ በሆነ መንገድ መደራጀታቸው ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ዘመኑ የሚጠይቀው ሕግ ተደንግጎ የወጣ፣ አሁን ካለው የስራ እንቅስቃሴ ጋር አብሮ የሚሄድ እና ለነጋዴው ግልፅ የሆነ የንግድ ሕግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ለልማታዊ ባለሀብቶች የሚያመች ሁኔታ በመፍጠር ረገድ በርካታ ጠቀሜታዎች ያሉት በመሆኑ በአግባቡ ልንጠቀምበት ይገባል፡፡

4. አዳዲስ የተካተቱ ጉዳዮች
ነባሩ የንግድ ህግ ጥራዝ በስድስት መጽሀፍት የተደራጀ ሲሆን፣ በአንደኛ መጽሀፍ ስለንግድ ስራና ነጋዴዎች፣ በሁለተኛ መጽሁፍ ስለንግድ ማኅበራት፣በሶስተኛ መጽሀፍ ስለኢንሹራንስና የማጓጓዣ አገልግሎት፣በአራተኛ መጽሀፍ ስለባንክና ተላላፊ ሰነዶች (የሚተላለፉ የገንዘብ ሰነዶች)፣በአምስተኛ መጽሀፉ ስለኪሳራ ህግ ፣ በስድስተኛ መጽሀፍ መሸጋገሪያ ድንጋጌዎች ሆኖ ዝርዝር ጉዳዮችን አካትቶ የተሰነደ ነው። በተደረገዉ ጥናት መጽሐፍት 3 እና 4 የንግድ ሕግ አካል ሳይሆኑ ራሳቸዉን ችለዉ የፋይናንስ አገልግሎት መድብል / Code / እንዲሆኑ እና መጽሀፍ አንድ፣ሁለት እና አምስት የንግድ ሕግ ተብሎ እንዲሻሻል ተደርጎ በአዲሱ የንግድ ሕግ ወጥቷል፡፡ በአዲሱ አዋጅ ያልተካተቱት የባንክ፣ የኢንሹራንስና፣ የማጓጓዣ ዘርፎችን የሚመለከቱ ጉዳዮች በቀድሞው አሠራር መሠረት የሚቀጥሉ ሲሆን አዲሱ የንግድ ሕግ በርካታ ማሻሻያዎችን እና አዳዲስ አሰራሮችን የያዘ ሆኖ ወጥቷል። ከእነዚህ ጥቂቶቹን እንመልከት።

 አንድ ግለሰብ ለብቻው ኩባንያ መክፈት እንዲችል ተፈቅዷል
አዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 534 እንደሚያሳየዉ አንድ ግለሰብ ብቻውን ኩባንያን መመስረት እንዲችል ተፈቅዷል። ይህም ሰዎች በቀላሉ ወደ ሥራ እንዲገቡ ያግዛቸዋል ።
 የንግድ ትርጓሜን መቀየር
በተሻረው ሕግ የተዘረዘሩት የንግድ አይነቶች 21 ብቻ ናቸው። ከነዚህ ውጪ ያሉት ንግድ አይደሉም ተብለው እንደሚገመቱ ባለሙያዎች ያስረዳሉ። አሁን ግን በአዲሱ የንግድ ህግ አንቀጽ 5 መሰረት የንግድ አይነቶችን ወደ 37 አድገዋል። በዚሁ ሕግ የንግድ ትርጉም ክፍት ነው። በግልፅ ካልተከለከለ በስተቀር ያተርፋል ብሎ እንደሙያ የያዘውን ሥራ አስመዝገቦ መቀጠል ይችላል። ይህ መሆኑ ደግሞ አዳዲስ የንግድ አይነቶችንና የፈጠራ ሐሳቦችን ያበርታታል ።
 ኃላፊነታቸው የተወሰነ የሙያ ሽርክና ማኅበራት (አንቀፅ 221)
በአዲሱ የንግድ ህግ ውስጥ ከተካተቱ ጉልህ ለውጦች መካከል አንዱ የሆነው ይህ አዲስ የሽርክና ማህበር አይነት፣ ሰዎች በተለይም የሙያ ስራዎችን ለመስራት በሙያ ከሚመስሏቸው ሌሎች ሰዎችና ለሙያው ደጋፊ የሆነ አገልግሎት ሊሰጡ ከሚችሉ አጋሮቻቸው ጋር ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ሆነው የሚያቋቁሙት፣ ኃላፊነቱም በሽርክና ማኅበሩ ሃብት ላይ ብቻ የተወሰነ የንግድ ማኅበር ነው በሚል በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 221 ላይ ተደንግጓል። ከቀደመው ሕግ በተቃራኒው አዲስ የጸደቀው አዋጅ ግለሰቦች በሙያቸው ተደራጅተው እንዲሠሩ በግልጽ ድንጋጌ አስቀምጧል። እያንዳንዱ ሙያ የሚጠይቀውን ሥነ ምግባር ይዘው ደንበኞቻቸውን የሚያስተናግዱ የሽርክና የሙያ ማኅበራት እንዲስፋፉ ያስችላል።

https://t.me/lawsocieties